Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የወንጀል ህግ.pdf


  • word cloud

የወንጀል ህግ.pdf
  • Extraction Summary

ውስጥ መኖር ማንም ሰው ሀ የመርከቡ ካፒቴን መኮንን ወይም ሠራተኛ ያለበትን እንደምልክት የመስጠት መርከብን የመጐጉብኘት የመመርመር የመቆጣጠርና የመሳሰለውን የደኅንነት እርምጃ የመውሰድ ግዴታ ወይም ለ የመርከቡን የባህር መዝገቦች መዝገቦች ወይም የሌሎች ሰነዶችን አያያዝ ወይም ሐጠ በባሕር ወይም በወደብ ላይ ጭነትን ፖስታን ወይም መንገደኞችን ማጓጓዝን ማሳፈርና ማውረድን መጫንና ማራገፍን ወይም መንቀሳቀስን ወይም መመሪያዎችን የጣሰ እንደሆነ የወንጀል ሕጉ ወይም ይህን የሚመለከት ልዩ ሕግ ሌላ ድንጋጌ ተፈፃሚ ካልሆነ በቀር በመቀጮ ወይም በማረፊያ ቤት እሥራት ይቀጣል።

  • Cosine Similarity

አንቀጽ ለወንጀል ስራ ማነሣሣትና አባሪነት የማነሳሳትና የአባሪነት ሙከራ ከዚህ በላይ ከአንቀጽ ቋቿ እስከ ሣ ከአንቀጽ ሣጃ አስከ ድረስ ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱ ሳይሞከር በቀረበት ጊዜ ወንጀሉ እንዲፈፀም የተደረገ የወንጀል ሥራ ማነሳሳት ሙከራ አንቀጽ ጣ አባሪነት አንቀጽ ሟ የአባሪነት ወይም የማነሣሣት ሙከራ አንቀጽ ከአንድ ወር እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እስራት ወይም ይህ አድራጐት ሊያስከትል ይችል የነበረው አደጋ በተለይ በጣም ከፍ ያለ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ያስቀጣል ማንም ሰው ከዚህ በላይ ከአንቀጽ ቋ እስከ ሣ ከአንቀጽ ጣ እስከ ድረስ ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱን ለመፈፀም ሀ ወታደሮችን የሽምቅ ተዋጊዎችን ሽፍቶችን ወይም ቅጥረኞችን የመለመለ ያቋቋመ ወይም ወደ አገር ውስጥ ያስገባ እንደሆነ ወይም ለ የጦር መሣሪያዎችን ጥይቶችን ስንቅን ገንዘብን ወይም እነዚህን የመሳሰሉትን ግዙፍ የሆኑ ነገሮችን ያዘጋጀ ያከማቸ ወይም ወደ አገር ያስገባ እንደሆነ ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ መገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ማንም ሰው ከዚህ በላይ ከአንቀጽ ቋቿ እስከ ሣ ከአንቀጽ ጣ እስከ ድረስ ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱ እንዲፈጸም ለማድረግ ወይም ለመደገፍ ሀ በንግግር በሥዕል ወይም በሁፍ አማካይነት በግልፅ የቀሰቀሰ እንደሆነ ወይም የወንጀል ሕግ ለ ሽፍቶች በአገር ውስጥ ወይም ከአገር ውጭም ቢሆን እንዲቋቋሙ ያደመ እቅድ ያወጣ ወይም የገፋፋ እንደሆነ ወይም ሐ እንደዚህ በመሳሰሉት ሽፍቶች ቡድን የገባ በእቅዱም የተባበረ ወይም ትዕዛዙን የተከተለ እንደሆነ ወይም መ ከውጭ አገር መንግሥታት የፖለቲካ ወይም ሌላ ድርጅት ወይም ከእነዚሁ ወኪሎች ጋር ግንኙነት ያደረገ ወይም በምስጢር ግንኙነት የተባበረ እንደሆነ ወይም ሠ የሕዝቡን ሞራል ዝቅ ለማድረግና እምነቱን ወይም የመቋቋም ኃይሉን ለማፍረስ በማቀድ በተቀናጀ ዘዴ ትክክለኛ ያልሆነ ጥላቻ የተሞላበት ወይም ያለውን አቋም የሚያፈርስ መረጃ በንግግር በጽሁፍ ወይም በስዕል የበተነ ወይም ያስታወቀ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ይህ አድራጐት ሊያስከትል ይችል የነበረው አደጋ በተለይ በጣም ከፍ ያለ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ ከባድ ሁኔታ በዚህ ምዕራፍ ወንጀሉ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት እንደሚያስቀጣ ሕጉ በደነገገባቸው ሁኬታዎች ሁሉ ፍርድ ቤቱ የሞት ቅጣትን የሚወስነው ሀ ወንጀሉ የተፈጸመው በአገሩ ላይ ሁከት በደረሰ ጊዜ ወይም ይኸው ሁከት ወይም የእርስ በርስ ጦርነት ወይም ከውጭ አገር ጋር የሚደረግ ጦርነት በሚያሠጋበት ጊዜ ወይም የውጭ መንግሥት ጣልቃ ገብነት በሚኖርበት ጊዜ ወይም በጸጥታ መታወክ የአስቸኳይ ሁኔታ አዋጅ ፀንቶ በሚቆይበት ጊዜ ወይም ልዩ ሁኔታዎች መኖራቸው በግልጽ በተነገረ ጊዜ እንደሆነ ወይም ለ አድራጐቶቹ የታቀዱትና የተፈጸሙት ከአድማ የተነሳ እንደሆነ ወይም የጦር መሣሪያ በያዙ ክፍሎች እንደሆነ ወይም ሐ ወንጀለኛው ከውጭ አገር ወይም ከውጭ መንግሥት የፖለቲካ ወይም ሌላ ድርጅት ባገኘው ሀብት የጦር መሣሪያ ወይም በማናቸውም አኳኋን በሚያገኘው ዕርዳታ ወይም ድጋፍ ወንጀሉን ፈሞ እንደሆነ ወይም መ በቦንብ በድማሚት ወይም በሌላ በማናቸውም በሚፈነዳ መሣሪያ ወይም በብዙ ሰው ላይ አደጋ ሊያደርስ በሚችል ይህንኑ በመሰለ የማሸበሪያ መሣሪያ ወይም ዘዴ ወንጀሉን ሰርቶት እንደሆነ ነው የወንጀል ሕግ በዚህ ምዕራፍ የተመለከተው ማናቸውም በጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል የተፈጸመው በተሾመ ወይም የመሪነት ሥልጣን በተሰጠው ሰው ወይም የግል ጥቅም ለማግኘት በመፈለግ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ከዚሁ ቅጣት ጋር በማጣመር ከአንድ መቶ ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ሊወስን ይችላል የውጭ አገር ዜጋ የሆነ ጥፋተኛ አምስት ዓመት ወይም ከዛ በላይ የሆነ ጽኑ አስራት ከተፈረደበት ቅጣቱን ከጨረሰ በኋላ ካገር እንዲወጣ ይወሰንበታል ሟ የክዳት የስለላ ወይም ምስጢር አሳልፎ የመስጠት ወንጀል ተፈጽሞ በተገኘ ጊዜ ሁሉ የወንጀሉ መፈጸሚያ የሆኑት ወይም ይህንኑ ጉዳይ የሚመለከቱት መሣሪያዎች ዕቃዎች የመልእክት ደብዳቤዎች ወይም ማስረጃዎች ሁሉ ይወረሳሉ አንቀጽ ንብረትን መውረስ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እንዲያስከብር በግልፅ አደራ የተጣለበት ሰው በዚህ ሕግ በአንቀጽ ቋጣ ሣ እና ማጣ ሣ እስከ እና ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱን በመፈፀም ጥፋተኛ ሆኖ የተፈረደበት እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ከሚፈርደው ከዋናው ቅጣት ጋር አጣምሮ የተፈረደበት ሰው ንብረት በሕግ መሠረት እንዲወረስ ለማዘዝ ይችሳል አንቀጽ ቋ ምዕራፍ ሁለት በውጭ አገር መንግሥት ላሳይ የሚደረጉ ወንጀሉች አንቀጽ በውጭ አገር መንግሥት ላይ የሚደረግ የተቃዋሚነት ድርጊት ማንም ሰው በኢትዮጵያ መንግሥት ግዛት ውስጥ ሆኖ የኢትዮጵያ መንግሥት ከውጭ አገር መንግሥት ጋር ያለውን ሰላማዊ ግንኙነት ለማበላሸት በሚችል አኳጓኋን ሀ በተንኮል ሥራ በሐሰት ውንጀላ በጥላቻ ስብከት ወይም በኃይል ሥራ የውጭ አገር መንግሥት ውስጣዊ የፖለቲካ ሥራ ወይም የውስጥ ፀጥታ እንዲናወጥ ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ በሚዋጉ በውጭ አገር መንግሥታት ጦርነት ውስጥ ኢትዮጵያ የማትገባ ስለመሆኑዋ በፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ በሚገባ የታወጀውን ወይም በሌላ ዓይነት ውሣኔ በመንግሥት የተገለጸውን ድንጋጌ የጣሰ እንደሆነ ወይም ሐ ጦርነት በሚያደርግ የውጭ አገር መንግሥት ላይ የጠላትነት ድርጊት የገፋፋ እንዲፈፀም የተስማማ ወይም ያበረታታ እንደሆነ ቢያንስ በሦስት ወር ቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ በውጭ አገር መንግሥታት መሪዎች መልዕክተኞች እና ሌሎች በአለም አቀፍ ሕግ ጥበቃ ባገኙ ሰዎች ላይ የሚፈጸም ወንጀል ማንም ሰው በኢትዮጵያ መንግሥት ግዛት ውስጥ በአንድ አገር መንግሥት ርዕሰ ብሔር የመንግሥት መሪ የውጭ ጉዳይ ሚሜኒስቴር መልዕክተኛ ወይም ቤተሰቡ ወይም ተከታዩ ወይም በዓለም አቀፍ ድርጅት ተወካይ ወይም በዓለም አቀፍ ጥበቃ ባገኘ ሌላ ሰው አካል ነፃነት ወይም ደህንነት ላይ ጉዳት ያደረሰ ወይም አደጋ የጣለ ወይም በሚሰራበት ተቋም የግል ቤቱ ወይም ተሽከርካሪው ላይ ጉዳት ያደረሰ ወይም ከላይ የተመለከቱትን ተግባራት ለመፈጸም የዛተ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ኑ እስራት ይቀጣል ቺ ወንጀሉ ሲፈፀም ከላይ በንዑስ አንቀጽ ከተመለከቱት ሰዎች የአንዱ ሕይወት አልፎ እንደሆነ ስለሰው መግደል የተደነገጉት አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀ የውጭ አገር መንግሥትን ግዛት መጣስ ማንም ሰው የዓለም አቀፍ ሕግን በመጣስ ሕገወጥ ድርጊት ለመፈፀም ሁከት ለማስነሳት ወይም አደገኛ የሆነ ድርጊት ለመፈፀም ሲል ሀ ወደ ውጭ አገር መንግሥት ግዛት ውስጥ የገባ እንደሆነ ወይም ለ በዚሁ መንግሥት ግዛት ውስጥ ሆኖ በዚሁ መንግሥት የሥልጣን ክልል ውስጥ የሚገኝ ተግባርን ያለአግባብ የፈፀመ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ የውጭ አገር መንግሥታትን ማዋረድ ማንም ሰው አንድን የውጭ አገር መንግሥት በቀጥታ ወይም መሪውን ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኘውን የዚህን የውጭ አገር መንግሥት የዲፕሎማቲክ አባል ተጠሪ ወይም መልዕክተኛ የሆነውን በአደባባይ በንግግር ወይም በአድራጐት ወይም በማናቸውም ሌላ አኳኋን ያዋረደ የሰደበ ስም ያጠፋ ወይም በሐሰት የወነጀለ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ቺ ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ በተለይም በሐሰት የመወንጀል ድርጊት ሲሆን እስራቱ ቢያንስ ሦስት ወር ይሆናል የወንጀል ሕግ ማንም ሰው ከኢትዮጵያ ጋር ሰላማዊ የወዳጅነት ግንኙነት ያለውን የውጭ አገር መንግሥት የታወቁ የሉዓላዊነት ምልክቶች ይልቁንም የዚሁ አገር መንግሥት እንደራሴ የሚያውለበልበውን አርማ ወይም ሰንደቅ ዓላማ በፀብ ስሜት በጥላቻ መንፈስ በንቀት ወይም ይህን በመሳሰለ በማናቸውም ስሜት የቀደደ ያቃጠለ ያጠፋ ያበላሸ የሰደበ ወይም በማናቸውም ሌላ አኳኋን ያዋረደ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ በመንግሥታት መካከል የተቋቋሙ ድርጅቶችን ማዋረድ ማንም ሰው በመንግሥታት መካከል የተቋቋመውንና ኢትዮጵያ አባል የሆነችበትን ተቋም ወይም ድርጅት ወኪል ወይም የታወቀውን ምልክቱን በአደባባይ ያዋረደ እንደሆነ በዚህ ሕግ በአንቀጽ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል አንቀጽ የውለታ መመለስ ሁኔታ በዚህ ምዕራፍ በውጭ አገር መንግሥታት ላይ የሚደረጉ ወንጀሎችን በተመለከተ የተደነገጉት በጠቅላላ ተፈጻሚ የሚሆኑት በሕጐቻቸው ለኢትዮጵያ ተመሣሣይ ጥበቃ ለሚሰጡ መንግሥታት ብቻ ነው ከላይ የተፃፈው ድንጋጌ ቢኖርም የአንቀጽ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ነው አንቀጽ የክስ አቀራረብ በዚህ ምዕራፍ በተመለከቱት ወንጀሉች ክስ የሚቀርበው ተበደልኩ የሚለው መንግሥት ወይም ድርጅት ወንጀለኛው እንዲቀጣለት ሲጠይቅና የፌዴራሉ የፍትህ ሚኒስትር ወይም ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሲፈቅድ ብቻ ነው ርዕስ ሁለት ዓለም አቀፍ ሕጐችን በመጣስ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ምዕራፍ አንድ መሠረታውያን ወንጀሎች አንቀጽ ዘርን ማጥፋት ማንም ሰው በሠላምም ሆነ በጦርነት ጊዜ በብሔር በብሔረሰብ በጉሣ በዘር በዜግነት በቀለም በሃይማኖት ወይም በፖለቲካ አንድ የሆነን ቡድን በመላ ወይም በከፊል ለማጥፋት በማሰብ የጥፋቱን ድርጊት በማደራጀት ትዕዛዝ በመስጠት ወይም ድርጊቱን በመፈፀም የወንጀል ሕግ ሀ በማናቸውም ሁኔታ የማኅበረሰቡን አባሎች የገደለ አካላዊ ወይም ኅሊናዊ ጤንነት ለ ሐ የጐዳ ወይም የአካል ጉዳት ያደረሰ ወይም ያጠፋ እንደሆነ ወይም የማኅበረሰቡ አባላት በዘር እንዳይራቡ ወይም በሕይወት እንዳይኖሩ ለማድረግ ማናቸውንም ዘዴ በሥራ ላይ ያዋለ እንደሆነ ወይም የማህበረሰቡን አባላት ወይም ሕፃናት በግዴታ ከሥፍራ ወደ ሥፍራ ያዛወረ ወይም የበተነ ወይም ሊሞቱ ወይም ሊጠፉ በሚችሉበት የኑሮ ሁኔታ እንዲኖሩ ያደረገ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ፅኑ እስራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ይቀጣል አንቀ ድ በሰላማዊ ሕዝብ ሳይ የሚፈፀም የጦርነት ወንጀል ማንም ሰው በጦርነት በጦርነት ግጭት ወይም በጠላት ወረራ ጊዜ የዓለም አቀፍ ሕግ ድንጋጌዎችንና የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግጋትን በመጣስ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ጉዳት ለማድረስ በማደራጀት በማዘዝ ወይም ድርጊቱን በመፈጸም ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ሀ ሰውን የገደለ ያሰቃየ ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ ያጉላላ ስነሕይወታዊ ሙከራዎችን ያደረገ በሰው አካል አእምሮ ወይም ጤንነት ላይ ከባድ ስቃይ ወይም ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ሌሎች ድርጊቶችን ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ ገንዘብ ዋጋ እንዳያገኝ ዋጋውን ዝቅ አድርጐ በማክሰር ሐሰተኛ ገንዘብ በማተም ሐ መ ሠ ረ ሰ ወይም በተደራጀ ፅቅድ ገንዘብን በማዋረድ ወይም በማናቸውም ሁኔታ አስቦ ሕዝብን ለረሀብ የዳረገ በችግር ላይ የጣለ ወይም በአጠቃላይ የሕዝቡን ኑሮ ያናጋ እንደሆነ ወይም ሕዝብን በኃይል ከሥፍራው እንዲፈናቀል ወይም እንዲበተን ያደረገ በተደራጀ ፅቅድ ከአገር ያስወጣ ወይም ወደ አንድ የግዞት ሥፍራ ወይም የግዴታ ሥራ ማከናወኛ ሥፍራ በመላክ እንዲታሰር ያደረገ እንደሆነ ወይም በጠላት የስለሳ አገልግሎት የጦር ኃይል ወይም የአስተዳደር ሥራ ውስጥ ተመልምሎ እንዲያገለግል ያስገደደ እንደሆነ ወይም በግዴታ ዜግነቱን እንዲያጣ ወይም ኃይማኖቱን እንዲለውጥ ያደረገ እንደሆነ ወይም የዝሙት አዳሪነት የብልግና ድርጊት ወይም የግብረ ሥጋ ድፍረት ተግባር እንዲፈጸም ያስገደደ እንደሆነ ወይም የማስፈራራት ወይም የማሸበር ድርጊት ያደረገ በወጆ በመያዣነት ያገተ ወይም የጅምላ ቅጣት የጣለ ወይም የበቀል ድርጊት ያደረገ እንደሆነ ወይም የወንጀል ሕግ ሸ ንብረትን የወረሰ ያወደመ ወይም ለራሱ ያደረገ ሕገወጥ ወይም ተገቢ ያልሆነ ግብር ወይም ቀረጥ የጣለ እንደሆነ ወይም ለወታደራዊ አገልግሉት ፍጹም አስፈላጊ ከሆነው በላይ ቀረጥና ግብር እንዲከፈል ያደረገ እንደሆነ ወይም ቀ ምግብን ለምግብ ማምረቻ የሚውሉ የእርሻ ቦታዎችን ሰብልን የቤት እንስሳትን የመጠጥ ውሃ አገልግሎቶችን የመስኖ ሥራዎችን የጤና ተቋማትን ወይም ትምህርት ቤቶችን የወረሰ ያፈረሰ ያጠፋ ከጥቅም ውጭ እንዲሆኑ ያደረገ ወይም ለእራሱ እንዲሆኑ ያደረገ እንደሆነ ወይም በ ታሪካዊ ሀውልቶችን የሥነ ጥበብ ሥራዎችን ወይም የማምለኪያ ቦታዎችን ያወደመ የወሰደ ከጥቅም ውጭ ያደረገ ለእራሱ ያደረገ ወይም በእነዚህ ላይ የኃይል ተግባር ያደረገ ወይም እነዚህን ነገሮች ለወታደራዊ ዓላማ ያዋለ እንደሆነ ወይም ተ አንደኛው ወገን በተቆጣጠረው ሥፍራ ላይ ለሚኖሩ ሰላማዊ ሰዎች አልባሣትን መኝታ መጠለያ የሕክምና መድኃኒትና መገልገያ ወይም ለኑሮ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ያላቀረበ እንዲቀርብላቸው ያላደረገ እንደሆነ ወይም ቸ ግጭት ከመፈጠሩ በፊት በተሰደዱበት ወይም ኗሪ በሆኑበት አገር ሕግ ወይም በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት እንደ ስደተኛ ወይም ዜግነት እንደሌላቸው የሚታወቁ ሰዎችን ያጠቃ ያፈናቀለ እንዲጠፉ ያደረገ ወይም በአግባቡ ያልያዘ እንደሆነ ወይም ኅኀ ዕድሜያቸው ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ልጆችን በጦርነት ውስጥ እንዲሣተፉ ለማድረግ ለወታደራዊ አገልግሎት አባልነት የመለመለ እንደሆነ ወይም ነ በተፈጥሮ አካባቢ ሳይ የተስፋፋ እና ለረዥም ጊዜ የሚቆይ ከባድ ጉዳት ሊያደርስ በሚችል መሣሪያ ወይም የውጊያ ስልት የተጠቀመ በዚሁም ምክንያት የአካባቢውን ነዋሪ ጤና እንዲታወክ ያደረገ እንደሆነ ወይም ኘ አደገኛ የሆነ ኃይል እንዲለቀቅ በሚያደርግና በዚሁም የተነሳ በሰላማዊ ነዋሪ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ በሚችል ሁኔታ ግድቦችን እና የኒውክሊየር የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ያጠፋ እንደሆነ ወይም አ በሕግ ከተቋቋሙና ለፍርድ ሂደት ዋስትና ከሚሰጡ መደበኛ ፍርድ ቤቶች ውጭ ቅጣትን የወሰነ እና ያስፈፀመ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ፅኑ እስራት ወይም ነገሩ በጣም ከባድ በሆነ ጊዜ በዕድሜ ልክ ዕኑ እስራት ወይም በሞት ይቀጣል አንቀጽ ድጳ በቁስለኞች በበሽተኞች በባሕር ወይም በአየር አደጋ ላይ ባሉ ሰዎች ወይም በጤና አገልግሎት ላይ የሚፈፀም የጦርነት ወንጀል ማንም ሰው ከዚህ በላይ በተመለከተው ሁኔታ ሀ በቁስለኞች በህመምተኞች በባህር ወይም በአየር አደጋ ላይ ባሉ በህክምና ወይም በመጀመሪያ እርዳታ ሠራተኞች ላይ የግድያ የማሰቃየት በሁኔታዎች የወንጀል ሕግ አስፈላጊ የሆነውን የጤና እርዳታን የመከልከል ርህራሄ በሌለው ሁኔታ ሰውን የመበደል ድርጊት የፈፀመ ወይም ማናቸውንም ሌላ የአካል ወይም የሕሊና ስቃይ እንዲደርስባቸው ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ ለጤና ጥበቃ ለእርዳታ መስጫ ክፍል ወይም ለመጓጓዣ የሚያገለግሉትን ዕቃዎች መሥሪያ ቤት ወይም ግምጃ ቤት ሕግን ተቃራኒ በሆነ መንገድ ወይም ያለአግባብ ወይም ለወታደራዊ አገልግሎት ፍፁም አስፈላጊ ሆኖ ከሚገኘው ውጭ ያፈረሰ ከአገልግሎት ውጭ ያደረገ ወይም የወሰደ እንደሆነ ወይም ሐ የጤና አገልግሎት ሠራተኞች የሀይማኖት አገልግሎት ሰጪዎችና ጋዜጠኞች የሞያ ሥነ ምግባር እና መመሪያ ከሚያዘው ውጭ እንዲሠሩ ወይም የሞያ ሥነ ምግባር እና መመሪያ በሚያዘው መሠረት እንዳይሠሩ ወይም ቁስለኞችን በሽተኞችን ወይም ሠላማዊ ሰዎችን ለመጠበቅ የወጡ ሌሎች መመሪያዎችን ወይም ደንቦችን ተላልፈው እንዲሠሩ ያስገደደ እንደሆነ በአንቀጽ ሮ እንደተመለከተው ይቀጣል በንዑስ አንቀጽ ላይ ሀ ቁስለኛ እና ህመምተኛ ማለት የመከላከያ ሠራዊት አባልም ይሁን ወይም ሰላማዊ ሰው በደረሰበት የመቁሰል አደጋ በበሽታ ወይም በሌላ አካሉ ላይ በደረሰበት ጉዳት ወይም በአእምሮው ላይ በደረሰበት መረበሽና አለመረጋጋት ምክንያት ህክምና የሚያስፈልገው ሰው ሲሆን አራሶችን አዲስ የተወለዱ ህፃናትን እና እንደእርጉዝ ሴቶች የመሳሰሉትን አስቸኳይ የሕክምና ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸውንና ከማናቸውም ዓይነት የጠላትነት እንቅስቃሴ ታቅበው የሚገኙትን ያጠቃልላል ለ በባህር ወይም በአየር አደጋ ላይ ያለ ማለት ወታደርም ሆነ ወይም ሰላማዊ ሰው በባህር ላይ ወይም በሌላ ውሀ ውስጥ ወይም በአየር ላይ ባጋጠመው ችግር ወይም አደጋ ምክንያት ህይወቱ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ያለና ከማናቸውም ዓይነት የጠላትነት እንቅስቃሴ የታቀበ ሰውን ሁሉ ያጠቃልላል አንቀጽ ድ በታሰሩ የጦር ምርኮኞች እና በቲጋዙ ሰዎች ላይ የሟፈፀመ የጦርነት ወንጀሉች ማንም ሰው ከዚህ በላይ በተመለከተው ሁኔታ ሀ በታሰሩ የጦር ምርኮኞች ወይም በተጋዙ ሰዎች ላይ የመግደል የማሰቃየት ተግባር ወይም ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ የሆነ የማጉላላት በደል እንዲፈጸምባቸው ያደራጀ ያዘዘ ወይም ድርጊቱን የፈጸመ እንደሆነ ወይም ለ በዚህ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎች በጠላት የስለላ የወታደራዊ ወይም የአስተዳደር ሥራ እንዲያገለግሉ ያስገደደ እንደሆነ ከዚህ በላይ በአንቀጽ ድሮ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀ ድ በጦርነት ጊዜ የሚደረግ ገፈፋ ዘረፋና የባህር ውንብድና ማንም ሰው በጦርነት ጊዜ ለወታደራዊ አገልግሎት አስፈላጊ ነው በሚል ሰበብ የባሕር ወንበዴነትን የዘረፋን የገፋፊነትን ወይም ሕገ ወጥ የሆነ የንብረት ማፍረስን ወይም የመውሰድን ተግባር ያዘጋጀ እንዲዘጋጅ ያዘዘ ወይም ይህንኑ ድርጊት የፈጸመ እንደሆነ ከዚህ በላይ በአንቀጽ ድሮ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል አንቀጽ ድክ መገፋፋትና ማሰናዳት ማንም ሰው ከዚህ በላይ ባሉት አንቀጾች ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱን ለመፈጸም እንዲፈጸም ለማድረግ ወይም አፈጻጸሙን ለመርዳት በማሰብ ሀ በንግግር በሥዕል ወይም በጽሁፍ በአደባባይ የገፋፋ ወይም ያደፋፈረ እንደሆነ ወይም ለ አንድ የወንበዴ ማህበር ወይም ቡድን እንዲቋቋም ከሌሎች ጋር ያደመ ዕቅድ ያወጣ ወይም እንዲቋቋም የገፋፋ ወይም ራሱ ያቋቋመ በዚሁ ማህበር ወይም ቡድን ውስጥ የገባ ዓላማውን የተከተለ ወይም ትዕዛዙን የፈፀመ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ ሮድጽሯ ለጠላት ሊደረግ የሚገባውን ተግባር መጣስ ማንም ሰው በጦርነት ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕጐችንና የሰብአዊነት አጠባበቅ ስምምነቶችን ተቃዋሚ በሆነ መንገድ ሀ የተማረከውን መሣሪያውን ለምርኮ ያስረከበውን ወይም በማናቸውም ዓይነት ለመከላከል የተሳነውን ወይም የመከላከል ተግባሩን የተወውን ጠላት የገደለ ወይም ያቆሰለ እንደሆነ ወይም ለ የሙት አካል ያጉደለ እንደሆነ ወይም ሐጠ በጦር ሜዳ ላይ በአንድ የጠላት ቁስለኛ በሽተኛ ወይም ሬሳ ላይ ስርቆት የፈፀመ ወይም ኃይልን ተጠቅሞ ገፈፋ የፈፀመ እንደሆነ ወይም ከነዚህ ተግባሮች አንዱን ለመፈፀም በማሰብ ቁስለኛውን በሽተኛውን ወይም ሬሳውን የበረበረ የያዘ ወይም የኃይል ተግባር የፈፀመበት እንደሆነ ወይም መ ከእነዚህ ተግባራት አንዱ እንዲፈጸም ያዘዘ እንደሆነ በጽኑ እስራት ወይም ወንጀሉ በጣም ከባድ በሆነ ጊዜ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ድጃ ሕገወጥ በሆኑ የጦር መሣሪያዎች መገልገል ማንም ሰው ኢትዮጵያ በተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ወይም በኢትዮጵያ ሕግ በግልፅ በተከለከሉ የጦር መሣሪያዎች ወይም የውጊያ ዘዴዎች ጠላትን የወጋ ወይም በእነዚህ መሣሪያዎች ወይም የውጊያ ዘዴዎች ጠላት እንዲወጋ ትዕዛዝ የሰጠ እንደሆነ ከሦስት ወር በማያንስ ቀላል እስራት ይቀጣል ነገሩ ከባድ ከሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ወይም የወንጀሉ አፈፃፀም በጣም ከባድ እንደሆነ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ይቀጣል አንቀጽ ድጂ የጦርነት ማቆም ውልን ወይም የሰላም ስምምነትን ማፍረስ ማንም ሰው የጦርነት ማቆም ውል ወይም የሰላም ስምምነት መፈረሙን በግልፅ እያወቀና ትዕዛዝ ከተሰጠው በኋላ ውጊያው እንዲቀጥል ያደረገ ወይም በማናቸውም ሌላ አድራጐጉት ከውሉ ወይም ከስምምነቱ ግዴታዎች አንዱን አስቦ ያፈረሰ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል ማንም ሰው በጦርነት ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕግን በሚቃወም ሁኔታ በኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣኖች የታወቀ የመከላከያ ሠራዊት አባል ወይም የድጋፍ ሰጪ ኃይል አባል ሳይሆን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ላይ ተቃዋሚ የሆነ ተግባር በመፈጸም በአገልግሎቶቹ በማመላለሻ መሣሪያዎቹ በመገናኛ ወይም በማጓጓዣ ዘዴዎቹ ላይ ጉዳት የሚያደርስ ተግባር የፈጸመ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ፅኑ እስራት ወይም ነገሩ በጣም ከባድ እንደሆነ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ይቀጣል የሟ ገባቸውን ማጓደል ማንም ሰው ዓለም አቀፍ ሕግጋትን በመጣስ ቁስለኛን በሽተኛን ወይም በእስራት ወይም በግዞት ላይ የሚገኘውን የጦር ምርኮኛ በጨካኝነት ያሰቃየ ወይም የኃይል ድርጊት የፈጸመበት እንደሆነ ወይም በእነዚሁ ሕግጋት የተረጋገጡለትን መብቶች እንዳይጠቀምባቸው የከለከለ ወይም በእነዚሁ መብቶች መጠቀም እንዳይችል ያዘዘ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ፍትህን መከልከል ማንም ሰው በጦርነት ወይም በወረራ ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕግን በመጣስ ሰላማዊ ሰው ቁስለኛ እሥረኛ ወይም የጦር ግዞተኛ ሰብአዊነቱን የሚያረጋግጥለትን በሕግ መሠረት የመዳኘት መብቱን እንዲሁም በነፃነት ራሱን የመከላከል መብቱን እንዲያጣ ያደረገ ወይም እንዲከለከል ያዘዘ እንደሆነ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እስራት ይቀጣል ምዕራፍ ሁለት በሰብአዊ ድርጅቶች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀ በዓለም አቀፍ ሰብአዊ ድርጅቶች ሳላይ የሚፈፀም የጠላትነት ድርጊት ማንም ሰው በሰላም ጊዜ አስቦ ሀ በቀይ መስቀል ወይም በቀይ ጨረቃ ማህበር ወይም እነዚህን በመሳሰሉ ሌሎች ሰብዓዊ ድርጅቶች ሠራተኞች ወኪሎች ወይም ባልደረቦች ወይም በነዚሁ ድርጅቶች ጥበቃ ሥር በሚገኙ ሰዎች ላይ የፀብ ሥራ ወይም የኃይል ድርጊት የፈጸመ የዛተ ወይም ያዋረደ እንደሆነ ወይም ለ የነዚህን ድርጅቶች ዕቃዎች ግዙፍ ሥራዎች ወይም ማከማቻዎች ያፈረሰ ወይም ጉዳት ያደረሰባቸው እንደሆነ በቀላል እስራት የተፈጸመው ወንጀል ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈፀመው በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እሥራት ይሆናል ማንም ሰው እስቦ ሀ ከዚህ በላይ የተመለከቱትን የዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ድርጅቶችን አርማዎች ወይም መለያ ምልክቶች ያለፈቃድ የያዘ የሰቀለ ወይም በእነዚሁ የተገለገለ እንደሆነ ወይም ለ የፀብ ድርጊት ለማዘጋጀት ወይም ለመፈጸም በማቀድ በዚህ ዓይነት አርማ ወይም መለያ ምልክት ወይም በማናቸውም በዓለም አቀፍ ሕግ በታወቀ የደህንነት ምልክት በተለይም በነጭ ሰንደቅ ዓላማ ያለአግባብ የተገለገለ እንደሆነ የወንጀል ሕግ በቀላል እስራት ወይም ወንጀሉ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ በዕርቅ መልእክተኛ ላይ የጠላትነት ድርጊት መፈፀም ማንም ሰው ከጠላት ወገን የእርቅ መልዕክተኛ ወይም የዕርቅ ድርድር አሳብ አቅራቢ ሆኖ የሚመጣውን ወይም ከእርሱ ጋር ያለውን ሰው ያጉላላ ያስፈራራ ያዋረደ ወይም ያለአግባብ የያዘ እንደሆነ በቀላል እስራት ይቀጣል ርዕስ ሦስት ወታደራዊ ወንጀሎች እና በመከላከኪያየ ሠራዊት እንዲሁም በፖሊስ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ምዕራፍ አንድ ወታደራዊ ወን ሎች ክፍል አንድ የአገልግሎት ግዴታን በመጣስ የሚደረጉ ወንጀሉች አንቀጹ ወታደራዊ አገልግሎትን እንቢ ማለት ሙ ቺ አንቀጽ ማንም ሰው በውትድርና የመቀጠር ወይም በወታደርነት የማገልገል ሕጋዊ ግዴታውን ከመፈጸም ለማምለጥ በማሰብ በወታደርነት እንዲመዘገብ ወይም በክተት አዋጅ መሠረት በየግንባሩ ቀርቦ እንዲያገለግል በግል በተደረገለት ጥሪ በአደባባይ በተለጠ ፈ ማስታወቂያ ወይም በመገናኛ ብዙኃን በተነገረ ማስታወቂያ የተላለፈውን ትዕዛዝ ያልፈጸመ እንደሆነ በቀላል እስራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው የጦር አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦር ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እስራት ይሆናል ዘጅ የጥሪ ትዕዛዝን አለማክበር ማንም ሰው በወታደርነት መመልመልን ወይም ማገልገልን ባለመፈለግ ሳይሆን የጥሪ ትዕዛዝን ያልፈፀመ እንደሆነ በተለይም ለወታደራዊ ምልመላ የሚደረገውን ምርመራ ፍተሻ የልምምድ ትምህርት ወይም ማናቸውንም ወታደራዊ ግዴታ እንዲፈፅም የተደረገለትን ጥሪ ያላከበረ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ ቺ ወንጀሉ የተፈፀመው በጦርነት ጊዜ ወይም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በታወጀበት ወይም ከፍተኛ የተፈጥሮ ወይም ሰው ሠራሽ አደጋ ወይም የሕዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ በተከሰተ ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እስራት ይሆናል አንቀጽ ከአገልግሎት ግዴታ ለማምለጥ ታስቦ የሚደረግ የችሎታ ማጣት ሙ ማንም ሰው በራሱ ወይም በሌሳ ሰው አድራጐት አካሉን በሙሉ ወይም በከፊል በማጉደል በሰውነቱ ወይም በጤንነቱ ላይ ጉዳት በማድረስ ወይም ፈቅዶ በሚፈጽመው በሰውነቱ ወይም በጤንነቱ ላይ ጉዳት በሚያደርስ በማናቸውም ሌላ ዘዴ በመጠቀም አካሉን በሙሉ ወይም በከፊል በማጉደል ለጊዜው ወይም ለዘወትር ለአገልግሎት ብቁ ሆኖ እንዳይገኝ ያደረገ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ ማንም ሰው ከዚህ በላይ ለተመለከተው ዓላማ በማናቸውም አድራጉት በባለጉዳዩ ፈቃድ ባለጉዳዩን በከፊል ወይም በሙሉ አገልግሎት መስጠት እንዳይችል ያደረገ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል ሟ ወንጀሉ የተፈጸመው የጦር አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦር ክተት አዋጅ በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥራ አምስት ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እስራት ይሆናል አንቀጽ ከወታደራዊ አገልግሎት ለማምለጥ የሚፈፀም ማጭበርበር ቺ ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል ለዘወትር ወይም ለጊዜው ከወታደራዊ አገልግሎት ግዴታው ለማምለጥ አግባብ ያላቸውን የሲቪል ወይም ወታደራዊ ባለሥልጣኖችን ለማታለል በታቀዱ ዘዴዎች የተጠቀመ እንደሆነ በተለይም ሐሰተኛ የምስክር ወረቀት በማቅረብ ሐሰተኛ በሆነ ቃል ወይም ሰነድ በመታገዝ ወይም በሽተኛ ወይም አካለ ጐደሎ በመምሰል ያታለለ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው የጦር አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦርነት ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እስራት ይሆናል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ኩብለላ ቺ ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል ከወታደራዊ አገልግሎት ግዴታው ለማምለጥ በማሰብ የጦር ክፍሉን ወይም የወታደራዊ ነክነት ያለውን የአገልግሎት ተግባሩን ትቶ የሄደ ወይም በፈቃድ ከሄደ በኋላ ወደ ክፍሉ ወይም ወደ አገልግሎት ተግባሩ ሳይመለስ የቀረ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው የጦር አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦር ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ ከሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እስራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ያስቀጣል አንቀጽ ያለአግባብ መቅረት ቺ ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል ከወታደራዊ አገልግሎት ለማምለጥ በማቀድ ሳይሆን ሀ ያለፈቃድ ወይም ከአቅም በላይ ባልሆነ ምክንያት ወታደራዊ ክፍሉን ትቶ የሄደ እንደሆነ ወይም ወታደራዊ ተግባሩን ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ ወይም ለ ከአቅም በላይ ባልሆነ ምክንያት ከተሰጠው ፈቃድ ወይም የዕረፍት ጊዜ ያሳለፈ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ይሆናል አንቀጽ አስቦ ወደ ጦር ክፍሉ ተመልሶ አለመምጣት ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል በጦርነት ጊዜ ሀ ከክፍሉ ጦር ተቋርጦ ከተለየ በኋላ ወደክፍሉ ወይም በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው የወገን ጦር ሳይቀላቀል የቀረ እንደሆነ ወይም ለ ከተማረከ በኋላ ነፃነቱን እንዳገኘ ወዲያውኑ ለአንድ የጦር ክፍል ወይም ወታደራዊ ባለሥልጣን ቀርቦ ሳያመለክት ወይም ወደ ምድቡ ሳይመለስ የቀረ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ወንጀሉን የፈጸመው አስቦ ለዘለቄታው ከወታደራዊ ግዴታው ለመሸሽ እንደሆነ ከሶስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት ለመድረስ በሚችል ፅኑ እስራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ ክፍል ሁለት በወታደራዊ ሥልጣን ያለአግባብ መገልገል ከአገልግሎት ግዴታ ያለአግባብ ነፃ ማድረግ ማንም ሰው የተሰጠውን የሥራ ወይም ወታደራዊ ሥልጣን ከመጠን በላይ በማሳለፍ ወይም በዚሁ ሥልጣኑ ያለአግባብ በመገልገል ሌላውን ሰው ከወታደራዊ አገልግሉት ግዴታው ነፃ ያደረገው እንደሆነ እጅግ ቢያንስ በስድስት ወር ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ ወንጀሉ የተፈጸመው የጦርነት አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦርነት ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ ከሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይሆናል አንቀጽ በበታች ላይ የሚፈፀም ዛቻና የኃይል ድርጊት ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል በትእዛዙ ወይም በስሩ ባለ ሰው ላይ የዛተበት የእጅ እልፊት የፈፀመበት ወይም ከዚሁ ሰው ጋር በሚያደርገው ግንኙነት ያዋረደው እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ ወንጀሉ የተፈጸመው በጭካኔ ወይም በኃይል ተግባር በጦር መሣሪያ ወይም በሌላ አደገኛ መሣሪያ እንደሆነ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል ክፍል ሦስት የወታደራዊ አገልግሎት ተግባሮችን በመጣስ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ንዑስ ክፍል አንድ መልካም ሥርዓቶችንና ዲስፕሊንን ለአደጋ በሚያጋልጥ ሁኔታ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል ከሥነሥርዓት ደንብ መተሳላለፍ አንቀጽ ጃ ውጭ የሆኑትን ጠቅላላ የመከላከያ ኃይሎችን የአገልግሎት ሥራ ትዕዛዞች ወይም ደንቦች አስቦ የጣሰ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ ቺ ወንጀሉ የተፈጸመው የጦር አደጋ ምልክት በተሰጠበት የጦርነት ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ ከሆነ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል ሟ ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት ሆኖ በሰላም ጊዜ ከሆነ ቅጣቱ የሥነ ሥርዓት ዲስፕሊን ቅጣት ይሆናል በጦርነት ጊዜ ወይም በሌላ ከባድ ሁኔታ ከሆነ ግን ከአንድ ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል ሥልጣኑ ወይም ወታደራዊ ተግባሩ ኦፊሴላዊ የሆነ ሪፖርት ወይም መግለጫ ማዘጋጀት ወይም የአገልግሎት ሰነድ ቅጽ መሙላት የሆነ ማንም ሰው ሀ አስቦ ፍሬ ነገርን ወይም እውነተኛውን ነገር የለወጠ ወይም የደበቀ ወይም በፊርማው ሊረጋገጥ በሚገባው ሰነድ ላይ ማናቸውንም ዝርዝር ወይም አሀዝ ሳይሞላ የተወ እንደሆነ ከሁለት ዓመት እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እሥራት ይቀጣል ለ የሥራ ግዴታው ሆኖ እያለ በእንቢተኝነት ቃለጉባኤ ሪፖርት ወይም መግለጫ ሳያዘጋጅ ወይም ሳይልክ የቀረ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ ወንጀሉ የተደረገው በቸልተኛነት ከሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል ሟ የዕረፍት ፈቃድን ለማግኘት ወይም ጊዜውን ለማራዘም በማሰብ አግባብ ካለው ባለሥልጣን እውነቱን የደበቀ ወይም ለዚሁ ባለሥልጣን ሐሰተኛ ማረጋገጫ ያቀረበ ማንኛውም የመከላከያ ሠራዊት አባል በቀላል እሥራት ይቀጣል ። ወንጀሉን የፈፀመው የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት እንደሆነ የዚህ ሕግ የአንቀጽ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆኑበታል አንቀጽ ህ የመከላከያ ሠራዊት የደንብ ልብስን ምልክትንና ሽልማትን ያለአግባብ ማምረትና ለንግድ ማዘዋወር ማንም ሰው ሳይፈቀድለት ወታደራዊ የደንብ ልብሶችን ምልክቶችን ወይም ሽልማቶችን የሠራ ያከማቸ ለሽያጭ ያቀረበ ወይም የሸጠ የገዛ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ በእጅ ያስገባ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ወንጀሉን የፈፀመው የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት እንደሆነ የዚህ ሕግ የአንቀጽ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆነበታል አንቀጽ ሞቋ የመከላኪያ ሠራዊት የደንብ ልብስን ምልክትንና ሽልማትን በማይገባ መልበስ ማንም ሰው ሳይፈቀድለት ወታደራዊ የደንብ ልብሶችን ምልክቶችን ወይም ሽልማቶችን ለብሶ ወይም አድርጉ የተገኘ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ቋፅ ወታደራዊ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መጣስ ሙ ማንም ሰው ለመከላከያ ሠራዊት አስፈላጊ የሆነውን ነገር ወይም ወታደራዊ ጥቅምን ለመጠበቅ መንግሥት ወይም የሚመለከተው የሲቪል ወይም ወታደራዊ ባለሥልጣን ያወጣውን ደንብ ትዕዛዝ ወይም መመሪያ የጣሰ እንደሆነ በዚህ ሕግ በሌላ ድንጋጌ በተለይ የሚቀጣ ካልሆነ በስተቀር ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከሦስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ያስቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ቋ ወታደራዊ ትዕዛዞች እንዲጣሱ ለማድረግ ሌላውን ሰው ማነሣሣት ማንም ሰው ወታደራዊ ትዕዛዞች እንዳይፈጸሙ ሥነ ሥርዓት እንዳይከበር ወይም ወታደራዊ ግዴታ እንዲጣስ በአደባባይ ቢሆንም ባይሆንም ያነሳሳ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ማንም ሰው ይህንኑ ወንጀል ለመፈጸም ቡድን ንቅናቄ ወይም ሕገወጥ ስብሰባ ያደራጀ ወይም በቡድኑ በንቅናቄው ወይም በሕገወጥ ስብሰባው ተካፋይ እንደሆነ ወይም በሥራው ዕቅድ ውስጥ የገባ ወይም ማህበርተኛ በመሆን ተካፋይ የሆነ ወይም ለዚህ አይነት ድርጊት አስተዋፅኦ ያደረገ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም ይህ አድራጐት ሊያስከትል ይችል የነበረው አደጋ በተለይ በጣም ከፍ ያለ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት ይቀጣል ወንጀሉን የፈፀመው የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት እንደሆነ የዚህ ሕግ የአንቀጽ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆኑነበታል አንቀጽ ቋ የተወሰኑ ወታደራዊ ሥፍራዎችን እና ዕቃዎችን ለመጠበቅ የወጡ ክልከላዎችን መጣስ ማንም ሰው ያለፈቃድ ወይም ሕገወጥ በሆነ መንገድ በወታደራዊ ባለሥልጣኖች ወይም ወታደራዊ በሆኑ ምክንያቶች ሰው እንዳይደርስበት በተከለከለ ወታደራዊ ሥፍራ የሥራ ቦታ ወይም በማናቸውም ሌላ ሥፍራ ገብቶ የተገኘ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ቺ ይህንን የመሳሰለ ወታደራዊ ሥፍራ የሥራ ቦታ ወይም ማናቸውም ሌላ ሥፍራ ወይም ይህን በመሰለ ሥፍራ የሚገኝ የሥራ ቦታን ወይም የመሣሪያን ወይም የሌላ ፅቃ መግለጫን ፕላንን ንድፍን ፎቶግራፍን ወይም ማናቸውም ሌላ ምስልን የሠራ የወሰደ ያዘጋጀ ያባዛ የገለጸ ወይም ለሌላ ሰው አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ቋ ጠቅላላ ትዕዛዞችን ወይም መመሪያዎችን ወደሐሰት መለወጥ ወይም ማጥፋት የአንቀጽ ሮሀ እና ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ማንም ሰው አስቦ ሀ ወታደራዊ ምልመላ ወይም ወታደራዊ አገልግሎት የሚመለከታቸው ዜጐችን ወይም የመከላከያ ኃይሎችን ጥቅም ወይም ፍላጐት በሚመለከት የተደረገ ማናቸውንም ዓይነት ትዕዛዝን ወይም ለወታደራዊ አገልግሎት ዕቃ እንዲቀርብ የወንጀል ሕግ የተሰጠ ትዕዛዝን አስመስሎ የሠራ ወይም ወደ ሐሰተኛነት የለወጠ ያጠፋ ወይም እንዲጠፋ ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ ይህን አስመስሎ የተሠራውን ወይም ወደ ሐሰት የተለወጠውን ትዕዛዝ ወይም መመሪያ የተገለገለበት እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም እንደነገሩ ከባድነት ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል ቺ ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት እንደሆነ ቅጣቱ ከስድስት ወር የማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም መቀጮ ይሆናል አንቀጽ ጀቋ በመከላኪያ ሠራዊት እና በወታደራዊ ግዴታዎች ላይ የሚፈፀሙ ሙ ቺ ሟ ወንጀሎችን አለማስታወቅ ማንኛውም ሰው ወታደራዊ ኩብለላ ወይም የወታደራዊ አመፅ ወንጀል መዘጋጀቱን ወይም መፈጸሙን እያወቀ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ሳይኖር ለባለሥልጣን ሳያስታውቅ የቀረ ወይም እንዳይፈጸም ለማገድ ወይም ወንጀለኛው እንዲያዝ የሚቻለውን ያሳላደረገ እንደሆነ የኩብለላ ወይም የአመጹ ወንጀል ቢያንስ የተሞከረ እንደሆነ በቀላል እሥራት ነገሩ ከባድ ሲሆን ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ዕኑ እሥራት ይቀጣል ወንጀልን ለባለሥልጣን የማስታወቅ ግዴታን ባለመፈጸም ለተደረገ ወንጀል የሞያ ወይም የሥልጣንን ምስጢር መብት እንደመከላከያ አድርጐ ለማቅረብ አይቻልምል ወንጀሉ የተፈጸመው በጦርነት ጊዜ ከሆነ የስጋ ዝምድናንና በፍቅር ወዳጅነት የተሳሰረ ግንኙነትን ልዩ የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች አድርጐ ለማቅረብ አይቻልም አንቀጽሽ የክዳትና የስለላ ወንጀሎችን አለማስታወቅ ስለአገር ደህንነትና ስለአገር መከላከያ አንቀጽ ቋ ወታደራዊ ምስጢርን መግለፅ ቺ ማንኛውም ሰው በዚህ ሕግ ከአንቀጽ ጣፃ ከተደነገጉትና በተለይ ከፍ ያለ ቅጣት ከሚያስከትሉት የክዳትና የስለላ ወንጀሎች ውጭ በሆነ ሁኔታ በጠቅላላው በሕዝብ ዘንድ በግልፅ ያልታወቁትንና በጠባያቸው ከፍተኛ ቁም ነገር በመያዛቸው ምክንያት ላልተፈቀደለት ሰው ወይም ለሕዝብ እንዳይገለጹ በምስጢር የሚጠበቁትን ወታደራዊ ምስጢርነት ያላቸውን ማናቸውንም ዓይነት ሰነዶች ወይም መረጃዎች ላልተፈቀደለት ሰው ወይም ለሕዝብ የገለጸ ወይም ያስተላለፈ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማያንስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ወንጀሉ የሚመለከተው በተለይ የተጠበቁትን ሰነዶች ወይም መረጃዎች እንደሆነ ወይም ወንጀለኛው እነዚህን ሰነዶች በሚገባ የሚያውቃቸው ወይም እንዲጠብቃቸው የወንጀል ሕግ የተመደበ ወይም አደራ የተቀበለ ሠራተኛ እንደሆነ ወይም ወንጀሉ ከባድ ወይም የተለየ አደጋ ሊያስከትል የሚችል እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት የማያንስ ፅኑ እሥራት ይሆናል ሟ ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት እንደሆነ ቅጣቱ በንዑስ አንቀጽ ቋ ለተመለከተው ድርጊት ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት በንዑስ አንቀጽ ለተመለከተው ደግሞ ከሶስት ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት ይሆናል አንቀጽ ቋወጁ የሀሰት ወይም የሚያደናግር መረጃ ማንም ሰው ወታደሮች በእንቅስቃሴ ላይ ሆነው ወይም ተግባራቸውን በመፈጸም ላይ እያሉ ለወታደራዊ ጥቅም ተብሎ የታዘዘውን የጥንቃቄ አርምጃ ለማሰናከል ወይም ለማገድ ወይም የመከላከያ ሠራዊት እንቅስቃሴዎችን ወይም የውጊያ ዕቅዶችን ለማሰናከል ወይም የሚያሰናክል አደጋ እንዲደርስባቸው ለማድረግ ወይም ወታደሮች ከሥነ ሥርዓት ውጭ እንዲሆኑ ወይም እንዳይታዘዙ ለማነሳሳት ወይም በህዝቡ መካከል አለመረጋጋትና ሁከት እንዲነሳ ለማበረታታት ትክክል አለመሆናቸውን እያወቀ አስቦ የሐሰት ወሬዎችን የነዛ ወይም ያሰራጨ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ወይም ወንጀሉ ከባድ ሲሆን እስከ ዕድሜ ልክ ሊደርስ በሚችል ፅኑ እሥራት ይቀጣል ክፍል ሦስት የወል ድንጋጌዎች አንቀጽ ቋ በአደጋ ወይም በጦርነት ጊዜ ቅጣት የሚከብድበት ሁኔታ ከዚህ በላይ ባሉት ሁለት ክፍሎች ውስጥ ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱ የተፈጸመው በሥራው ላይ ባለ የመከላከያ ሠራዊት አባል ላይ ወይም በመከላከያ ኃይል ወይም በአጋዥ ኃይል ላይ ወይም በወታደራዊ ጥቅሞች ላይ ሆኖ ወንጀሉ የተፈጸመው የአደጋ ምልክት በተሰጠበት ጠቅላላ የጦር ክተት በታወጀበት ወይም በጦርነት ጊዜ እንደሆነና ቅጣቱን የሚያከብድ ሌላ ልዩ ድንጋጌ ከሌለ ፍርድ ቤቱ ሀ በቀላል እሥራት ምትክ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እሥራት ለ ቅጣቱ ኑ እሥራት በሆነ ጊዜ በዚህ ሕግ ጠቅላላ ክፍል ስለጽኑ እሥራት የተደነገገው ከፍተኛ የቅጣት ጣራ እንደተጠበቀ ሆኖ የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት አጠፌታ ድረስ ከፍ በማድረግ ለመወሰን ይችላል ቢሆንም የኩብለላ ወይም የአመጽ ወንጀልን ወይም ዕቅድን ወንጀሉ በቸልተኛነት ሲፈጸምና እንደሚያስቀጣ በሕጉ ላይ ተደንግጐ ሲገኝ ፍርድ ቤቱ የወንጀል ሕግ ሀ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ምትክ ከሶስት ዓመት የማይበልጥ የፅኑ እሥራት ቅጣት ለ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ምትክ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ የፅኑ እሥራት ቅጣት ለመወሰን ይችላል ፍርድ ቤቱ መቀጮ በሚወስንበት ጊዜ ተፈጻሚ በሆነው ድንጋጌ መሠረት ሕጉ የደነገገውን የመቀጮ መጠን አጠፌታ ድረስ ለመወሰን ይችላል ሟ አንቀጽ ቋወ በአፍቅሮ ንዋይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች የጽኑ እሥራት ቅጣትን የሚያስከትሉ ወንጀሎች ባጋጠሙ ጊዜ ሁሉ ጥፋተኛው ወንጀሉን የፈጸመው በአፍቅሮ ንዋይ ምክንያት እንደሆነ እንደነገሩ ከባድነትና እንደወንጀለኛው የሀብት መጠን ፍርድ ቤቱ ከእሥራት ቅጣቱ ጋር ከመቶ ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ አጣምሮ ሊወስን ይችላል ምዕራፍ ሦስት በፖሊስ ላይም ተፈፃሚ መሆናቸው አንቀጽ የአፈፃፀም መርህ ከዚህ በላይ ባሉት ሁለት ምዕራፎች ውስጥ ቅጣትን ያስከትላሉ ተብለው ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱን የፈፀመው የፖሊስ አባል እንደሆነ ወይም ወንጀሉ የተፈፀመው በሥራ ላይ ባለ የፖሊስ አባል ላይ እንደሆነ ይህ ወንጀል በሌላ ድንጋጌ የሚያስቀጣ ካልሆነ በስተቀር ከዚህ በላይ ባሉት ሁለት ምዕራፎች ውስጥ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ በሚሆኑበት ጊዜ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ልዩ ተግባርና አቋም ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት የወንጀል ሕግ አንቀጽ ሣ የመንግሥት ሠራተኞችን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በፖሊስ ላይ ተፈፃሚ መሆናቸው በፖሊስ ተቋም በአገልግሎት ግዴታና ደህንነት ላይ ስለሚፈጸሙ ወንጀሎች ከዚህ ቺ አንቀጽ ሙ ቺ በላይ ከተደነገጉት ድንጋጌዎች በተጨማሪ በዚህ ሕግ የመንግሥት ሠራተኞችን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች አንቀጽ እስከ በፖሊስ አባሎች ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ የወንጀሉ ድርጊት በዚህ ርዕስ ወይም በአራተኛው መጽሐፍ በርዕስ ሦስት ድንጋጌዎች ያለአግባብ ጥቅምን ስለማግኘት ያለአግባብ ስለማጥፋት ወይም ሥራዎችን በማያመች አኳኋን ስለመምራት አንቀጽ ጄ እና ሂቿ ወይም ከአንቀጽ እስከ ሀ እንዲሁም የሥራ ምስጢርን ስለመግለጽ አንቀጽ ወይም አንቀጽ እና ወንጀሉ ወታደራዊ ጠባይ የያዘ ወይም የመንግሥት ሠራተኛን የሚመለከት መሆኑን በመመርመር ተገቢ ሆኖ የሚያገኘውን ድንጋጌ ተፈጻሚ ያደርጋል። ማንም ሰው በሐሰት የተዘጋጀ የምስክር ወረቀት መሆኑን እያወቀ ሌላውን ሰው ለማታለል የተገለገለበት እንደሆነ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው ቅጣት ይቀጣል አንቀጽ ተደራራቢ ወንጀሎች ማንም ሰው ሐሰተኛ የምስክር ወረቀት ሐሰተኛ የምስክርነት ማስረጃ ወይም እርሱን የማይመለከተውን ወይም እንዲገለገልበት ያልታሰበውን ትክክለኛ የምስክር ወረቀት አግኝቶ በዚሁ አስቦ በመጠቀም ተጨማሪ ወንጀል ለመፈጸም የተገለገለበት እንደሆነ በተለይም የእምነት ማጉደል ወይም የማታለል ወንጀል ሆኖ ወንጀሉ ቢያንስ ተሞክሮ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ስለወንጀል መደራረብ የቅጣት ማክበጃ ድንጋጌዎችን አንቀጽ ቿ በመከተል ቅጣቱን ይወስናል አንቀጽ ሐሰተኛ የቃል አሰጣጥና ምዝገባ ማንኛውም አሠሪ የሆቴል ወይም የማደሪያ ቤት ባለቤት ወይም ሥራ አስኪያጅ ወይም በሕግ መሠረት ለባለሥልጣኖች መቆጣጠሪያ እንዲሆን የግለሰቦችን ወይም የድርጊቶችን ዝርዝር እንዲመዘግብ ግዴታ የተጣለበት ማንኛውም ሌላ ሰው አስቦ ሀ አውነተኛ ያልሆነውን የሰው ስም ቀንና ዘመን ወይም የሰው ወይም የዕቃ መግለጫዎችን የመዘገበ ያስመዘገበ ወይም እንዲመዘገብ የፈቀደ እንደሆነ ወይም ለ በእውነተኛ ሁኔታው መሠረት ሳይመዘግብ ወይም እንዲመዘገብ ሳያደርግ የቀረ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ቺ ጥፋተኛው ወንጀሉን የፈፀመው በጥቅም ፍላጐት እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት ያላነሰ ቀላል እሥራትና መቀጮ ይሆናል የወንጀል ሕግ አንቀጽ የሐሰት ሥራ ለመፈፀም የሚያገለግሉ መሣሪያዎችና መሥሪያዎች ማንም ሰው ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ሊገለገልባቸው በማሰብ ኦፊሴላዊ ጽሁፎችን የምስክር ወረቀቶችን ዲፕሎማዎችን ወይም ሰነዶችን ወደ ሐሰተኛነት ለመለወጥ ወይም በሐሰት ለመፍጠር የሚያገለግሉ መሣሪያዎችንና መሥሪያዎችን ወይም ቁሳዊ ነገሮችን የሠራ በእጁ ያስገባ የያዘ የሰጠ ወይም ለሽያጭ ወይም ለስጦታ ያቀረበ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ጥፋተኛው እንደነዚህ ዓይነቶቹን መሣሪያዎችሃ መሥሪያዎች ወይም ቁሳዊ ነገሮች ለማናቸውም ዓይነት አገልግሎትች ከመዋላቸው በፊት በራሱ ነፃ ፈቃድ ያጠፋቸው እንደሆነ ከማናቸውም ቅጣት ነፃ ይሆናል ምዕራፍ ሦስት ዕቃዎችን ወደ ሐሰት መለወጥ አንቀጽ ፅ ዕቃዎችን ወደ ሐሰተኛነት መለወጥና ጥራታቸውን ማርከስ ማንም ሰው ሌላውን ሰው ለማታለል በማሰብ የንግድ ዕቃዎችን ወደሐሰተኛነት የለወጠ አስመስሎ የሠራ ወይም ጥራታቸውን ያረከሰ ወይም ወደሌላ የለወጠ እንደሆነ ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ማዘዋወር ማንም ሰው ሌላውን ሰው ለማታለል አስቦ ወደ ሐሰተኛነት የተለወጡትን መስሎ የተሠሩትን ወይም ጥራታቸው የረከሰውን ወይም ወደ ሌላ የተለወጡትን የንግድ ዕቃዎች እንደ እውነተኛ እንዳልተለወጡ ወይም ምንም ጉድለት እንደሌለባቸው በማስመሰል ለሽያጭ ያቀረበ የሸጠ በሕዝብ እጅ እንዲዘዋወሩ ያደረገ እንደሆነ ቺ ወንጀሉ በቸልተኛነት ሲፈፀም ከአሥር ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ የሚያስቀጣው ሁኔታው በጣም ከባድ ሆኖ አድራጊውም ልዩ የሆነ ጥንቃቄ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት ሲሆን በተለይም በነጋዴነቱ ምክንያት የዚህ ዓይነቱን ጥንቃቄ መፈፀም የሚገባው ሆኖ ሲገኝ ነው የወንጀል ሕግ አንቀጽ እ ፅቃዎችን ወደአገር ማስገባት ወደውጭ መላክ በእጅ ማድረግና ማከማቸት ማንም ሰው ሌላውን ሰው ለማታለል በማሰብ ወይም ለማታለያ የታሰበ መሆኑን እያወቀ ወደ ሐሰተኛነት የተለወጡትን ወይም ሐሰተኛ የሆኑትን ወይም የተበላሹትን ወይም ጥራታቸው የረከሰውን የንግድ ዕቃዎች ወደ አገር ውስጥ ያስገባ ወደውጭ አገር የላከ በእጅ ያደረገ ወይም ያከማቸ እንደሆነ ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት እና በመቀጮ ይቀጣል አንቀ ቅጣትን ማክበድና ተጨማሪ ቅጣቶች ቺ አድራጊው ከዚህ በላይ የተመለከቱትን ወንጀሎች ሙያው አድርጐ ይዞ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እሥራትና እንደነገሩ ከባድነት ከብር አምስት ሺህ ባላነሰ መቀጮ ይቀጣል ፅቃዎቹን የመውረስና ፍርድን የመግለፅ ድንጋጌዎች በማናቸውም ጊዜ የተጠበቁ ናቸው አንቀጽ ጤናን በሚጉዳ አኳኋን የንግድ ዕቃን ወደ ሐሰት መለወጥና ጥራቱን ማርከስ ጤናን ለመጉዳት የሚችሉ ምግቦችን ሸቀጦችን እና ለጤንነት ጠንቅ የሆኑ ወይም የተበላሹ የንግድ ዕቃዎችን ስለመሥራት ጥራታቸውን ስለማርከስና ስለመሸጥ የተመለከቱት ድንጋጌዎች አግባብነት ሲኖራቸው ተፈጻሚ መሆናቸው እንደተጠበቀ ነው አንቀጽ ጽድ ርዕስ ሁለት የሕዝብ ጥቅምን የሚመለከት ምስጢርን መግለፅ አንቀጽ ወታደራዊ ምስጢርን መግለፅ ማንኛውም ወታደር ወይም በመከላከያ ኃይል አገልግሎት ውስጥ የሚገኝ ሰው ቺ ገ ክዳትንና ስለላን በሚመለከት ከሚያስቀጡት ሁኔታዎች አንቀጽ ጣቷ ውጭ በሥራው ወይም በወታደራዊ ግዳጅ ምክንያት ያወቀው ሆኖ በጠባዩ ምስጢር የሆነውን ወይም ምስጢር ሆኖ እንዲጠበቅ የታዘዘውን ወይም ለሕዝብ እንዳይገለጽ የተከለከለውን መረጃ ሰነድ ወይም ፍሬ ነገር የገለፀ ወይም ያስተላለፈ እንደሆነ ሥራው ወይም ግዳጁ ከተፈፀመ በኋላ ቢሆንም እንኳን ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ቅጣቱ ከአሥራ አምስት ዓመት የማይበልጥ ዕኑ እሥራት የሚሆነው ሟ የወንጀል ሕግ ሀ ወንጀሉ የሚመለከተው በምስጢር ኮድ አሀዝ የተያዘ መረጃን ወይም ሰነድን እንደሆነ ወይም አድራጊው ምስጢሩን እንዲጠብቅ በግልፅ አደራ የተጣለበት ወይም ምስጢሩን እንዳይገልፅ የመሐላ ቃሉን የሰጠበት እንደሆነ ወይም ለ ወንጀሉ ልዩ በሆነ ጥቅም ላይ ጉዳት አድርሶ እንደሆነ አንቀጽ ሙ ቺ ሟ ነው ወንጀሉ በቸልተኛነት ተፈጽሞ እንደሆነ ከዚህ በላይ በንዑስ አንቀጽ ለተመለ ከተው ቀላል ወንጀል ቅጣቱ ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት ወይም መቀጮ በንዑስ አንቀጽ ለተመለከተው ከባድ ወንጀል ደግሞ ከሦስት ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት ይሆናል የሥራ ምስጢርን መግለፅ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ አንቀጽ በአንቀጽ በተመለከተው ድንጋጌ በተገለፀው መሠረት ምስጢር ሆኖ ሊጠበቅ የሚገባውን እና በሥራው ምክንያት ያወቀውን ማናቸውንም ዓይነት ሰነድ መረጃ ወይም ፍሬ ነገር ሥራውን ወይም ሹመቱን ከለቀቀ በኋላ ቢሆንም እንኳ የገለጸ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ጥፋተኛው የተለየ ምስጢር የመጠበቅ ግዴታ ወይም እምነት የተጣለበት ወይም ወንጀሉ በተለይ ከፍ ያለ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ቅጣቱ ከአስር ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት ሲሆን ቅጣቱ በንዑስ አንቀጽ ለተመለከተው ቀላል ወንጀል ከብር አንድ ሺህ የማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት በንዑስ አንቀጽ ለተመለከተው ወንጀል ደግሞ ከሦስት ዓመት ያልበለጠ ቀላል እሥራት ይሆናል ደ እንዲገለፅ የተፈቀደ ምስጢር ለህዝብ ጥቅም ሲባል አግባብ ባለው የሲቪል አስተዳደራዊ ወይም ወታደራዊ ባለሥልጣን የጽሁፍ ፈቃድ ከተሰጠ በኋላ በፍርድ ቤት ወይም ሥልጣን ባለው በማናቸውም ምርመራ በሚያደርግ ፍርድ ቤት ፊት የተደረገ የምስጢር መግለፅ አያስቀጣም ሀ በሞያ ወይም በሥራ ምክንያት የታወቀ ምስጢርን መግለፅ የማናቸውም እምነት አገልጋይ የሕግ አማካሪ ጠበቃ ነገረ ፈጅ የሽምግልና ዳኛ አስታራቂ ሽማግሌ ልዩ አዋቂኤክስፐርት ነባሪ አስተርጓሚ ውል አዋዋይ የግል ድርጅት ዳይሬክተር የሥራ መሪ ተቆጣጣሪ ወይም በፍትሐብሔር ወይም በንግድ ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ምስጢር መጠበቅ የሚገባው ማንኛውም ሠራተኛ ሐኪም የጥርስ ሐኪም የመድሀኒት ቅመማ ባለሙያ ፋርማሲስት አዋላጅ ነርስ ቺ ሟ የወንጀል ሕግ ወይም ሌላ ረዳት የህክምና ሠራተኛ ወይም ሌላ በሙያው ወይም በሥራው ምክንያት የተገለጠለትን ምስጢር በሙያ ሥራው ላይ ሳለም ሆነ ሥራውን ከለቀቀ በኋላ የገለጸ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል በሞያ ሥራ መለማመድ ትምህርት ምክንያት ሊያውቅ የቻለውን ምስጢር የገለጸ ተማሪ በሙከራ ላይ ያለ ሠራተኛ ወይም ተለማማጅ ሠራተኛ በንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል ምስጢር የመግለፁ ወንጀል የተፈጸመው በቸልተኛነት እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብ ቅጣቱ ከብር አንድ ሺህ የማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ዓመት የማይበልጥ ቀሳል እሥራት ይሆናል አንቀጽ እንዲገለፅ የተፈቀደ ምስጢር ምስጢር መግለፅ የማያስቀጣው ሀ ምስጢሩ ሊጠበቅለት የሚገባው ሰው በግልፅ ፈቃድ ከሰጠ በኋላ እንደሆነ ለ ምስጢሩን በያዘው ሰው አሳሳቢነት ወይም ጠያቂነት አግባብ ያለው የበላይ የሙያ ወይም የቁጥጥር አካል የጽሁፍ ፈቃድ ሰጥቶ እንደሆነ ሐ በአንድ በተወሰነ ጉዳይ ሳላይ የተሰጠን ግልፅ የፍርድ ቤት ውሳኔ መሠረት በማድረግ ተገልጾ እንደሆነ ወይም መ ለሕዝባዊ ተግባር ሲባል በፍርድ ችሎት እንዲመሰክር ወይም ላንዱ ባለሥልጣን መግለጫ እንዲሰጥ የሕጉ ልዩ ድንጋጌ የሚፈቅድ ወይም የሚያዝዝ እንደሆነ ነው በሕግ በፍርድ ቤት ወይም በሚመለከተው ባለሥልጣን ምስጢር እንዲገልጽ የታዘዘ ሰው የሚስጢር መጠበቅ ግዴታውን ምክንያት በማድረግ ምስጢሩን ለመግለጽ እንቢተኛ ለመሆን አይችልም በማናቸውም ምክንያት ሀይማኖታዊ ኑዛዜ እንዲገለፅ ለማስገደድ አይቻልም አንቀጽ የሳይንስ የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ ምስጢርን መግለፅ ማንም ሰው ባለቤቱን ወይም ባለይዞታውን ለመጉዳት ወይም ጥቅም ለማግኘትም ሆነ ለማስገኘት በማሰብ በሕግ ወይም በውል ወይም በሥራው ኃላፊነት ምክንያት ያለበትን ግዴታ በመጣስ በምስጢር መጠበቅ የሚገባውን ማናቸውንም የኢኮኖሚ የሳይንስ ወይም የቴክኖሎጂ ግንባታ ዘዴ ወይም መረጃ የኢንዱስትሪን ወይም የንግድን የሳይንስን ሥነ ጥበብ ምስጢር ወይም በሥራ ላይ የሚውልበትን ጥበባዊ ዘዴ ሊገለፅለት ለማይገባ ሰው የገለፀ እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት እና ከአሥር ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ለአገር መከላከያ ጠቃሚ የሆነ የሳይንስ ወይም የስነጥበብ ምስጢር የተገለጸ እንደሆነ ርዕስ ሦስት በመንግሥት ሥራ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ ትርጓሜ የመንግሥት ሠራተኛ ማለት በመንግሥት መሥሪያ ቤት ወይም በመንግሥት ልማት ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ ተሹሞ ተመድቦ ወይም በሕዝብ ተመርጦ በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ሥራን የሚያከናውን ማንኛውም ሰው ነው የመንግሥት መሥሪያ ቤት ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግሥት በጀት የሚተዳዳር እና የፌደራል ወይም የክልል መንግሥት ስራዎች የሚከናወኑበት ማናቸውም መሥሪያ ቤት ነው ቺ የመንግሥት ልማት ድርጅት ማለት የመንግሥት ባለቤትነት ድርሻ በሙሉ ወይም በከፊል ያለበት የፌደራል ወይም የክልል መንግሥት የልማት ድርጅት ወይም የአክስዬን ማህበር ነው ሟ በዚህ ርዕስ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም ካላሰጠው በቀር ጥቅም ማለት ሀ በገንዘብ ወይም በማናቸውም ዋጋ ባለው መያዣ ወይም በሌላ ንብረት ወይም በንብረት ላይ ባለ ጥቅም መብት የሚተመን ማናቸውም ስጦታ ብድር ክፍያ ወሮታ ወይም ኮሚሽን ለ ማናቸውም ሹመት ቅጥር ወይም ውል ሐ ብድርን ግዴታን ወይም ማናቸውንም ዕዳ በሙሉም ሆነ በከፊል መክፈል ማስቀረት ማወራረድ ወይም ከነዚህ ነገሮች ነፃ ማድረግ መ ከተመሰረተ ወይም ካልተመሰረተ የአስተዳደር የፍትሐብሔር ወይም የወንጀል ክስ ወይም ካስከተለው ወይም ከሚያስከትለው ማናቸውም ቅጣት ወይም የችሎታ ማጣት በማዳን ወይም ይህን በመሰለ ዘዴ የሚደረግ አገልግሎት ወይም ውለታ ሠ ማናቸውንም መብት ተግባር ወይም ግዴታ መፈጸም ወይም ከመፈጸም መታቀብ የወንጀል ሕግ ረ ከላይ ከተዘረዘሩት ሁኔታዎች ውጭ በገንዘብ የማይተመን ማናቸውም ሌላ ጥቅም ወይም አገልግሉት እና ሰ ከዚህ በላይ ከፊደል ተራ ሀ እስከ ረ ከተጠቀሱት ጥቅሞች አንዱን ማቅረብ ጥቅሙ የሚገኝበትን መንገድ ማመቻቸት ወይም ይህንኑ በሚመለከት የተስፋ ቃል መግባት ወይም መቀበል ነው የማይገባ ጥቅም ማለት ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ወይም አግባብ ባልሆነ መንገድ የተገኘ ጥቅም ነው አንቀጽ ጥቅም የማግኘት ወይም የመጉዳት ሐሳብ ግምት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በቀር የሙስና ወንጀሎቹ የተፈፀሙት የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ወይም ለመጉዳት መሆኑ በተደነገገ ጊዜ በአንቀጹ ውስጥ የተመለከተው ግዙፋዊ ፍሬ ነገር ድርጊት እንደተፈፀመ ከተረጋገጠ ድርጊቱ የተፈፀመው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራስ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ወይም የሦስተኛ ወገንን መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት እንደሆነ ይገመታል አንቀጽ መርህ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ ርዕስ ከተመለከቱት ወንጀሎች አንዱን ባደረገ ጊዜ ከዚህ በታች የተፃፉት የቅጣት ድንጋጌዎች ይፈፀሙበታል ቺ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የተከሰሰበት በወንጀለኛነት የፈጸመው ወይም ሳይፈጽም በግድፈት የተወው ተግባር የተሠጠውን ሥራ በሚሠራበት ጊዜ የተፈፀመ እንደሆነና ተግባሩም መደበኛ ሕግ የሚፈጸምበት ሆኖ ነገር ግን በመንግሥት ሥራ ላይ በመሆኑና በእርሱ ላይ ከተጣለው እምነት የተነሣ ያለበትን ግዴታ በመጣሱ ቅጣቱ የሚከብድ ሲሆን በዚህ የወንጀል ሕግ በሌሎች ርዕሶች የተደነገጉት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ ሟ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የማይገባ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ በተሰጠው ኃላፊነት ወይም ተግባር ማድረግ የሚገባውን እንዳያደርግ ወይም ማድረግ የማይገባውን እንዲያደርግ ከሌሳ ሰው ላይ ጥቅም የተቀበለ ወይም የጠየቀ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ጥቅም ለማስገኘት የተሰጠውን ስልጣን ወይም የሕዝብ አደራ ያለአግባብ የተገለገለበት እንደሆነ ወይም ማንኛውም ሰው ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት እንዲደርስ ለማድረግ በማሰብ ለመንግሥት ሠራተኛ ። ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የማይገባውን ጥቅም ለራሱ ለማግኘት አስቦ ሀ ሊከፈል የማይገባ መሆኑን ወይም በሕግ ከተወሰነው ታሪፍ በላይ መሆኑን እያወቀ ቀረጥ ግብር ልዩ ልዩ ገቢ ወይም ልዩ ልዩ የገቢ ጥቅም ምንዳ ደመወዝ ካሣ ወይም ሌላ ወጪ የሰበሰበ ወይም እንዲሰበሰብ ያዘዘ እንደሆነ ለ ማንኛውቸም ዕቃ ወይም ክፍያ በሚያስረክብበት ወይም በሚሰጥበት ጊዜ ማስረከብ ወይም መክፈል ከሚገባው አሳንሶ ያስረከበ ወይም የከፈለ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ከአስር ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራትና እስከ አሥራ አምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ወንጀሉ የተፈፀመው ከዚህ በላይ አንቀጽ ከተመለከቱት ሁኔታዎች በአንዱ እንደሆነ ቅጣቱ ከሰባት ዓመት እስከ አሥራ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እሥራትና ከሠላሳ ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል ወንጀሉ የተፈፀመው ከዚህ በላይ በአንቀጽ ደፎ በተመለከቱት ሁኔታዎች እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እሥራትና ከሃምሳ ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል ወንጀሉ የተደረገው በቸልተኛነት እንደሆነ በቀላል እሥራትና በመቀጮ ያስቀጣል ያለአግባብ ጉዳይን ማጓተት አንቀጽ ማ ንኛውም የመንግስት ሠራተኛ በኃላፊነቱ ወይም በሥራው ምክንያት በቀረበለት ጉዳይ ላይ ጥቅም ካለው ማንኛውም ሰው በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ጥቅም ለማግኘት በጉዳዩ ላይ ጥቅም ያለውን ማንኛውንም ወገን ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት ሲል ከሕግ ወይም ከሥራ ደንብ ወይም መመሪያ ወይም ከተለመደው አሠራር ውጭ ያለ በቂ ምክንያት ያልወሰነ ወይም ያዘገየ ወይም ባለጉዳይን ያጉላላ እንደሆነ በደንብ መተላለፍ ከሚያስቀጡት ሁኔታዎች ውጭ በሆነ ጊዜ እንደነገሩ ሁኔታ በመቀጮ ወይም በቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ጂ ዋጋ ያለውን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማግኘት ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ተገቢ ምክንያት ሳይኖረው ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማናቸውንም ዋጋ ያለውን ነገር የተቀበለ እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ ንብረትን የፋይናንስ አቋምን ወይም ስጦታ መቀበልን ማስመዝገብ እንደሚገባ በሕግ ወይም በደንብ በተደነገገ ጊዜ አለማሳወቅ ወይም አለማስመዝገብ በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሰረት ያስቀጣል ሟ በአገሩ ወይም በአካባቢው ባህል ወይም ልማድ መሰረት እንደተራ የወዳጅነት ምልክት የሚሰጥ ዋጋ ያለው ስጦታ መቀበል ወይም ከቅርብ የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ ወይም ከቅርብ ወዳጅ ስጦታ ማግኘት በዚህ አንቀጽ ለተመለከተው ወንጀል ማቋቋሚያ አይሆንም አንቀጽ ቿ ያለአግባብ ፈቃድ መስጠት እና ማፅደቅ ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ አስቦ ብቁ ላልሆነ ወይም በሕግ ሊሰጠው ለማይገባው ሰው ማናቸውንም የንግድ ወይም የሥራ ፈቃድ የሰጠ ወይም ያጸደቀ እንደሆነ ወይም አንድ ነገር የሚከናወንበትን ቦታ ያለአግባብ የፈቀደ ወይም የሰጠ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል አንቀጽ ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ የመንግሥት ሠራተኛ የሆነ ወይም የነበረ ማንም ሰው ሀ የኑሮ ደረጃው አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት የመንግስት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ሕጋዊ ገቢ የበለጠ እንደሆነ ወይም ለ ያለው ንብረት ወይም የገንዘብ ምንጭ አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት የመንግስት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ሕጋዊ ገቢ ጋር የማይመጣጠን እንደሆነ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ወይም ያለው ንብረት ወይም የገንዘብ ምንጭ በእጁ እንዴት ሊገባ እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በቀር እንደሁኔታው የንብረቱ መወረስ ወይም ለባለቤቱ መመለስ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ቺ ከላይ በንዑስ አንቀጽ ጳለ የተጠቀሰው ወንጀል በፍርድ ቤት እየታየ ባለበት ጊዜ አንድ ሰው ከተከሳሽ ጋር ካለው ቅርበት ወይም ሌሎች ሁኔታዎች የተነሳ ለተከሳሹ ባለአደራ በመሆን አንድን ንብረት ወይም የገንዘብ ምንጭ እንደያዘ ወይም ከተከሣሹ በስጦታ እንዳገኘ ፍርድ ቤት ካመነበት ጉዳዩን በሌላ ማስረጃ ካላፈረሰ በስተቀር ንብረቱ ወይም የገንዘብ ምንጩ በተካሣሹ ይዞታ ሥር እንደሆነ ይቆጠራል የወንጀል ሕግ ክፍል ሁለት የሥራ ግዴታን በመጣስ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ የሥራ ኃሳፊነትን ባለመወጣት የሚፈፀም ወንጀል ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ ግዴታ ተግባሩን በአግባቡ ሳይፈጽም በመቅረቱ በመንግሥት በሕብረተሰቡ ወይም በግለሰብ ጥቅም ላይ ጉዳት አድርሶ እንደሆነ ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ በወንጀሉ ምክንያት ከባድ ጉዳት ደርሶ እንደሆነ ቀላል እሥራቱና መቀጮው በሕግ እስከተወሰነው ከፍተኛ ቅጣት ሊደርስ ይችላል አንቀጽ ህገወጥ የሥራ ማቆም አድማ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ሕግን ወይም ሙያውን በሚቃረን ሁኔታ በፈቃዱ የሥራ ማቆም አድማ ያደረገ እንደሆነ ወይም የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ሌሎችን የገፋፋ እንደሆነ በአንቀጽ የተመለከተው ቅጣት ይፈጸምበታል አንቀጽ የሰውን ንብረት የመበርበር ወይም የመያዝ ሥልጣንን ያለአግባብ መገልገል ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በሕግ ስልጣን ሳይኖረው የሰውን ንብረት የበረበረ የያዘ ወይም ንብረቱን የወሰደ እንደሆነ ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ቺ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ለመበርበር ወይም ለመያዝ በሕግ ሥልጣን የተሰጠው ቢሆንም ተገቢ ከሆነው ኃይል በላይ ተጠቅሞ ወደሌላ ሰው ቤት ወይም ግቢ የገባ እንደሆነ ወይም በሕግ ከታዘዘው ወይም ከተፈቀደው ሥርዓት ውጭ የሰውን ንብረት የበረበረ የያዘ ወይም የወሰደ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ሕገወጥ በሆነ መንገድ ሰውን መያዝ ወይም ማሰር ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በሕግ ከተመለከተው ውጭ ወይም ሕጋዊ ሥርዓትና ጥንቃቄ ሳይከተል ሌላውን ሰው በመያዝ በማሠር ወይም በማናቸውም ሌላ አኳኋን ነፃነቱን ያሳጣው እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ በማይገባ የአሠራር ዘዴ መጠቀም ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የመያዝ የመጠበቅ የመቆጣጠር የማጀብ ወይም የመመርመር ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ የተጠረጠረን የተያዘን በምስክርነት የቀረበን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ የተጠራን ተይዞ በማረፊያ ቤት ወይም በአሥር ቤት የተቀመጠን ወይም የእሥራት ቅጣት በመፈጸም ላይ የሚገኝን ሰው አንድ መግለጫ እንዲሰጠውም ሆነ ጥፋቱን አንዲያምን ወይም ይህን የመሳሰለ ነገር እንዲገልጽለት ወይም በፈለገው መንገድ የምስክርነት ቃል እንዲሰጥ የደለለው የተስፋ ቃል የሰጠው ያስፈራራው ወይም በዚህ ሰው ላይ አግባብነት የሌለው ወይም ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ የሆነ ወይም ለሰው ልጅ ክብር ወይም ለተሰጠው የሥራ ሥልጣን ተቃራኒ የሆነ ድርጊት የፈጸመበት እንደሆነ በተለይም ድብደባ የጭካኔ ተግባር ወይም የአካል ወይም የመንፈስ ስቃይ ያደረሰበት እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ድርጊቱ ተጨማሪ ወንጀል ባስከተለ ጊዜ አግባብነት ያለው ድንጋጌ በተደራቢነት እንዳይፈፀም የዚህ አንቀጽ ድንጋጌ አያግድም ቺ ወንጀሉ የተፈጸመው በባለሥልጣን ትዕዛዝ እንደሆነ ይኸው ባለሥልጣን ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ እሥረኛን ህገወጥ በሆነ መንገድ መፍታትና እንዲያመልጥ መርዳት ጳ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ሀ ሕግን ወይም የተሰጠውን ትዕዛዝ ተቃራኒ በሆነ መንገድ በሕግ አግባብ የታሰረውን ወይም የተያዘውንና እንዲጠብቀው የተሰጠውን ሰው የፈታ እንደሆነ ወይም ለ የዚሁ ዓይነት ሰው እንዲያመልጥ ያደረገ የፈቀደ ወይም እንዲያመልጥ የረዳው እንደሆነ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራትና ከብር ሶስት ሺህ በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ሕገወጥ አፈታቱ ወይም ማምለጡ የተፈጸመበት ዘዴ ወይም ሁኔታ ያደረሰው ጉዳት እንዲያዝ የታዘዘበት ምክንያት ክብደት ወይም የተያዘው ሰው አደገኛነት ሲታይ ሁኔታው በተለይ ከባድ እንደሆነ ቅጣቱ እስከ መደበኛው ከፍተኛ ጣራ ለመድረስ የሚችል መቀጮ እና ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል ወንጀሉ በቸልተኛነት የተፈጸመ ሲሆን ቅጣቱ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ብር የማይበልጥ መቀጮ እና ከአንድ ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል የወንጀል ሕግ አንቀጽ የጦር ምርኮኞችንና የወታደር ግዞተኞችን መፍታትና እንዲያመልጡ መርዳት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በጥበቃው ሥር ያሉትን የጦር ምርኮኞች ወይም ቺ የወታደር ግዞተኞች ሕግን ወይም ትዕዛዝን በመቃረን የፈታ ወይም እንዲያመልጡ የረዳ እንደሆነ ከአስራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው በቸልተኛነት ከሆነ ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ያስቀጣል ምዕራፍ ሦስት ሌሎች ሰዎች በመንግሥት ሥራ ላይ የሚፈፅሟቸው ወንጀሎች ክፍል አንድ ሌሎች ሰዎች ከመንግሥት ሥራ ጋር በተያያዘ መንገድ የሚፈጽሟቸው የሙስና ወንጀሎች ጉቦ መስጠት አንቀጽ ሦ ። ሎሦጅቕ በዚህ አንቀጽ ከተቀመጠው ቅጣት በተጨማሪ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛው ከመንግሥት ጋር ማናቸውንም ዓይነት ውል ወይም ግብይት በዘላቂነት ወይም ለተወሰነ ጊዜ እንዳይፈጽም የሚከለክል ትዕዝዝ ሊሰጥ ይችላል አንቀጽ ዋጋ ያለውን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ መስጠት ማንኛውም ሰው በአንቀጽ በተመለከቱት ሁኔታዎች ለማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ ወይም ከእርሱ ጋር ግንኙነት ላለው ማንኛውም ሌላ ሰው ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማናቸውንም ዋጋ ያለው ነገር ያቀረበ የሰጠ ወይም ለመስጠት የተስማማ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ህሀ ማቀባበል ማንኛውም ሰው ለራሱ ማናቸውንም አይነት ጥቅም ባያገኝም እንኳ የመንግስት ስራን ለሚያከናውን ሰው ጉቦ ለመስጠት ገንዘብ ዋጋ ያለው ነገር አገልግሎት ወይም ሌላ አይነት ጥቅም ከሌላ ሰው የተቀበለ እንደሆነ ወይም የራሱን የባንክ ሂሳብ እንደዚህ አይነት ጉቦ ለማቀባበል ያዋለ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ወ በሌለው ስልጣን መጠቀም ማንም ሰው ሀ ከመንግስት ስራው ከታገደ ከተዛወረ ከተሻረ ከተወገደ ወይም ሥልጣኑን ወይም ኃላፊነቱን ከተወ በኋላ በስራው ላይ ያለ በማስመሰል ለ ለወደፊቱ የመንግስት ሠራተኛ እሆናለሁ ብሎ በማመን ወይም ሐ የመንግሥት ሠራተኛ ሳይሆን መስሎ በመቅረብ ይህንን አደርጋለሁ በማለት የተስፋ ቃል በመግባት ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ወይም ስጦታ ከሌላ ሰው ላይ የጠየቀ ወይም የተቀበለ እንደሆነ የወንጀል ሕግ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ወፅ በግል ተሰሚነት መነገድ ማንም ሰው የመንግሥት ሠራተኛ ባለመሆኑ ለመንግሥት ሠራተኛ የተደነገገው አንቀጽ የማይመለከተው ቢሆንም ያለውን ወይም እንዳለው ያስመሰለውን ተሰሚነት በመጠቀም በአንድ የመንግሥት ሠራተኛ ብቻ ሊሰጥ የሚችለውን ልዩ መብት ወይም ጥቅም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ሲል ከሌላው ሰው ገንዘብ ስጦታ እጅ መንሻ ወይም ሌላ ጥቅም የጠየቀ የተቀበለ ወይም እነዚህን በተመለከተ የተስፋ ቃል የተቀበለ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ከሁለት ሺህ ብር በማያንስ መቀጮ ይቀጣል ክፍል ሁለት ሌሎች ሰዎች በመንግሥት ሥራ ላይ የሚፈፅሟቸው ወንጀሎች አንቀጽ ቋ መንግሥታዊ የሆኑ ማስታወቂያዎችንና ሕጐችን መድፈር ማንም ሰው ሥልጣን ወይም መብት ሳይኖረው አስቦ ባለሥልጣኖች በአደባባይ የለጠፏቸውን ማስታወቂያዎች ሕጐች ወይም ውሣኔዎች ከሥፍራቸው ያነሳ ያበላሸ የቀደደ ወይም እንዳይነበቡ ያደረጋቸው እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከብር አንድ ሺህ በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ያለፈቃድ ወይም ከተሰጠው ፈቃድ ውጭ መሥራት ማንኛውም ሰው በሕግ ወይም በደንብ መሠረት ፈቃድ ሊሰጥበት የሚገባውን ማናቸውም ሥራ ያለፈቃድ ወይም ከተሰጠው ፈቃድ ውጭ የሰራ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ወይም እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እስራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ቋ የማስመዝገብ ግዴታን የሚመለከቱ ድንጋጌዎችን መጣስ ማንም ሰው በመንግሥት መዛግብት ውስጥ መመዝገብ ያለባቸውን ጋብቻ ሞት ንብረት የንግድ ወይም ሌሎች ሥራዎች ወይም የግለሰቦችን የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የኩባንያዎችን መቋቋም ወይም አሠራር ወይም ተመሳሳይ ድርጊቶችን የሚመለከቱ ፍሬነገሮችን ወይም ማረጋገጫዎችን በተወሰነው ጊዜ ውስጥ ለሚመለከታቸው ባለሥልጣኖች ሳያስታውቅ የቀረ ወይም እነዚህኑ በሀሰት ያስመዘገበ እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከሦስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ቺ የዚህ ዓይነቱ አለማስታወቅ ወይም በሐሰት የማስመዝገቡ ሥራ ተደጋግሞ የተፈጸመ ወይም አንደልማድ ሆኖ የተያዘ እንደሆነ ወይም የሚመለከተው ባለሥልጣን በተለይ የሰጠውን ሕጋዊ ትዕዛዝ ወይም መጥሪያ በመቃወም እንደሆነ ቅጣቱ ከስድስት ወር ያልበለጠ ቀላል እሥራት ወይም ከብር ሁለት ሺህ ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል ሟ ልጅ መውለድን ስለ አለማስታወቅ የሚመለከተው ድንጋጌ እንደተጠበቀ ነው አንቀጽ አንቀጽ ጣጽ እንዳይገለፁ የተከለከሉ መንግሥታዊ ውይይቶችን ወይም ሰነዶችን መግለፅ ማንም ሰው መብት ሳይኖረው ወይም በግልጽ ሳይፈቀድለት በሕጉ መሠረት ወይም ከሚመለከተው መንግሥታዊ ባለሥልጣን በተሰጠው ግልጽ ውሣኔ መሠረት ምስጢር ሆኖ ሊጠበቅ የሚገባውን ሰነድ ሪፖርት መመሪያ ቃለ ጉባኤ ወይም ውሣኔ በሙሉ ወይም በከፊል ለመገናኛ ብዙሃን የገለፀ እንደሆነ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ጣ ሕገወጥ በሆነ መንገድ መብትን ማስከበር ማንም ሰው መብት ሳይኖረው ወይም ሕግን ተቃራኒ በሆነ መንገድ ሀ በመያዣ ወይም በዋስትና ያስረከበውን ዕቃ ተረካቢው ሳይፈቅድለት ወይም በዚሁ ፅቃ ምክንያት ክስ ቀርቦ በክርክር ላይ እያለ የወሰደ እንደሆነ ለ ሊከፈለው የሚገባውን ክፍያ ለማግኘት ሲል የባለዕዳው ንብረት የሆነውን ማናቸውንም ተንቀሳቃሽ ዕቃ የወሰደበት እንደሆነ ወይም ሐ በጠቅላላው የሌለውን ወይም በሕጉ መሠረት ሊሰራበት የማይችለውን መብት የተጠቀመበት እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ፀወዷ ሥልጣንን በማይገባ መያዝ ማንም ሰው ህገወጥ ለሆነ ዓላማ ወይም ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ያንድ ባለሥልጣን ወይም ኮሚሽን ሥልጣንን መለያ ምልክትን ማዕረግን ወይም ኦፊሴላዊ የሆኑ ማናቸውንም ትዕዛዞችን የመስጠት ሥልጣንን የራሱ በማድረግ የተገለገለበት እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ወንጀሉ የተፈጸመው ሌላውን ሰው ለመበደል ወይም ጉዳት እንዲደርስበት ለማድረግ እንደሆነ ቅጣቱ ቀላል እሥራት ወይም መቀጮ ይሆናል አንቀጽ የመንግሥት ሥራን ማሰናከልና የመተባበር ግዴታን መጣስ ማንም ሰው ከመንግሥት ሥራ ጋር በተያያዘ ሁኔታ በሕግ በተፈቀደው ወይም ከፍርድ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት በመንግሥት ሠራተኛ ሲጠየቅ ቀርቦ ለማስረዳት ተገቢውን መልስ ለመስጠት ሰነዶችን ለማቅረብ ወይም ለማስመርመር ወይም ልዩ ልዩ ቤቶችን ቦታዎችን ወይም ነገሮችን ለማስፈተሽ እምቢተኛ ከሆነ በጠቅላላው ለምርመራ ያልተባበረ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ የመንግሥትን ሥራ ያደናቀፈ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ቋሀ እሽጐችን መቅደድ መስበርና ዕቃዎችን መውሰድ ማንም ሰው ሕጋዊ ሥልጣን ሳይኖረው አስቦ ሀ አንድን ፅዕቃ ሁፍ ወይም ሰነድ ለመጠበቅ ለማስቀመጥ ለመለየት ወይም ለመሸፈን ወይም ወደማናቸውም ሥፍራ መግባትን ለመከልከል የተደረገውን ኦፊሴላዊ ማህተምሃ ምልክት ወይም መለያ ያነሳ ያበላሸ ወይም የሰበረ ወይም በማናቸውም መንገድ እንደነዚህ ዓይነቱ ማህተም ምልክት ወይም መለያ ውጤት እንዳያገኝ ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ የተያዘ የተወረሰ ወይም በማናቸውም ምክንያት በአንድ ባለሥልጣን ወይም በሌላ ሰው በጥንቃቄ እንዲያዝ ወይም እንዲጠበቅ የተሰጠ ዕቃን ጽሁፍን ወይም ሰነድን የሰረቀ ለግል ጥቅሙ ያዋለ ያበላሸ ወይም ያጠፋ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ወይም ከአሥር ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ዌ መቃወምና አለመታዘዝ ሙ ማንም ሰው በቂ ምክንያት ሳይኖረው ሀ ኦፊሴላዊ የሆነ የሥራ ግዴታውን የሚፈጽመውን የመንግሥት ሠራተኛ ሥራውን እንዳይፈጽም የተቃወመ እንደሆነ ለ ሕገወጥ ከሆነ ስብሰባ እንዲበተን ወይም ከአንድ ከተከለከለ ሥፍራ እንዲለቅ ወይም በቃጠሉ በማዕበል ወይም ይህን በመሰለ ሌላ ክስተት ምክንያት በሕዝብ ላይ አደጋ እንዳይደርስ ለመከላከል በሚወሰድ እርምጃ እንዲካፈል ሥራውን የወንጀል ሕግ በማከናወን ላይ የሚገኝ የመንግሥት ሠራተኛ ሲጠይቀው አልታዘዝም ያለ እንደሆነ ወይም ሐ በሚመለከተው ባለሥልጣን በሕጉ አግባብ በተሰጠ ውሣኔ መሠረት ካልፈጸመ በዚህ አንቀጽ የተደነገገው ቅጣት እንደሚወሰንበት ተገቢ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል መቃወሙ ወይም አለመታዘዙ ኃይልን ዛቻን የኃይል ሥራን ወይም የእጅ እልፊትን አስከትሉ እንደሆነ በአንቀጽ ማ የተመለከተው ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል። ወንጀሉን የፈጸመው በአፍቅሮ ንዋይ ወይም ቁሣዊ ጥቅም ለማግኘት እንደሆነ መቀጮው እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር ሊደርስ ይችላል ወንጀሉ የተፈጸመው የሞት ቅጣት ወይም የእድሜ ልክ ጽኑ እሥራት በሚያስቀጣ ወንጀል በተከሠሠ ሰው ላይ ጉዳት በሚያስከትል ሁኔታ እንደሆነ ቅጣቱ ከአሥር ዓመት የማይበልጥ ኑ እሥራት ይሆናል ሟ በንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ወንጀል የተፈፀመው በቸልተኛነት እንደሆነ ከሦስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ያስቀጣል ምዕራፍ ሦስት በወንጀል ፍርድ አፈፃፀም ሳይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ ተጨማሪ ቅጣቶችን የመከላከልና የመጠበቅ የጥንቃቄ እርምጃዎችን አለማክበር ማንም ሰው ከመብት የመሻር ተጨማሪ ቅጣት አንቀጽ ወይም የጥንቃቄ እርምጃ ከአንቀጽ ያጣሣ ከተወሰነበት በኋላ እያወቀ በሕግ አግባብ የተወሰነበትን ክልከላ ወይም ግዴታ የጣሰ እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከአንድ መቶ ሃይበልጥ ቀላል በሌላ አንቀጽ ከፍተኛ ቅጣት የሚቀጣ ካልሆነ በስተቀር አንቀጽ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ጥፋቱ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአንድ ወር በ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የቅጣትና የጥንቃቄ እርምጃዎችን ማሰናከል ማንም ሰው በአንድ ወንጀለኛ ላይ በፍርድ ቤት የተወሰነውን ቅጣት ወይም የጥንቃቄ እርምጃ በማናቸውም አኳኋን እንዳይፈጸምበት ያደረገ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ የእሥረኛ ማምለጥ ማንም ሰው በሕግ አግባብ ተይዞ ወይም ታስሮ ካለበት ቦታ ያመለጠ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ወንጀሉ የተፈፀመው በሰዎች ላይ ዛቻ ወይም የኃይል ተግባር በመፈፀም ወይም በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ያስቀጣል ጥፋተኛው በመጀመሪያው ወንጀል የተፈረደበት ወይም የሚፈረድበት ሲሆን ስለወንጀሎች መደራረብ ወይም ስለደጋጋሚነት የተመለከቱት ድንጋጌዎች እንደአግባብነቱ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ እሥረኛ እንዲያመልጥ ማመቻቸትና መርዳት ማንም ሰው የመንግሥት ሠራተኛ ሳይሆን አንቀጽ በሕግ አግባብ የተያዘ ወይም የታሰረ ሰው እንዲያመልጥ በኃይል ድርጊት በማስገደድ በዛቻ በተንኩል በግል ተሰሚነቱ ያለአግባብ በመገልገል ወይም በማናቸውም ሌላ ዘዴ መንገድ ያመቻቸ ወይም የረዳ እንደሆነ በቀላል እሥራት ይቀጣል ቅጣቱ ከሦስት ወር የማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ ከሰባት ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እሥራት የሚሆነው ሀ ማምለጡ የተፈፀመው የተሞከረው ወይም የተመቻቸው በቡድን የኅብረት ሥራ በጦር መሣሪያ ወይም በማናቸውም ሌላ መሣሪያ እንደሆነ ወይም ለ እንዲያመልጥ እርዳታ የተደረገለት ሰው ሲቪል ወይም የመከላከያ ሠራዊት አባል ቢሆንም ቢያንስ የሃያ ዓመት ፅኑ እሥራት የተፈረደበት ወንጀለኛ እንደሆነ ነው የወንጀል ሕግ ወንጀለኛው ዕቅዱን ለማሣካት ሁከት አንስቶ በሰው ወይም በንብረት ላይ የኃይል ድርጊት ፈፅሞ ወይም ሠራተኛን ወይም ጠባቂን ደልሎ ወይም ማናቸውንም ሌላ ተደራቢ ወንጀል ፈፅሞ እንደሆነ የተደራረቡ ወንጀሎች በተፈፀሙ ጊዜ ቅጣትን ስለማክበድ የተደነገጉት ድንጋጌዎች ተፈፃሚዎች ይሆናሉ አንቀጽ ጃ እና ጂ አንቀጽ የጦር ምርኮኞችና ወታደራዊ ግዞተኞች ማምለጥና እንዲያመልጡ መርዳት የአንቀጽ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይ በተዘጋጀ የወታደር ግዞት ቦታ ወይም ሠፈር ውስጥ የሚገኙ የጦር ምርኮኞችን ወይም የወታደር ግዞተኞችን በሚመለከት በፍርድ ውሳኔ በወንጀል ቅጣት የተያዙ ባይሆኑም እንኳ ከዚህ በላይ በአንቀጽ እና የተመለከቱት ድንጋጌዎች በተመሳሳይ ሁኔታ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ የእስረኞች አመፅ ፅ ማንም ሰው በሕግ አግባብ ተይዞ እንዲቆይ በተደረገበት ጊዜ ሀ የእስር ቤቱን አስተዳዳሪ ባለሥልጣን ጠባቂ ወይም የእስር ቤቱን አስተዳደር ወይም ቁጥጥር ለማካሄድ ኃላፊነት የተሰጠውን ማንኛውንም ሰው በኃይል ድርጊት ወይም በዛቻ የሥራ ግዴታውን እንዳያከናውን ወይም የሥራ ግዴታውን የሚቃረን ድርጊት እንዲፈጽም ለማስገደድ ለ ከነዚሁ ሰዎች መካከል የሥራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንዱ ላይ አደጋ ለመጣል ወይም ሐ በሰዎች ወይም በንብረት ላይ የኃይል ድርጊት በመፈጸም ለማምለጥ በማሰብ በአመጽ ወይም በሁከት ተካፋይ እንደሆነ ሊወሰንበት ከሚገባው ወይም ተወስኖበት በመፈፀም ላይ ካለው ቅጣት ጋር ተደራቢ በሚሆን ከሦስት ወር እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ ቀላል እሥራት ይቀጣል ቺ አመፁን ያዘጋጀው ወይም የመራው ሰው ሀ የማስገደድ ወይም የኃይል ድርጊት ባልተፈጸመ ጊዜ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ለ የማስገደድ ወይም የኃይል ድርጊት ተፈጽሞ እንደሆነ ከዚህ የበለጠ ቅጣት የሚያስከትሉ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ከአስር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል በሰዎች ወይም በንብረት ላይ ጉዳት ደርሶ እንደሆነ ስለወንጀሎች መደራረብ የተደነገጉት የማክበጃ ጠቅላላ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ አንቀጽ ቿ የወንጀል ሕግ አንቀጽ ፀ አካባቢያዊ ክልከላን መጣስ ማንም ሰው በአንድ ቦታ ወይም አካባቢ ተወስኖ እንዲኖር ወይም በአንድ በተወሰነ ቦታ ከመኖር ወይም ውሎ ከማደር የመከልከል ወይም ከአገር የመውጣት ፍርድ ተወስኖበት ሳለ ከአቅሙ በላይ የሆነ ምክንያት ሳይኖረው ይህን ውሳኔ የጣሰ እንደሆነ አስፈላጊ ሲሆን ተወስኖበት የጣሰውን የጥንቃቄ እርምጃ ከፍ ለማድረግ መቻሉ እንደተጠ በቀ ሆኖ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል የቅጣቱ ውሳኔ የሚቆይበት ጊዜ የግል ነፃነትን ከሚቀንሱ የጥንቃቄ እርምጃዎች ጋር አይታሰብም ርዕስ አምስት በሕዝባዊ ምርጫዎችና በድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ ለምርጫ የሚደረግ ስብሰባንና የምርጫ ሂደትን ማወክና ማሰናከል ሙ ማንም ሰው በሕግ የተፈቀደ ከምርጫ ጋር የተገናኘ ሕዝባዊ ስብሰባን ወይም በሚመለከታቸው ባለሥልጣኖች ቁጥጥር በአግባቡ የሚደረግ የድምፅ አሰጣጥን ወይም ምርጫን አግባብ በሌለው በማናቸውም መንገድ ያወከ የከለከለ ያደናቀፈ ወይም እንዲቋረጥ ያደረገ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራትና ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ቺ በሰዎች ወይም በንብረት ላይ የኃይል ድርጊት ተፈጽሞ እንደሆነ ወይም የአምባጓሮ ወይም የሁከት ጠባይ ያለው ረብሻ ተነስቶ እንደሆነ አግባብ ያላቸው ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ የምርጫ ድምፅ የመስጠትን ወይም የመመረጥን መብት መንካት ነጅ ማንም ሰው በዛቻ በማስገደድ በሥልጣኑ ያለአግባብ በመጠቀም ወይም በኃይል ድርጊት በማጭበርበር በተለይም ስምን በመለዋወጥ ማስታወቂያን ወይም መጥሪያን በመደበቅ ወይም በማስቀረት ወይም በማናቸውም ሌላ ብልሀት ወይም ዘዴ ሀ ሌላ ሰው በመምረጥ ወይም በመመረጥ መብቱ እንዳይጠቀምበት የከለከለ እንደሆነ ወይም ለ ይህን በመሰለ ዘዴ ሌላ ሰው መብቱን በአንድ በተወሰነ መንገድ እንዲጠቀምበት ወይም በዚሁ መብቱ ሳይጠቀምበት ለመቅረት ግዴታ እንዲገባ ያደረገ ወይም ያግባባ እንደሆነ የወንጀል ሕግ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ማንም ሰው እንደፍላጎቱ ለመጠቀም በተሰጠው መብት መሠረት የመምረጥ መብቱን በአንድ በተወሰነ መንገድ በተጠቀመበት ወይም ሳይጠቀምበት በቀረው ሰው ላይ በደል ወይም ጉዳት ያደረሰበት እንደሆነ ከዚህ በላይ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል አንቀጽ በምርጫ ላይ የሚሰጥ መደለያ ማንም ሰው የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት ያለውን ሌላውን ሰው በመብቱ በተወሰነ መንገድ እንዲጠቀም ወይም መብቱን እንዲተው ለማድረግ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ ገንዘብ ወይም ማናቸውንም ሌላ ዓይነት ጥቅም የሰጠ ወይም ለመስጠት ቃል የገባ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ቺ የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት ያለው ማንም ሰው በዚሁ መብቱ እንዲጠ ቀምበት ወይም በአንድ በተወሰነ መንገድ እንዲጠቀምበት ወይም ሳይጠቀምበት እንዲቀር ገንዘብ ወይም ማናቸውንም ሌላ ዓይነት ጥቅም የተቀበለ ወይም ለመቀበል የተስማማ እንደሆነ ከዚህ በላይ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል። ማንም ሰው በሕዝብ ጎዳና ወይም በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታ ላይ በሕግ በተከለከለ ማናቸውም ስብሰባ ላይ በፈቃዱ የተካፈለ እንደሆነ ከሁለት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል የወንጀሉ መሪ አዘጋጅ ወይም አዛዥ የሚቀጣው ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ነው መሣሪያ በያዙ ሰዎች በተደረገ ሕገወጥ ስብሰባ አስቦ ተካፋይ የሆነ ማንም ሰው ከሦስት ወር እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እሥራት ይቀጣል ከላይ በንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ሁኔታ ወንጀሉ ሲፈፀም የወንጀሉ መሪ አዘጋጅ ወይም አዛዥ የሆነ ወይም መሳሪያ የያዘ ሰው ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እሥራት ይቀጣል የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በሕግ የተከለከለ ስብሰባን ያደራጀ ወይም የመራ እንደሆነ ከአሥር ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ በወሬ ሕዝብን ማሸበር ፅ ማንም ሰው ሀ ለሕዝብ ደህንነት ወይም ለግለሰቦች ሕይወት ጤና ወይም ንብረት አስጊ የሆነ አደጋ በተለይም የወረራ የሰው ግድያ የእሳት ቃጠሉ የጥፋት ወይም የዘረፋ አደጋ እንደሚደርስ በማስፈራራት ወይም ለ ስለነዚሁ ሁኔታዎች ወይም በአጠቃላይ ስለሚደርስ ሁከት ወይም በቅርብ ስለሚደርስ ጥፋት ወይም የተፈጥሮ አደጋ የሀሰት ወሬ በመንዛት አስቦ ሕዝብን ያሸበረ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ከፍተኛ ቅጣቶችን የሚወስኑ አግባብ ያላቸው ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ሁኔታዎቹ በጣም ከባድ የሆነ ብጥብጥን ወይም ምስቅልቅልን ሊያመጡ የሚችሉ ወይም ያመጡ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል አንቀጽ የሐሰት ወሬዎችን በማውራት ሕዝብን ማነሳሳት ማንም ሰው በአገር ደህንነት ላይ ከሚፈጸሙት ወንጀሎች ውጭ በሆነ አኳኋን አንቀጽ ሣ ፃሠ እና ሀ በመንግሥት በሕዝብ ባለሥልጣኖች ወይም በሥራቸው ላይ የሐሰት ወሬዎችን ጥርጣሬዎችን ወይም የሐሰት ሐሜታዎችን የሚፈጥር ወይም የሚነዛ ሰው ከዚህም የተነሳ የሕዝብን አስተሳሰብ ያናወጠ የቀሰቀሰ ወይም ለማናወጥ የሚችል እንደሆነ ወይም ለ በማናቸውም ዓይነት ማሳጣት ወይም ሌላ ዘዴ ጥርጣሬን ያስፋፋጥላቻን ያነሳሳ ወይም የኃይል ድርጊት ወይም የፖለቲካ የዘር ወይም የኃይማኖት ሁከት የቀሰቀሰ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮወይም ወንጀሉ ከባድ በሆነ ጊዜ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የማነሳሳት ጠባይ ያላቸው የሐሳብ መግለጫዎች ማንም ሰው ሀ በማናቸውም የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታ ወይም ስብሰባ ላይ ሕገወጥ ለሆነ ድርጊት የሚያነሳሳ ወይም የዛቻ ጠባይ ያለው ንግግር መግለጫ ወይም ምስል ያዘጋጀ ያስፋፋ ያሰራጨ ወይም ያሰማ እንደሆነ ወይም የወንጀል ሕግ ለ አግባብ ባለው ባለሥልጣን በሕግ የተሰጡ ትዕዛዞችን ወይም የወጡ ሕጎችን እና ደንቦችን ሕዝብ እንዲቃወም ለማድረግ በግልጽ ያነሳሳ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ረብሻ ሙ ቺ ሟ ማንም ሰው በሰው ወይም በንብረት ላይ የኀብረት የኃይል ድርጊት በተፈጸመበት ሕገወጥ ስብሰባ በገዛ ፈቃዱ ተካፋይ እንደሆነ ከአንድ ወር በማያንስ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል የወንጀሉ አደራጅ አነሳሸ ወይም መሪ ከስድስት ወር በማያንስ ቀላል እሥራትና በመቀጮ ወንጀሉ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል በሰው ወይም በንብረት ላይ በግሉ የኃይል ድርጊት የፈጸመ ማንም ሰው የፈጸመው ወንጀል በተለየ የሕግ ድንጋጌ ከፍ ያለ ቅጣት የሚያስቀጣ ካልሆነ በቀር ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ አንቀጽ ፅ ልዩ አስተያየት የሚደረግላቸው ጉዳዮች የኃይል ድርጊት ሳይፈጽሙ ወይም እንዲፈጸም ሳያነሳሱ ከተከለከለ ስብሰባ የማነሳሳት ጠባይ ካለው የሃሳብ መግለጫ ሰልፍ ሕገ ወጥ ከሆነ ጉባኤ ወይም ከሕብረት ዛቻ በገዛ ፈቃዳቸው ወይም በባለሥልጣን ትዕዛዝ ወጥተው የሄዱ ተካፋዮች አስፈላጊ ሲሆን ተወቅሰው ወይም ተገስጸው አንቀጽ ከሌላ ቅጣት ነፃ እንዲሆኑ ለመወሰን ይቻላል ምዕራፍ ሁለት በሕዝብ ሰላምና ተረጋግቶ መኖር ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ስብሰባን ወይም ጉባኤን ማወክ ማንም ሰው በሕግ የተፈቀደውን ማናቸውንም ስብሰባ ወይም ጉባኤ በቃል በዛቻ በኃይል ድርጊት በጉልበት ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ሕግን በመቃረን የወረረ ያወከ የከለከለ ወይም የበታተነ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ወንጀሉ የሚመለከተው የባለሥልጣን ኦፊሴላዊ የሆነ የቦርድ ወይም የኮሚሽን ወይም ኦፊሴላዊ የሆነ የምርጫ የሐራጅ ሽያጭ ወይም ሕጋዊ የሆነ ማናቸውንም የሕዝብ ሥራ ለማከናወን የተደረገ ስብሰባን ወይም ጉባኤን እንደሆነ ስብሰባው ወይም የወንጀል ሕግ ጉባኤው የፖለቲካ የአስተዳደር የሕግ አስፈጻሚነት ወይም የዳኝነት ጠባይ ያለው ቢሆንም ቅጣቱ ከሦስት ወር የማያንስ ቀላል እሥራትና ከአምስት መቶ ብር የማያንስ መቀጮ ይሆናል ሟ ጥፋቱ የተፈፀመው በቡድን ወይም የጦር መሣሪያ ወይም ሌላ መሣሪያ በመያዝ እንደሆነ ቅጣቱ ከሰባት ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል አንቀጽ በራስ ጥፋት ከኃላፊነት ውጭ በመሆን የሚፈጸም የሁከት ተግባር በራሱ ጥፋት በመስከር ወይም በሌላ ሁኔታ ወደ ፍፁም ኢኃላፊነት ራሱን ያስገባ ሰው ቢያንስ የአንድ ዓመት እሥራት የሚያስቀጣ ወንጀል የፈፀመ እንደሆነ እንደተፈፀመው ተግባር ከባድነትና እንደ አደገኛነቱ ማደግ ወይም ማነስ በመቀጮ ወይም ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የኃይማኖትን ሰላምና ስሜት መንካት ማንም ሰው አስቦ በአደባባይ ሀ የተፈቀደውን ኃይማኖታዊ ሥርዓት ሥነ በዓል ወይም ኃይማኖታዊ ተግባር እንዳይፈጸም የከለከለ ያወከ ወይም ያስተሐቀረ እንደሆነ ወይም ለ ለሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት የሚያገለግለውን ቦታ ሥዕል ወይም ዕቃ ያረከሰ እንደሆነ ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የሙታንን ሰላምና ክብር መንካት ማንም ሰው ሀ የሬሳን አጀብ ወይም የቀብር ሥነ ሥርዓት ያወከ ወይም ያረከሰ እንደሆነ ለ የሞተ ሰው ያረፈበትን ቦታ የደፈረ ያረከሰ የመቃብሩን ሐውልት ወይም ምልክት ያፈረሰ ወይም ያረከሰ ወይም የተቀበረውንም ሆነ ያልተቀበረውን አስከሬን ያረከሰ ወይም አካሉን የቆረጠ እንደሆነ ጠ አስከሬንን በአደባባይ ያዋረደ ወይም የመታ እንደሆነ ወይም መ ሬሳን ወይም ማናቸውንም የሬሳን አካል ክፍል ወይም ቅሪት የወሰደ እንዲጠፋ ያደረገ ወይም የበታተነ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል የወንጀል ሕግ ርዕስ ሰባት በሕዝብ በመገናኛዎችና በማጓጓዣዎች ደህንነት ሳይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ምዕራፍ አንድ በሕዝብ ፀጥታና ደህንነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ የእሳት ቃጠሎ ማድረስ ጳ ማንም ሰው በሰዎች ወይም በንብረት ላይ የጅምላ አደጋ ለማድረስ አስቦ የራሱን ወይም የሌላውን ሰው ሕንፃ ወይም ማናቸውም ዓይነት ግዙፍ ሥራን ሰብሎችን የግብርና ምርቶችን ደኖችን ዛፎችን ወይም ማናቸውንም ሌሎች ዕቃዎችን በእሳት የለኮሰ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ወንጀሉ ከፍ ያለ አደጋን ያስከተለ ወይም በሰዎች ወይም በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት የተስፋፋ እንደሆነ በተለይም የተጎዱት የሕዝብ ሕንፃዎች የሕዝብ አገልግሎት ሕንፃዎች ነዎሪዎች ያሉባቸው ወይም ለመኖሪያ የሚያገለግሉ ቤቶች የምግብ የሚቀጣጠል ነገር ወይም የፈንጂ መጋዘኖች ጫካዎች ማዕድኖች የነዳጅ ዘይት ጉድጓዶች ወይም የነዳጅ ማጣሪያዎች መርከቦች አውሮኘላኖች ወይም በተለይ ለአደጋ ምቹ የሆኑ ማናቸውም ሌሎች ዕቃዎች በሚሆነበት ጊዜ ቅጣቱ ከአሥራ አምስት ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል አንቀጽ የተፈጥሮ አደጋዎችን ማድረስ ማንም ሰው በሰዎች ወይም በንብረት ላይ አደጋ ለማድረስ አስቦ የውሃ ማጥለቅለቅ ወይም ማስጠም የመሬት መናድ የመፍረስ ወይም ይህን የመሳሰለ ማናቸውም ሌላ አደጋ እንዲደርስ ያደረገ እንደሆነ አንቀጽ ግዙፍ ሥራዎችን ወይም የመጠበቂያ ሥራዎችን መጉዳት ማንም ሰው በሰዎች ወይም በንብረት ላይ አደጋ ለማድረስ አስቦ ኤሌክትሪክን ወይም ውሃን የሚመለከቱ ህንፃዎችን ወይም የተፈጥሮ ኃይልን ለመከላከል የተሰሩ ስራዎችን በተለይም ቧንቧዎችን ቦዮችን ማጠራቀሚያዎችን የውሃ ማገጃዎችን መልቀቂያዎችን ወይም ማዕበል ማገጃዎችን ያበላሸ ወይም ያፈረሰ እንደሆነ ከዚህ በላይ በአንቀጽ በተደነገገው መሠረት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ማፈንዳት ማንም ሰው በሰዎች ወይም በንብረት ላይ አደጋ ለማድረስ አስቦ ነዳጅ ባሩድ ዲናሚት ወይም ይህንን የመሳሳለ ማናቸውንም ሌላ አደገኛ ነገር እንዲፈነዳ ያደረገ እንደሆነ ወንጀል በቸልተኛነት የፈጸመ እንደሆነ እንደወንጀሉ ከባድነት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ጥፋተኛው ሰዎችን ወይም ንብረትን ከባድ ለሆነ አደጋ አጋልጦ የተገኘ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ቀላል እሥራት መወሰን አለበት አንቀጽ ሀ በሚፈነዱ በሚቀጣጠሉ ወይም በሚመርዙ ነገሮች አደጋ ማድረስ ማንም ሰው በሕዝብ ደህንነት ላይ አደጋን ለማድረስ በማቀድ በሚፈነዱ ወይም በቀላሉ በሚቀጣጠሉ ነገሮች ወይም በሚመርዙ ጋዞች የሰውን ሕይወት ጤና ወይም አካል ወይም የሌላውን ሰው ንብረት እያወቀ ለአደጋ ያጋለጠ እንደሆነ ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ጥፋተኛው ለአደጋ ያጋለጠው ንብረትን ብቻ ሲሆንና ያደረሰውም ጉዳት ቀላል ሲሆን ቅጣቱ ከስድስት ወር የማያንስ ቀላል እሥራት ይሆናል ቺ ወንጀሉ ከአምስት ዓመት እስከ አስራ አምስት ዓመት በሚደርስ ኑ እሥራት የሚያስቀጣው ድርጊቱ በሰው ሕይወት ወይም አካል ላይ ጉዳት ለማድረስ ወይም በኢኮኖሚ ላይ ከባድ ጉዳት በሚያደርስ ወይም ሊያደርስ በሚችል ድርጊት በአደባባይ በሕዝብ መገልገያ ቦታ በመንግሥት ተቋም በአገልግሎት መስጫ ተቋም ወይም ሥርዓት ላይ ጉዳት ለማድረስ ታስቦ በተጠቀሱት ተቋማት አገልግሎቶች ወይም ሥርዓቶች ላይ የባዮሎጂካል ኤጀንቶችን መርዝነት ያላቸው ነገሮችን በማፍሰስ በመልቀቅ በማሰራጨት ወይም በሰው ሕይወት ወይም አካል ወይም በንብረት ላይ ጉዳት ለማድረስ ኃይል ያላቸውን ወይም ለዚሁ ተግባር የተሰሩ ተቀጣጣይና ፈንጂዎችን በማስቀመጥ በመወርወር በማፈንዳት የተፈጸመ በሆነ ጊዜ ይሆናል ሟ ማንም ሰው በሕዝብ ደህንነት ላይ አደጋን ለማድረስ በማቀድ ሳይሆን ከዚህ በላይ በተገለፀው ሁኔታ የሌላውን ሰው ሕይወት አካል ጤንነት ወይም ንብረት አስቦ ለአደጋ ያጋለጠ እንደሆነ በቀላል እሥራት ይቀጣል ። አስቸኳይ ወይም አስፈላጊ የሆነ ወይም በደግነት ወይም ለሙያ ስነ ምግባር ተገዥ በመሆን አልፎ አልፎ በነፃ የሚሰጥ ምክር እርዳታ ወይም አገልግሎት ወይም ይህን በመሳሰሉ ሁኔታዎች የተፈጥሮ ወይም የተለመዱ ፍቱንና አደጋ የማያስከትሉ መድሃኒቶችን በመስጠት የሚደረግ እርዳታ አያስቀጣም በሚኖሩበት አካባቢ በቂ ልምድ አላቸው በመባል የታወቁ ሰዎች በአካባቢው ልማድ መሠረት በሚያከናውኑት ሕክምና ነክ ሥራዎች ላይ ይህ ድንጋጌ ተፈጻሚነት የለውም ይህም የሚሆነው እነዚህ ሰዎች ሥራቸውን የሚያከናውኑት በሚኖሩበት አካባቢ ብቻ ሲሆንና ድርጊታቸውም የአካባቢውን ሕብረተሰብ አባላት ሕይወት አካል ወይም ጤንነት አደጋ ላይ የማይጥል ወይም የማይጎዳ እንደሆነ ነው አንቀጽ ቋ መርዛማና አደገኛ የሆኑ ነገሮችን ያለአግባብ ማቅረብ ማንኛውም ሐኪም መድሃኒት ቀማሚ ፋርማሲስት የጥርስ ሐኪም የእንስሳት ሐኪም አስታማሚ ወይም መርዛማ በሆኑ በናርኮቲክ ወይም በሳይኮትሮፒክ ነገሮች ወይም በጤና ላይ ከባድ ጉዳት ሊያስከትሉ በሚችሉ ሌሎች ነገሮች ሕክምና ለመስጠት ወይም እነዚህኑ ለማስቀመጥ ወይም ለመሸጥ የተፈቀደለት ማንኛውም ሌላ ሰው መደበኛ የሕክምና አሠራር ከሚፈቅዳቸው ሁዬታዎች ውጭና ልዩ ፈቃድ ሳይኖረው እነዚህኑ ነገሮች የሠራባቸው ለሕዝብ የሰጠ ወይም የሸጠ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማያንስ ቀላል እሥራትና በመቀጮ ወይም ጥፋቱ ከባድ እንደሆነ ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ጥፋተኛው ወንጀሉን የፈፀመው በአፍቅሮ ንዋይ እንደሆነ መቀጮው እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር ሊደርስ ይችላል አንቀጽ የሕክምና እርዳታን ያለምክንያት መከልከል ማንኛውም ሐኪም መድሃኒት ቀማሚ ፋርማሲስት የጥርስ ሃኪም የእንስሳት ሐኪም አዋላጅ አስታማሚ ወይም ማናቸውንም ሕክምና ለመስጠት ተግባሩ መሆኑ በሕግ የታወቀለት ማንኛውም ሌላ ሰው ተግባሩን በሚቃረን መንገድና በቂ ባልሆነ ምክንያት በምንቸገረኝነት በራስ ወዳድነት ገንዘብን አለመጠን በመፈለግ በጥላቻ በንቀት ወይም በማናቸውም ተመሳሳይ ምክንያት አስፈላጊ የሆነውንና በሞያ ተግባሩ ሊያደርገው የሚገባውን አገልግሎት ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ ቺ የወንጀል ሕግ በመቀጮ ወይም ወንጀሉ የተደጋገመ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንድ ሰው በሕይወቱ በአካሉ ወይም በጤናው ላይ ከባድ ጉዳት የሚደርስበት ሆኖ ሳለ እርዳታ ያላደረገ ማንም ሰው የሚቀጣበት የከፍተኛ ቅጣት ድንጋጌ አንቀጽ የወንጀል ሕግ አምስተኛ መጽሐፍ በሌሎች ሰዎችና በቤተዘመድ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ርዕስ አንድ በሰው ሕይወት አካልና ጤንነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ምዕራፍ አንድ በሰው ሕይወት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ክፍል አንድ የመግደል አደራረግና ዓይነቶች አንቀጽ ቋ መርህ ማንም ሰው አስቦ ወይም በቸልተኛነት በማናቸውም ዓይነት መሣሪያ ወይም ዘዴ ሌላውን ሰው የገደለ እንደሆነ ነፍሰ ገዳይ ነው አስቦ ወይም በቸልተኛነት ሰውን በመግደል ጥፋተኛ የሆነ ሰው ላይ የሚጣለው ቅጣት እንደአገዳደሉ ቀላልነትና ከባድነት ከዚህ በታች በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ይወሰናል አስቦ ወይም በቸልተኛነት የገደለ ሁሉ የሚቀጣው ሕጋውያን በሆኑ የፍርድ ሂደቶች እና በውሣኔዎቻቸው መሠረት ብቻ ይሆናል አንቀጽ ቋ ከባድ የሰው ግድያ ማንም ሰው ሀ ሰውን ለመግደል አስቀድሞ የነበረው አሳብ ወይም ምክንያት ለመግደል የተጠ ቀመበት መሣሪያ ወይም ዘዴ ያገዳደሉ ሁኔታ ወይም ግድያው የተፈፀመበት ቅጣትን የሚያከብድ ጠቅላላ ምክንያት አንቀጽሽቹ ወይም ሌላ ምክንያት አንቀጽ ቭ ሲታይ ገዳዩ በተለይ ጨካኝ ነውረኛ ወይም አደገኛ መሆኑን በሚገልጽ ሁኔታ ወይም ለ ሰውን ለመግደል ወይም የውንብድና ወንጀልን ለመፈጸም የተደራጀ የወንበዴ ቡድን አባል በመሆን ወይም ሐ ሌላ ወንጀልን ለመፈጸም እንዲመቸው ወይም የተፈጸመ ወንጀል እንዳይገለጽ ለማድረግ ሲል አስቦ ሰውን የገደለ እንደሆነ በእድሜ ልክ ፅኑ እሥራት ወይም በሞት ይቀጣል የወንጀል ሕግ ወንጀለኛው የዕድሜ ልክ ፅኑ እሥራት ተፈርዶበት ቅጣቱን በመፈፀም ላይ ሳለ ከዚህ በላይ በንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ሁኔታ ሰውን የገደለ እንደሆነ በሞት ይቀጣል አንቀጽ ሣ ተራ የሆነ የሰው ግድያ ማንም ሰው አገዳደሉ በአንቀጽ ቋ የተመለከተውን ያህል ከባድ ወይም በአንቀጽ ማ የተመለከተውን ያህል ቀሳል ባልሆነ ሁኔታ አስቦ ሌላ ሰውን የገደለ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ ዓመት በሚደርስ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ጓጳ ቀላል የሆነ የሰው ግድያ ማንም ሰው ሀ የአስገዳጅ ሁኔታን ወሰን በመተላለፍ አንቀጽ ድ ወይም ህጋዊ መከላከልን ከመጠን በማሳለፍ አንቀጽ ድቿ ወይም ለ ከፍ ባለ ደም በሚያፈላ ምክንያት ወይም ባልጠበቀው ሕሊናን በሚያውክ ድንገተኛ ምክንያት ወይም በከፍተኛ ስሜት ወይም በብርቱ ዝንባሌ የተነሣ ሆኖ በአእምሮ ግምት ይህን ለማድረግ በሚያደርሱና በከፊል ይቅርታን በሚያሰጡ ሁኔታዎች አስቦ ሌላ ሰውን የገደለ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ሌላ ሰው ራሱን እንዲገድል ማነሣሣትና መርዳት ቺ ማንም ሰው ሌላውን ሰው ራሱን እንዲገድል ያነሣሣ ወይም የረዳ እንደሆነ እራስን የመግደል ሙከራው በተደረገ ጊዜ በቀላል እሥራት እራስን የመግደሉ ተግባር በተፈፀመ ጊዜ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ራሱን እንዲገድል የተነሣሣው ወይም እርዳታ የተደረገለት ለአካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ወይም በአእምሮ ህመም ወይም በዕድሜ መግፋት የተነሣ ችሎታ ያልነበረው ሰው ሲሆን በአነሳሹ ወይም በረጂው ላይ የሚወሰነው ቅጣት የተነሣሣው ወይም የተረዳው ሰው ራሱን ለመግደል ሞክሮ እንደሆነ ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እሥራት ራሱን ገድሎ እንደሆነ ከአሥር ዓመት የማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይሆናል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ድ በቸልተኛነት ሰውን መግደል ሙ ቺ ሟ ማንም ሰው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና ከጀጧ ውስጥ ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውጭ በቸልተኛነት ሰውን የገደለ እንደሆነ ከስድስት ወር እስከ ሦስት ዓመት ሊደርስ በሚችል ቀላል እሥራት ወይም ከሁለት ሺህ እስከ አራት ሺህ ብር ሊደርስ በሚችል መቀጮ ይቀጣል የሌላ ሰውን ሕይወት ጤንነት ወይም ደኅንነት የመጠበቅ የሙያ ወይም ሌላ ግዴታ ያለበት እንደ ህክምና ባለሙያ ወይም አሽከርካሪ ያለ ሰው በቸልተኛነት ሰው የገደለ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት ሊደርስ የሚችል ቀላል እሥራት እና ከሦስት ሺህ እስከ ስድስት ሺህ ብር ሊደርስ የሚችል መቀጮ ይሆናል ጥፋተኛው ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎችን የገደለ ወይም ወንጀሉን የፈፀመው ግልጽ የሆነ ደንብ ወይም መመሪያን ተላልፎ እንደሆነ ወይም የሚያሰክሩ ወይም የሚያፈዙ ንጥረ ነገሮችን ወይም መጠጦችን በመውሰድ እራሱን ከኃላፊነት ነፃ በሚያወጣ ሁኔታ ውስጥ ካስገባ በኋላ ቢሆንም እንኳ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት እስከ አሥራ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ኑ እስራት እና ከብር አሥር ሺህ እስከ አስራ አምስት ሺህ የሚደርስ መቀጮ ይሆናል ድሣ ሕፃንን መግደል አንቀጽ ሬ ሙ ሟ አንዲት እናት ለመውለድ ምጥ በተያዘች ጊዜ ወይም የምጥ ስሜትዋ ሳያልፍ አስባ ልጅዋን የገደለች እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ትቀጣለች ወንጀሉ ሲሞከር በሕፃኑ ሳይ ምንም ዓይነት ጉዳት ያልደረሰ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በአንቀጽ ሸመሠረት ቅጣቱን ያቃልላል አንዲት እናት በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ከተመለከቱት ሁኬቤታዎች ውጭ ልጂን አስባ ወይም በቸልተኛነት የገደለች እንደሆነ ግድያን የሚመለከቱት መደበኛ የሕጉ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ወንጀል በዋና ወንጀል አድራጊነት በአነሳሸነት ወይም በአባሪነት ተካፋይ የሆነ ሌላ ሰው የሕጉ ልዩ አስተያየት ሳይደረግለት እንደነገሩ ሁኔታና እንደጥፋቱ መጠን ሰው ስለመግደል በተመለከቱት መደበኛ የሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ሬ ሙ አንቀጽ ሬ ሙ የወንጀል ሕግ ክፍል ሁለት በፅንስ ላይ የሚደረግ ወንጀል ፅንስ ማስወረድ ኙ መርህ በማናቸውም የእርግዝና ደረጃ የሚገኘውን ጽንስ በአንቀጽ ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውጭ አስቦ ማስወረድ ከዚህ በታች በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ያስቀጣል ፍርድ ቤት የቅጣቱን ዓይነትና መጠን የሚወስነው የማስወረድ ተግባሩ ታስቦ የተፈፀመው በእናቲቱ ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገን መሆኑን ድርጊቱ የተፈፀመው በሦስተኛ ወገን ከሆነ እናቲቱ ፈቅዳ ወይም ሳትፈቅድ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ይሆናል ድሣ አንዲት ሴት በራሷ ላይ የምትፈፅመው የማስወረድ ድርጊት የራሷን ፅንስ አስባ የምታስወርድ ሴት በቀላል እሥራት ትቀጣለች የማስወረጃ መሣሪያ በመስጠት ወይም ማናቸውንም ሌላ ድጋፍ በመስጠት አንዲት ሴት የፀነሰችውን ስታስወርድ በዋና ወንጀል አድራጊነት ወይም በአባሪነት ተካፋይ የሆነ ሌላ ሰው በቀላል እሥራት ይቀጣል ጓ በሌላ ሰው የሚፈፀም የማስወረድ ድርጊት አንቀጽ ሙ ቺ ሟ በሕግ ከተፈቀደው ውጭ አስቦ በፀነሰች ሴት ላይ የማስወረድ ድርጊት የፈፀመ ወይም የማስወረድ ድርጊት በሚፈፀምበት ጊዜ የረዳ ሰው በቀላል እሥራት ይቀጣል የማስወረድ ድርጊቱ የተፈፀመው ያረዝችው ሴት ባልፈቀደችበት ወይም ፈቃዷን ለመስጠት በማትችልበት ጊዜ እንደሆነ ወይም በዛቻ በማስገደድ በማታለል ወይም ድርጊቱ የሚያስከትለውን ውጤት ለማወቅ በማትችልበት ጊዜ ፈቃዷን በማግኘት እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት ለመድረስ የሚችል ፅኑ እሥራት ይሆናል በሕግ ከተፈቀደው ውጭ ለሚፈፀም የጽንስ ማስወረድ ድርጊት ፈቃዲን የሰጠች እርጉዝ ሴት በቀላል እስራት ትቀጣለች ድሣ ከባድ ሁኬቤታዎች አንቀጽ ፅንስ የማስወረድ ተግባር የተፈጸመው በሕግ ከተደነገገው ውጭ የሆነ እንደሆነ ቅጣቱ እንደሚከተለው ይከብዳል የወንጀል ሕግ ሙ ጥፋተኛው ወንጀሉን ያደረገው በአፍቅሮ ንዋይ ወይም ጥቅም ለማግኘት ወይም የዘወትር ተግባሩ በማድረግ እንደሆነ አንቀጽ በአንቀጽ ጽማግጁጄ ከተመለከተው ቅጣት በተጨማሪ በመቀጮ ይቀጣል ቺ ወንጀሉ የተደረገው በቂ የህክምና ሙያ በሌለው ሰው እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት የማያንስ ቀላል እስራትና መቀጮ ይሆናል ሟ ወንጀሉን ያደረገው ባለሙያ በተለይም በሀኪም በመድኃኒት ቀማሚ ፋርማሲስት አዋላጅ ወይም አስታማሚ እንደሆነና ድርጊቱን የፈጸመውም በሙያ ሥራው ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ ከቀላል እስራትና ከመቀጮ በተጨማሪ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛውን ለአንድ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ወንጀሉን የደጋገመ እንደሆነ ለዘወትር ከሙያ ሥራው ያግደዋል አንቀጽ አንቀጽ ጽቋህ እርግዝና በሌላት ሴት ላይ የማስወረድ ድርጊት ለመፈፀም መሞከር እርግዝና በሌላት በአንዲት ሴት ላይ እርጉዝ ናት በማለት የማስወረድ ድርጊት ሙከራ የተደረገ እንደሆነ ሊደረግ ስለማይቻል ወንጀል የተደነገገው ጠቅላላ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል አንቀጽ አንቀጽ ቅጣትን የሚያቀሉ ሁኔታዎች ፅንሱ የተቋረጠው ከዚህ በታች በአንቀጽ ከተዘረዘሩት ሁኔታዎች ውጭ ጥልቅ በሆነ እና በሚቆይ የኑሮ ችግር ምክንያት እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በአንቀጽ መሠረት በመሰለው ቅጣቱን ያቃልላል አንቀጽ ፃ ፅንስን ማቋረጥ በሕግ የተፈቀደባቸው ሁኔታዎች በሕክምና ሙያ በተፈቀደ የጊዜ ገደብ ውስጥ በሕክምና ተቋም ፅንስ ሲቋረጥ በወንጀል የማያስቀጣው ሀ በመደፈር ወይም በዘመድ መካከል በተደረገ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ምክንያት ፅንሱ የተገኘ ሲሆን ለ የእርግዝናው መቀጠል በእናቲቱም ሆነ በፅንሱ ህይወት ወይም በእናቲቱ ጤንነት ላይ አደጋ የሚያስከትል ሲሆን ወይም የልጁ መወለድ በእናቲቱ ጤንነት ወይም ሕይወት ላይ አደጋ የሚያመጣ ሲሆን ሐ ንሱ ሊድን የማይችል ከባድ የአካል ጉድለት ያለው ዲፎርምድ ሲሆን ወይም መ አንዲት እርጉዝ ሴት የአካል ወይም የአእምሮ ጉድለት ያለባት በመሆኗ ወይም ለአካለ መጠን ያልደረሰች በመሆኗ የሚወለደውን ህፃን ለማሳደግ የህሊናም ሆነ የአካል ዝግጅት የሌላት ሲሆን የወንጀል ሕግ ነው በፍጥነት በሚደረግ የሕክምና ሥራ ካልሆነ በቀር ሊወገድ የማይቻል ከባድና ጊዜ የማይሰጥ አደጋ ሲያጋጥም በዚህ ሕግ አንቀጽ ድጽ መሠረት የሚፈፀም የንስ ማስወረድ ተግባር አያስቀጣም አንቀጽ ጽ ፅንስ የሚቋረጥበት ስነስርዓትና ስነስርዓቱን መጣስ የሚያስከትለው ቅጣት ከላይ በአንቀጽ ቿ በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መሠረት ጽንስ ስለሚቋረጥበት ስነ ሥርዓት የእርጉዝ ሴቶችን መብት በማይነካ ሁኔታ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝርዝር መመሪያ ያወጣል በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ጳሀ በተገለጹት ምክንያቶች ጽንስ ለማቋረጥ ሴትየዋ መደፈሯን ወይም ከቤተዘመድ መጸነሷን መግለጺ ብቻ በቂ ይሆናል በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ የተመለከተውን መመሪያ የጣሰ ማንኛውም ሰው ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከሦስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ምዕራፍ ሁለት በሰው አካልና ጤና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች አንቀጽ መርህ ማንም ሰው አስቦ ወይም በቸልተኛነት በማናቸውም ነገር ወይም ዘዴ የሌላውን ሰው አካል ያጐደለ ወይም ጤንነቱን የጉዳ እንደሆነ በዚህ ምዕራፍ በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣል እነዚህ ድንጋጌዎች ማናቸውንም በሰውነት ላይ የሚፈጸሙትን የእጅ እልፊቶችን መምታትን ማቁሰልን የአካል ማጉደልን ጉዳቶችን ወይም ጥፋቶችን እንዲሁም በሰው የአካል ወይም የአእምሮ ጤንነት ላይ የሚፈጸሙትን ጉዳቶች ሁሉ ያጠ ቃልላሉ ፍርድ ቤቱ ለተበዳዩ የሚከፈለውን የጉዳት ካሣ የሚወስነው የጉዳቱን ከባድነትና የተከራካሪ ወገኖችን ሁኔታ ከግምት ወስጥ በማስገባት በዚሁ ሕግ ስለ ጉዳት ካሣ በተደነገገው ጠቅላላ ድንጋጌ መሠረት ይሆናል አንቀጽ ጳ ቺ አንቀጽ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የሚደረግ የልዩ አዋቂ ወይም የባለሙያ ምርመራ ፍርድ ቤቱ ስለ አንድ የአካል ጉዳት ጉዳይ ባህሪ ስለሚያስከትለው ውጤት ወይም ስለከባድነቱ የሚያጠራጥር ነገር ያጋጠመው እንደሆነ ጉዳዩን ለመወሰን በወንጀል ጉዳይ የወንጀል ሕግ ላይ የሚፈጸሙ ድርጊቶችን በሕክምና ምርመራ የሚያውቅ ባለሙያ እንዲረዳው መጠየቅ ይችላል አንቀጽ ዛ ታስቦ የሚፈፀም ከባድ የአካል ጉዳት ማንም ሰው አስቦ ሀ የተጐጂውን ሕይወት በሚያሰጋ ወይም በሰውነቱም ሆነ በአእምሮው ላይ ለዘወትር ጠንቅ በሚያተርፍ ሁኔታ በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም ለ የሌላ ሰውን አካል ወይም አስፈላጊ ከሆኑት ብልቶቹ ወይም ሕዋሳቶቹ አንዱን ያጐደለ እንዳያገለግሉት ያደረገ ወይም በሚያሰቅቅና ጉልህ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ መልኩን ያበላሸ እንደሆነ ወይም ሐ በማናቸውም ሌላ መንገድ ከባድ የሆነ ጉዳትን ወይም በሽታን በሌላ ሰው ላይ ያደረሰ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታና እንደ ጉዳቱ ከባድነት ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት ወይም ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እሥራት ይቀጣል አካል ወይም ጤና ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ቺ ድርጊቱ በወንጀል ክስ አቅራቢነት የሚያስቀጣውና ቅጣቱ ከስድስት ወር እስከ ሦስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ቀላል እሥራት የሚሆነው ሀ ጥፋተኛው ጉዳት ያደረሰው በመርዝ ወይም በገዳይ መሣሪያ ወይም የአካል ጉዳት ለማድረስ በሚችል በማናቸውም ሌሳ መሣሪያ በመጠቀም እንደሆነ ወይም ለ ጥፋተኛው የሙያ ወይም ሌላ ግዴታን በመተላለፍ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም ሐ ተጐጉጂው ደካማ በሽተኛ ወይም ራሱን ለመከላከል የማይችል እንደሆነ ነው የወንጀል ሕግ አንቀጽ ዛ የቅጣት ማቅለያ ሁኔታዎች ማንም ሰው በሌላ ሰው አካል ወይም ጤንነት ላይ አስቦ ጉዳት ያደረሰው ሀ የአስገዳጅ ሁኔታን ወሰን በመተላለፍ አንቀጽ ድ ወይም ሕጋዊ መከላከልን ከመጠን በማሣለፍ አንቀጽ ድቿ እንደሆነ ወይም ለ ከፍ ባለ ደም በሚያፈላ መቀስቀስ ምክንያት ባልጠበቀው ህሊናን በሚያውክ ድንገተኛ ምክንያት ወይም በከፍተኛ ስሜት ወይም ከብርቱ ዝንባሌ የተነሣ ሆኖ ሁኔታዎቹ በአእምሮ ግምት ድርጊቱን ከመፈፀም የሚያደርሱና በከፊል ይቅርታን የሚያሰጡ እንደሆነ ወይም ሐጠ የደረሰው ጉዳት በሕግ የተከለከለ ወይም ጉዳቱ መልካም ጠባይን ሞራልን የሚነካ በሚሆንበት ጊዜ የድርጊቱን ምንነትና ውጤት መገመት በሚችል ተጉጂ ጥያቄ ወይም ፈቃድ መሠረት እንደሆነ ቅጣቱ ከሁለት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአራት ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ፅሐ በተመለከተው ሁኔታ ተጐጂው በዕድሜው ወይም በአእምሮው ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ጥያቄው ወይም እሺታው የሚያስከትለውን ነገር በሙሉ ወይም በከፊል ለመረዳት የማይችል እንደሆነ በጥፋተኛው ላይ የሚወሰነው ቅጣት ከአራት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት ይሆናል አንቀጽ ጽዛ ከጥፋተኛው አሳብ በላይ የደረሰ ጉዳት ማንም ሰው ቀላል የአካል ጉዳት ለማድረስ አስቦ በቸልተኛነት ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ከስድስት ወር እስከ ሶስት ዓመት በሚደርስ ቀላል እሥራት ይቀጣል። ተበዳዩ የጥፋተኛው ተማሪ የሙያ መለማመጃ ትምህርት ተማሪ የቤት ሰራተኛ ወይም ጥፋተኛው በሞግዚትነት የሚያሳድገው ልጅ ወይም እንዲጠብቀው ወይም እንዲንከባከበው የተሰጠው ልጅ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ በቀጥታ በእርሱ ጥገኝነት ወይም ቁጥጥር ሥር የሚገኝ ልጅ እንደሆነ ሀ የንዑስ አንቀጽ ድነጋጌን በተመለከተ ወንጀሉ በሌላ ሰው ከሚፈፀምበት ጊዜ ይልቅ በዚህ ዓይነቱ ሰው ላይ ቅጣቱ ይከብዳል ለ የንዑስ አንቀጽ ድንጋጌን በተመለከተ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ይሆናል ሐ የንዑስ አንቀጽ ድንጋጌን በተመለከተ ቅጣቱ ከስድስት ወር የማያንስ ቀሳል እስራት ይሆናል ድርጊቱ በተበዳዩ ላይ ሞትን ወይም ከባድ የአካል ወይም የአእምሮ ጉዳትን አስከትሎ እንደሆነ ወይም ተበዳዩ ተበዳዩዋ ከጭንቀት ከሀፍረት ወይም ተስፋ ከመቁረጥ የተነሣ ራሱን ራስዋን የገደለ የገደለች እንደሆነ ቅጣቱ የዕድሜ ልክ ጽኑ እሥራት ይሆናል አንቀጽ ጄጣ የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት ለአካለመጠን ባልደረሱ ልጆች የንጽሕና ክብር ላይ በሚፈጸም የድፍረት በደል ያለው ተካፋይነት ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን ለማሣደግ ለማስተማር ለማሰልጠን ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለመንከባከብ የተቋቋመ ድርጅት ሃላፊ ሠራተኛ ወይም ማንኛውም ሌላ ሰው በዚህ ዓይነቱ ድርጅት ውስጥ በሚገኝ ልጅ ላይ በዚህ ሕግ ከአንቀጽ ቿ እና በአንቀጽ ቋጂ ከተመለከቱት ድርጊቶች አንዱን የፈፀመ ሲሆንና የድርጅቱ አሠራር ወይም አስተዳደር ለወንጀሉ አፈፃፀም ምቹ ሁኔታን የፈጠረ እንደሆነ ወይም ድርጊቱ የተፈጸመው ድርጅቱ በቂ ጥበቃ ባለማድረጉ እንደሆነ እንደየወንጀሉ ዓይነትና ከባድነት በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ጣ በእንስሳት ላይ የግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈፀም ማንም ሰው በእንስሳት ላይ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፈጸመ እንደሆነ በቀላል እሥራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ ክፍል ሦስት በሌሎች የሥነምግባር ብልሹነት መጠቀም አንቀጽ ወ የሌላውን ሰው የዝሙት ድርጊት የዘወትር መጠቀሚያ ማድረግ ማንም ሰው ጥቅም ለማግኘት ሲል የሌላውን ሰው የዝሙት ድርጊት የዘወትር መጠቀሚያው አድርጉ የያዘ ሌላውን ሰው ለዝሙት ድርጊት ያቀረበ ወይም ያቃጠረ ቤቱን በሙሉ ወይም በከፊል ለዚሁ ተግባር ያዋለ ወይም ያከራየ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ የሌላውን ሰው የዝሙት ድርጊት የዘወትር መጠቀሚያ አድርጉ የያዘ እንደሆነ በቀላል እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ጸወራ ሴቶ በማቃጠር መነገድ ማንም ሰው ለጥቅም ሲል ወይም የሌላውን ሰው ፍትወተ ሥጋ ለማርካት ሀ በፈቃዳቸውም ቢሆን በዝሙት አዳሪነት እንዲሰማሩ በማነሳሳት በማባበል በማቅረብ ወይም በማናቸውም ዘዴ በመገፋፋት ሴቶችን ወይም ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን በማቃጠር የነገደ ወይም ከቦታ ቦታ ያዚዚረ ወይም ለ የተባለውን ሰው ለዝሙት ለማቅረብ በዝሙት አዳሪ ቤት ያስቀመጠ እንደሆነ በተለይ ከሕግ ውጭ በግድ ይዞ የማስቀመጥ ድርጊት አብሮ በተፈጸመ ጊዜ ከበድ ያሉ የቅጣት ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት እንደተጠበቀ ሆኖ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና ከአሥር ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ ጣ ወንጀሉን የሚያከብዱ ሁኔታዎች ሞያ ተብሎ በተያዘ ሰዎችን ለዝሙት የማቅረብ ወይም ከቦታ ቦታ የማዚዚር ሥራ ሀ ተበዳዩ ለአካለ መጠን ያልደረሰ እንደሆነ ወይም ለ ተበዳዩ የወንጀለኛው ሚስት ወይም ወደታች የሚቆጠር ተወላጅ የጉዲፈቻ ልጅ የሚስቱ የወንድሙ ወይም የእህቱ ልጅ በሞግዚትነት የሚጠብቀው ልጅ ወይም በማናቸውም ምክንያት እንዲጠብቀው ወይም እንዲንከባከበው በአደራ የተሰጠው እንደሆነ ወይም ሐ ወንጀለኛው ድርጊቱን የፈፀመው የተበዳዩን የገንዘብ ችግር ወይም የኅሊና ኀዘን ወይም በዚህ ሰው ላይ ያለውን የጠባቂነት የአሠሪነት የአስተማሪነት የአከራይነት ወይም የአበዳሪነት ወይም ይህን የመሰለውን ሌላ ሥልጣኑን ምክንያት በማድረግ እንደሆነ ወይም የወንጀል ሕግ መ ወንጀለኛው በተንኮል በማታለል በኃይል በዛቻ ወይም በማስገደድ ተጠቅሞ ወይም በተበዳዩ ላይ ያለውን ሥልጣን ያለአግባብ ተገልግሎ እንደሆነ ወይም ሠ ተበዳዩ ማቃጠርን የሙያ ሥራ አድርጐ ለያዘ ሰው ተላልፎ የተሰጠ እንደሆነ ወይም ወደ ውጭ አገር ተወስዶ ወይም ወሬው አድራሻው ወይም መኖሪያ ቦታው ሊታወቅ ያልተቻለ እንደሆነ ወይም ረ ተበዳዩ ከኃፍረት ከጭንቀት ወይም ተስፋ ከመቁረጥ የተነሣ ራሱን ለመግደል ተገፋፍቶ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እሥራት እና ከሃያ ሺ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል አንቀጽ ሴቶችንና ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን ለዝሙት ለማቅረብ የሚደረጉ ዝግጅቶች ማንም ሰው ሴቶችን ወይም ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን ለዝሙት ሥራ እንዲውሉ ለማቅረብ ወይም ከቦታ ቦታ ለማዚዚር ዝግጅቶችን ያደረገ ወይም ሁኔታዎችን ያመቻቸ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም እንደነገሩ ሁኔታ በተለይም ማቃጠርን የሙያ ሥራ አድርጐ የያዘ ሰው ተሳትፎ እንደሆነ ወይም ዝግጅቶቹ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁና በብዙ ተበዳዮች ላይ ሊፈጸሙ ታቅደው እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት እና ጥፋቱ ከባድ ሲሆን ከአምስት መቶ ብር በማያንስ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት የወንጀል ተጠያቂነት የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በዚህ ክፍል በተደነገጉት ወንጀሎች ተካፋይ እንደሆነ እንደወንጀሉ ዓይነትና እንደነገሩ ሁኔታ በዚህ ሕግ በአንቀጽ መሠረት ይቀጣል ክፍል አራት በመልካም ጠባይ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ ቋሀ ለመልካም ሥነ ምግባርና ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ብልግናና አሣፋሪ ሥራን በአደባባይ መፈፀም ማንም ሰው አስቦ ሕዝብ በሚያዘወትርበት ቦታ ወይም በሕዝብ ፊት የግብረ ሥጋ ድርጊትን ወይም ለመልካም ጠባይ ወይም ለመልካም ሥነ ምግባር በብርቱ ተቃራኒ የሆነውን ማናቸውንም ሌላ ጸያፍ ድርጊት የፈጸመ ወይም በአኳጓኋን ያሳየ እንደሆነ ከሦስት ወር እስከ አንድ ዓመት በሚደርስ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል የወንጀል ሕግ ጥፋተኛው ለአካለመጠን ባልደረሰ ልጅ ፊት ድርጊቱን የፈፀመ እንደሆነ ቅጣቱ ከስድስት ወር እስከ አምስት ዓመት የሚደረስ ቀላል እሥራት ይሆናል ፀያፍ ወይም የብልግና ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን ለሕዝብ መግለፅ ውጮ ከ አንቀጽ ሙ ማንም ሰው ሀ ጸያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ ጽሁፎችን ምስሎችን ስዕላዊ መግለጫዎችን ፖስተሮችን ፊልሞችን ወይም ሌሎች ነገሮችን ያዘጋጀ ወደ አገር ውስጥ ያስገባ ወይም ወደ ውጭ አገር የሳከ ያጓጓዘ የተቀበለ የያዘ ለህዝብ ያሳየ ለሽያጭ ወይም ለኪራይ ያቀረበ ያከፋፈለ ያሰራጨ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ከቦታ ቦታ ያዚዚረ ወይም በነዚህ ነገሮች የነገደ ወይም ለ እነዚህ ነገሮች እንደምን ወይም ከማን ሊገኙ ወይም ሊዘዋወሩ ሊሠራጩ እንደሚችሉ በማናቸውም ዘዴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስታወቀ ያመለከተ ወይም እንዲታወቅ ያደረገ እንደሆነ የተከሰሰባቸው ነገሮች መወረሳቸው ወይም እንዲጠፉ መደረጋቸው ሳይቀር ከስድስት ወር በማያንስ ቀላል እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል ቺ ወንጀለኛው ሀ ይህ ዓይነቱን ንግድ ሙያው አድርጐ የያዘው ወይም የተሠማራበት ለ እንደዚህ ያሉትን ነገሮች ለአካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች አስቦ ያሳየ የሰጠ ወይም ያስረከበ እንደሆነ ወይም ሐ ለዚሁ ዓላማ ሲባል አካለመጠን ያልደረሱ ልጆች የግብረስጋ ግንኙነት የፈጸሙ በማስመሰል ያሳየ ወይም ሀፍረተሥጋቸው እንዲታይ ያደረገ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት የማያንስ ቀላል እሥራት እና ከአስር ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል አንቀጽ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን ማሣየት ማንም ሰው ጸያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን በትያትር በሲኒማ በተንቀሳቃሽ ፊልሞች በሬዲዮ በቪዲዮ በቴሌቪዥን ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ እንዲተላለፍ ያደራጀ ለሕዝብ ያሰማ ወይም እንዲታይ ያደረገ እንደሆነ ከዚህ በላይ በተመለከተው አንቀጽ የተወሰኑት ቅጣቶች ይፈጸሙበታል የወንጀል ሕግ አንቀጽ የተፈቀዱ ሥራዎች ወሲብን ወይም ፍትወተ ሥጋን ለመቀስቀስ ያልታሰቡ በባሕሪያቸው በሞላ ስነ ጥበባዊ ስነ ጽሁፋዊ ወይም ሣይንሳዊ የሆኑ ሥራዎች እንደጸያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶች እንደሆኑ ሊቆጠሩ አይችሉም አንቀጽ ግ ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆኑ መግለጫዎችና ማስታወቂያዎች ማንም ሰው ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ ወይም ከግብረ ገብ ውጭ የሆኑ ነገሮችን ምርቶችን ወይም ሥራዎችን ለሕዝብ እይታ ያቀረበ እንደሆነ ከአንድ ወር በማያንስ ቀላል እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ማንም ሰው እነዚህኑ ነገሮች ወዳልጠየቁ ወይም በነዚሁ ላይ የሙያ ዝንባሌ ወደሌላቸው ሰዎች በማናቸውም ዘዴ የሳከ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም በቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ሣ ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን አደጋ ላይ ከሚጥሉ ሥራዎች መጠበቅ ማንም ሰው ለጥቅም ወይም ስሜትን ለመቀስቀስ ሲል ሀ ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን የግብረ ሥጋ ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ ከልክ በላይ ለመቀስቀስ ለማበላሸት ወይም ለማሳሳት ወይም ለአካለመጠን ባልደረሱ ልጆች ላይ የጭካኔ ወይም የገዳይነት ዝንባሌን ወይም ፀረ ማኅበራዊ የሆኑ ወይም ቤተሰባዊ ኑሮን የሚያናጉ ስሜቶችን ከመጠን በላይ ለማነሣሣት ለመቀስቀስ ወይም ለማሳደር የሚችሉ ጽሁፎችን ምስሎችን ወይም ነገሮችን በንግድ ቤት መስኮት በንግድ ዕቃ ማሳያ ቦታ ወይም ከውጭ ለሕዝብ ሊታይ በሚችል በማናቸውም ሌላ ስፍራ በማስቀመጥ በቪዲዮ ወይም በማናቸውም ሌላ ዘዴ እንዲታይ ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ እንደነዚህ ያሉ ነገሮችን ምስሎችን ወይም ሁፎችን ለአካለ መጠን ላልደረሰ ልጅ እያወቀ ያቀረበ ያዋሰ የሰጠ ወይም የሸጠ እንደሆነ አስፈላጊም ሲሆን የዕቃው መወረስ ሳይቀር ከስድስት ወር እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ ቀላል እሥራት እና በመቀጮ ይቀጣል የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት የወንጀል ተጠያቂነት ከ ውጮ አንቀጽ የወንጀል ሕግ የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በዚህ ክፍል በተደነገጉት ወንጀሉች ተካፋይ እንደሆነ እንደወንጀሉ ዓይነትና እንደነገሩ ሁኔታ በዚህ ሕግ በአንቀጽ ሾዩዝ መሠረት ይቀጣል ምዕራፍ ሁለት በቤተዘመድ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ክፍል አንድ በጋብቻ ሥርዓት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች አንቀጽ ዌ ጋብቻን በተንኮል ወይም በማታለል መፈፀም ማንም ሰው ጋብቻን በሚፈጽምበት ጊዜ ወይም ለመፈጸም ሲል ጋብቻውን ለማፍረስ ቺ ወይም እንዳይጸና ለማድረግ ከሚያስችሉት በሕግ ከተደነገጉት ምክንያቶች አንዱን የሚያሟላ ፍሬ ነገር አስቦ ከሌላው ተጋቢ የደበቀ እንደሆነ ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ማንም ሰው አስቦ ማንነቱን በተመለከተ ሌላውን ሰው በመደበቅ በማሳሳት በማጭበርበር ወይም በማታለል ጋብቻን የፈፀመ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አንቀጽ በሕግ የተከለከለ ጋብቻን ማስፈፀም ወይም መፈፀም ቺ ሟ አንቀጽ ፎ መሚ ዴ ሁ ማንም ሰው በሕግ የተከለከውን ጋብቻ አስቦ ያስፈፀመ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል አስቦ በሕግ የተከለከለውን ጋብቻ የፈፀመ ተጋቢ የፈቀደ ሰው ወይም ለዚህ ዓይነቱ ጋብቻ ምስክር የሆነ ሰው በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ጳ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ እና የተመለከተው ድርጊት የተፈፀመው በቸልተኛነት ሲሆን ከሦስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ያስቀጣል ያለዕድሜ ጋብቻ የወንጀል ሕግ አግባብ ባለው የቤተሰብ ሕግ ከተፈቀደው ውጭ ማንም ሰው አስቦ ለአካለ መጠን ያለደረሰችውን ልጅ ያገባ እንደሆነ ሀ የተበዳይዋ ዕድሜ አስራ ሶስት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ በሆነ ጊዜ ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እስራት ወይም ለ የተበዳይዋ ዕድሜ ከአስራ ሶስት ዓመት በታች በሆነ ጊዜ ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ አስራት ያስቀጣል አንቀጽ ግሀ ሕገወጥ ጋብቻ መፈፀምና ማስፈፀም በወንጀል የማያስጠይቅበት ሁኔታ ጋብቻው ካልፈረሰ በቀር በአንቀጽ ዌ ወይም በአንቀጽ ማግ በተመለከተው ወንጀል ላይ ክስ ሊቀርብ አይችልም አንቀጽ ፃ በጋብቻ ላይ ጋብቻ መፈፀም ፅጳ ማንም ሰው አስቀድሞ በሕግ በጸና ጋብቻ ታስሮ ሳለ ይኸው ጋብቻ ከመፍረሱ ወይም ከመሻሩ በፊት ሌላ ጋብቻ የፈጸመ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን በተለይም ጥፋተኛው የራሱን እውነተኛ ሁኔታ በመሰወር ከርሱ ጋራ ሁለተኛውን ጋብቻ የፈጸመውን ሰው አውቆ ያሳሳተ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እስራት ይቀጣል ማንም ያላገባ ሰው ሌላው ሰው በጸና ጋብቻ የታሰረ መሆኑን እያወቀ ከዚሁ ሰው ጋር ጋብቻ የፈጸመ እንደሆነ በቀላል እሥራት ይቀጣል ከሁለቱ ጋብቻዎች አንዱ እስከሚፈርስበት ወይም እስከሚሻርበት ጊዜ ድረስ የወንጀሉ ክስ ይርጋ ዘመን መቆጠር ታግዶ ይቆያል አንቀጽ የተለየ ሁኔታ በጋብቻ ላይ ጋብቻ የተፈጸመው አግባብ ባለው ሕግ በተለየ ሁኔታ በሀይማኖት ወይም በባህል ሥርዓቶች ላይ ተመስርተው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች በሚሰጠው እውቅና መሠረት እንደሆነ ከዚህ በላይ የተመለከተው ቅጣት ተፈጻሚ አይሆንም አንቀጽ አመንዝራነት የወንጀል ሕግ አንድ ባለትዳር በፍትሐ ብሔር ሕግ መሠረት በፀና ጋብቻ ታስሮ ሳለ ከሌላ ሰው ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፈፀመ እንደሆነ በተበደለው ባለትዳር የግል አቤቱታ አቅራቢነት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል እያወቀ ህጋዊ ጋብቻ ካለው ሰው ጋር ባመነዘረው ሰው ላይም ይኸው ቅጣት ተፈጻሚ ይሆናል አቤት ባይ ያመንዝራነት ተግባሩ እንዲፈጸም የገፋፋ ወይም የተስማማ ወይም ይቅርታ ያደረገ ወይም ከዚሁ ተግባር ጥቅምን ያገኘ እንደሆነ ጥፋተኛው ሰው በወንጀል ተጠያቂ አይሆንም ቺ ያመንዝራነቱ ድርጊት የተፈፀመው ባልና ሚስቱ በመካከላቸው በተፈጠረ ጠብ ምክንያት ከአንድ ዓመት በላይ በአንድነት መኖራቸው ቀርቶ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በአንቀጽ ሸመሠረት የጥፋተኛውን ቅጣት ሊያቃልል ይችሳላል ሟ ጥፋተኛው ሳይፋታ ወይም ሌላው ተጋቢ ጥሎት ሳይሄድ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ውሽማ ያስቀመጠ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ወር የማያንስ ቀላል እሥራት ይሆናል አንቀጽ የአቤት ባዩ መሞት ተበዳዩ የግል አቤቱታ ሳያቀርብ የሞተ እንደሆነ ጥፋተኛው በወንጀል ተጠያቂ አይሆንም ተበዳዩ የግል አቤቱታ ካቀረበ በኋላ ጥፋተኛው ክስ ቀርቦበት የእሥራት ቅጣት ተፈርዶበት እንደሆነ ተበዳዩ ቢሞትም ባይሞትም የአካባቢ ሁኔታዎቹ በተለይም ጥፋተኛው ቤተሰብን የማስተደደር ወይም የመደገፍ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ለፍርዱ በቂ ምክንያት ሆኖ ሲገኝ ፍርድ ቤቱ ምክንያቱን በመግለፅ ቅጣቱ እንዲቀርለት ለማዘዝ ይችላል ክፍል ሁለት በዘመዳሞች መካከል የሚፈፀም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ወንጀል አንቀጽ በዘመዳሞች መካከል የሚፈፀም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጋብቻቸው በሥጋ ዝምድና ምክንያት አግባብ ባለው ሕግ በተከለከለ ሰዎች መካከል ታስቦ የሚፈፀም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ከቤተ ዘመድ ሥልጣን የመሻሩ ቅጣት እንደተጠበቀ ሆኖ እንደነገሩ ሁቤኔታ ከሦስት ወር በማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ከሦስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ያስቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ በዘመዳሞች መካከል የሚፈፀም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ የብልግና ድርጊት የሥጋ ዝምድና ባላቸው ሰዎች መካከል የሚፈፀም የግብረ ሥጋ ግንኙነትን የመሰለ ወይም ለንፅህና ክብር ተቃራኒ የሆነ ሌላ ድርጊት ከስድስት ወር በማያንስ ቀላል እሥራት ያስቀጣል ክፍል ሦስት በክብር መዝገብ ላይ እና የቤተዘመድ ግዴታዎችን በመተላለፍ የሚፈፀሙ ወንጀሎች የህፃን መወለድን ወይም ተጥሎ መገኘትን አለማስታወቅ ሕግ በሚያዘው መሠረት የአንድ ህፃንን መወለድ ለክብር መዝገብ ሹም ያላስታወቀ ማንም ሰው ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ማንም ሰው የተጣለ ሕፃን አግኝቶ ለሚመለከተው ባለሥልጣን ሳያስታውቅ የቀረ እንደሆነ በንኡስ አንቀጽ ቋ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል አንቀጽ የክብር መዝገብን በሐሰት መለወጥ አስመስሎ ህፃንን ማቅረብ ወይም መለወጥ ማንም ሰው በሌላ ሰው የክብር መዝገብ ሊመዘገብ የሚገባውን ማናቸውንም ፍሬ ነገር የደበቀ ወይም ወደ ሀሰት የለወጠ በተለይም የአንድን ህፃን ማንነት ወይም ልደት በሚመለከት አስቦ ሀሰተኛ መግለጫ የመዘገበ ወይም ያስመዘገበ እንደሆነ በቀላል እሥራት ይቀጣል ወንጀሉ አስቀድሞ ሊታወቅ ይችል የነበረ ከባድ ውጤትን ያስከተለ ወይም ሊያስከትል የሚችል ሆኖ በተለይም ህፃን አለዋውጦ የማስመዝገቡ ድርጊት የሚያስከትለውን ውጤት የሚመለከት ሲሆን ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ያስቀጣል አንቀጽ የቀለብ መስጠት ግዴታን አለመፈፀም ማንም ሰው ያለበቂ ምክንያት የወንጀል ሕግ ሀ በሕግ መሠረት ሊሰጥ የሚገባውን ቀለብ ለባለመብቶች የፍቺ ውሣኔ እስከ ሜሰጥበት ጊዜ ድረስ የፍቺ ጥያቄ ላቀረበ የትዳር ጓደኛም ቢሆን አልሰጥም ያለ ወይም መስጠትን ያስተጓጐጉለ እንደሆነ ወይም ለ በሕግ ወይም በውል በገባው ግዴታ መሠረት ከጋብቻ ውጭ ላስረገዛት ሴት ወይም ከጋብቻ ውጭ በግብረ ሥጋ ግንኙነት አብሮት ለኖረ ሰው ወይም ከጋብቻ ውጭ ለተወለደው ልጅ ሊያሟላ የሚገባውን የገንዘብ ግዴታ ያልተወጣ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በመቀጮ ወይም ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የልጅ ማሣደግ ግዴታን አለመፈፀም ማንም ወላጅ ወይም የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥልጣን ያለው ሌላ ሰው ጥቅምን በመፈለግ ወይም ያለበትን ግዴታ ቸል በማለት ሀ በኃላፊነቱ ሥር የሚገኘውን ልጅ በከባድ ሁኔታ ያለ በቂ ጥንቃቄና ክብካቤ የተወ ወይም ለሥነ ልቦናዊ ወይም አካላዊ አደጋ ያጋለጠ እንደሆነ ወይም ለ አካላዊ ወይም ሥነ ልቦናዊ ጉዳት እንደሚያደርስበት ለሚያውቀው ወይም መገመት ለሚችለው ሰው ድርጅት ወይም ተቋም ልጁን ለረጅም ጊዜ የሰጠ እንደሆነ ነገሩ ከባድ ሲሆን ከቤተዘመድ ሥልጣኑ መሻሩ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል ቺ የመቅጣትን ልክ በመተላለፍም ይሁን በመበደል ልጁ አስቀድሞ ሊታወቅ የሚችል ወይም የታቀደ ጉዳት የደረሰበት እንደሆነ አግባብ ያለው የዚህ ሕግ ሌላ ድንጋጌ በተደራቢነት ተፈጻሚሜ ይሆናል አንቀጽ ቿከ ምዕራፍ ሦስት የወል ድንጋጌዎች የወንጀሎች መደራረብ በጋብቻ ሥርዓት ላይ ከሚፈፀሙት ወንጀሎች አንዱ አንቀጽ ሣቿ ማሣ ወይም በዝምድና ላይ ከሚፈፀም ወንጀል ጋር አንቀጽ ዛ በ አንድ ላይ ተጣምሮ ሲገጃ ሁለቱም ድንጋጌዎች በተደራራቢነት ተፈፃሚ ይሆናሉ በግብረ ሥጋ ነፃነት ላይ የሚፈፀሙት ወንጀሎች አንቀጽ እና ሄ እና ወ በዝምድና ላይ ከሚፈፀም ወንጀል አንቀጽ ያ ጋር ተጣምረው ሲገኙ አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈፃሚ ይሆ ሟ የወንጀል ሕግ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች በወንጀል ተጠያቂነት ቺ የግብረ ሥጋ በደል ለንፅሕና ክብር ተቃራኒ የሆነ ድርጊት ወይም ተፈጥሮአዊ ያልሆነ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የተፈፀመበት ለአካለመጠን ያልደረሰ ሰው በወንጀሉ ተጠያቂ አይሆንም ተስማሚ የሆኑት የመልካም አስተዳደግና የጥበቃ ውሳኔዎች በእርሱ ላይ ሊፈፀሙ ይችላሉ በሌሎች ሰዎች ላይ ወንጀሉን የፈፀመው ለአካለመጠን ያልደረሰ ሰው የዚህ ሕግ መደበኛ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆነብታል አንቀጽ ነ የወንጀል ሕግ ስድስተኛ መጽሐፍ በንብረት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ርዕስ አንድ በንብረት መብቶች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ መርህ በሌላ ሰው የንብረትና የኢኮኖሚ መብት ወይም በገንዘብ ሊተመኑ በሚችሉ መብቶች ላይ የሚደረግ ጣልቃ ገብነት አነስተኛ ከመሆኑ የተነሣ በደንብ እልፊት የሚያስቀጣ ካልሆነ በቀር ከዚህ ቀጥሎ በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ያስቀጣል የመንግሥት የሕዝብና የግል ንብረት በዚህ ሕግ ጥበቃ ይደረግለታል በዚህ ሕግ መሠረት በንብረት መብት ላይ ጉዳት ደርሷል የሚባለው ወንጀሉ ባይፈፀም ኖሮ ንብረቱ ሊገኝበት ይችል የነበረውን ሁኔታ የሚለውጥ ጉዳት ወይም ብልሽት ደርሶ ከሆነ ነው አንቀጽ ሕገወጥ በሆነ መንገድ ወይም ያለአግባብ የመበልፀግ ግምት ወንጀል አድራጊው ለራሱ ወይም ለሌላ ሦስተኛ ሰው ሕገወጥ የሆነ ጥቅም ለማስገኘት አስቦ የፈፀመው ድርጊት ወንጀል መሆኑ በሕግ የተደነገገ ሲሆን ድርጊቱ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት የተፈፀመ ነው ተብሎ ይገመታል እንደዚህ ባለ ሁኔታ የታሰበው ብልፅግና ባይገኝም እንኳን ያለአግባብ የመበልፀግ ፍላጐቱና ተግባሩ ተጣምረው መገኘታቸው ከተረጋገጠ ፍፃሜ ያገኘ ወንጀል እንደተደረገ ይቆጠራል በዚህ ሁኔታ የተወሰደውን ሀብት የመመለስ ወይም ለደረሰው ጉዳት ካሣ አስቀድሞ የመክፈሉ ጉዳይ በአድራጊው ፈቃደኛነት የተፈፀመ ቢሆንም ወንጀሉን አያስቀረውም ነገር ግን ስለቅጣቱ አወሳሰን ፍርድ ቤቱ ይህንን ከግምት ማስገባት ይችላል አንቀጽጀሠ አንቀጽ በቤተዘመድ አባሎች መካከል ወንጀል በተደረገ ጊዜ የሚቀርብ ክስ እንደ ውንብድና መንጠቅ ወይም ማስፈራራት ከመሳሰሉ በኃይል ወይም በማስገደድ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች በስተቀር ሌሎች ወንጀሎች የተደረጉት ሀ በወላጅና ተወላጅ በአሣዳጊና በማደጐ ልጅ ባልተለያዩ ባልና ሚስት በጋብቻ ወቅት በአሣዳጊና በእንጀራ ልጅ በእናት ወይም በአባት ወይም በሁለቱም በሚገናኙ ልጆች መካከል ሲሆን ወይም የወንጀል ሕግ ለ በተበዳዩ ቤት በሚኖሩ ቤተዘመዶች መካከል ሲሆን ክሱ የሚታየው በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ ይሆናል የግል ተበዳዩ የክስ አቤቱታ አለማቅረቡ ከላይ በተጠቀሱት የዝምድና ሐረጐች ያልተሸፈኑ የወንጀሉ ተካፋዩችን ከተጠያቂነት አያድናቸውም አንቀጽ ማ ምዕራፍ ሁለት በንብረት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች ክፍል አንድ በተንቀሳቃሽ ንብረት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሉች አንቀጽ ስርቆት ማንም ሰው የማይገባውን ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የሌላ ሰው ንብረት የሆነውን ተንቀሳቃሽ ዕቃ ወይም ከማይንቀሳቀስ ንብረት የተነጠ ለን ዕቃ አንስቶ የወሰደ በቀጥታ የራሱ ንብረት ያደረገ ወይም በተዘዋዋሪ ከራሱ ንብረት ጋር እንዲቀላቀል ያደረገ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አድራጊው ከማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ተንቀሳቃሹን ዕቃ የነጠለው ራሱ እንደሆነና ይሄንን ድርጊት የፈፀመው በተንቀሳቃሹ ወይም በማይንቀሳቀሰው ንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ እንደሆነ የዚህ ሕግ የአንቀጽ ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈፃሚ ይሆኑበታል ማንም ሰው በቀላል አኳኋን የሰረቀው እጅግ አነስተኛ ግምት ያለው የሌላ ሰው ዕቃ ሲሆን ስለደንብ እልፊት በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ቿ እና አንቀጽ ኃይልን መስረቅ ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የሌላ ሰው ንብረት ከሆነ የኃይል ማሰራጫ ወይም ለሌላ ሰው ከተዘረጋ መስመር ላይ ጋዝ እንፋሎት ኤሌክትሪክ ወይም ሌላ ዓይነት ኃይል በመውሰድ የራሱ ያደረገ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ የጋራ ንብረት የሆኑትን ዕቃዎች መስረቅ ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በጋራ ባለንብረትነት በሽርክና ወይም በወራሽነት ምክንያት የጋራ ሀብት የሆነውን ዕቃ የወሰደ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል የጋራ ንብረቱ አላቂ ነገር ሆኖ ተከሳሹ የወሰደው ለራሱ ከሚገባው ድርሻ ያልበለጠ እንደሆነ አያስቀጣውም አንቀጽ ቿ በሙታን ላይ የሚፈፀም ስርቆት ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ከሙታን መቃብር ላይ ወይም ከመቃብር ቤት ውስጥ ወይም ከተቀበረ ወይም ካልተቀበረ አስከሬን ላይ ዕቃ የወሰደ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ሀ ከባድ ስርቆት እንደወንጀሉ ክብደትና በተሰረቀው ዕቃ ዓይነት በወንጀለኛው የኑሮ ደረጃና ሁኔታ እንዲሁም በአሰራረቁ ዓይነት ቀጥሎ የተዘረዘሩት የቅጣት ማክበጃ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት የማያንስ ቀላል እስራት ወይም ከአሥራ አምስት ዓመት የማይበልጥ ኑ እሥራት የሚሆነው ወንጀሉ የሚመለከታቸው ሀ የተሠረቀው ዕቃ የሀይማኖት ሥርዓት በሚፈፀምበት ሥፍራ ውስጥ የሚገጃቿ የሃይማኖት ዕቃ ወይም በቤተ መዘክር ውስጥ የተቀመጠ ዕቃ ወይም ለሕዝብ ክፍት በሆነ ህንፃ ውስጥ የተቀመጠ ሳይንሳዊ ኪነጥበባዊ ወይም ታሪካዊ ዋጋ ያለው ዕቃ እንደሆነ ለ የተለየ ጠባቂ የሌለው እንስሳ ወይም ሰብል ወይም ለቴሌኮሙኒኬሽን ለኤሌክትሪክ ኃይል ለውሃና ፍሳሽ ወይም ለማናቸውም ሌላ ድርጅት አገልግሎት የሚውል ጠባቂ የሌለው መሣሪያ ወይም ዕቃ ወይም እንዲቀመጥ ወይም እንዲላክ ለዕቃ ማከማቻ ለአንድ ድርጅት ወይም የመንግሥት መሥሪያ ቤት በተለይም ለፖስታ ቤት ወይም ለማመላለሻ ድርጅት የተሰጠ ሸቀጥ ወይም ዕቃ እንደሆነ ነው ወንጀሉን የፈፀመው የወንጀል ሕግ ሀ የመከላከያ ሰራዊት አባል ሆኖ ወንጀሉን የፈፀመው በጓደኞቹ ወይም በአለቆቹ ላይ ሲሆን ወይም የተሰረቀው ዕቃ ሠራዊቱን የሚያገለግል ወይም እንዲያ ገለግል የተመደበ ሲሆን ለ የመንግሥት ሠራተኛ ወይም አንድ የንግድና ይህን የመሳሰለ ልዩ ሥራ የሚያከናውን ሰው የባንክ ሠራተኛ ጠበቃ ውል አዋዋይ የወኪልነት ሥልጣን የተሰጠው እንደራሴ ወይም በእንደዚህ ያለ ምክንያት የተሰጠውን ሥልጣን በማከናወን ላይ የሚገኝ የንግድ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ድርጊቱን የፈፀመው በተለይ በተሰጠው ሥልጣን ምክንያት በእጁ በገባው የመንግሥት የህዝብ ወይም የግል ንብረት ላይ ሲሆን ሐ ባለሆቴል የቤት አከራይ ዕቃ አመላላሽ ተሸካሚ ወይም ይህን የመሳሰለ ሥራ የሚያካሂድ ሆኖ የተሰረቀው ንብረት የደንበኛው ሲሆን መ የቤት ሠራተኛ ሠራተኛ ወይም ሥራ ለማጅ ሆኖ ሥራውን ምክንያት በማድረግ በአሳዳሪው ወይም በአሰሪው ላይ ጉዳት በሚያደርስ ሁኔታ ሲሆን ነው አድራጊው ሀ በሰዎች ወይም በንብረት ላይ ወንጀል ለመፈፀም የተቋቋመ ቡድን አባል ሲሆን ለ ስርቆቱን የፈፀመው በተለይ አደገኛ መሆኑን በሚያሣይ በማናቸውም ሌላ ሁኔታ ይልቁንም የማጥቂያ ወይም የመከላከያ የጦር መሣሪያ ወይም የቤት መሰርሰሪያ መሣሪያ በመያዝ ሲሆን ወይም ራሱን የመንግሥት ሠራተኛ በማስመሰል ሲሆን ወይም በሌሊት ወይም ቅጥር በመጣስ አጥር በመዝለል በር በመስበር ግድግዳ በመሰርሰር ወይም በቡድን በመሆን ሲሆን ወይም ያልተጠበቀ አደገኛ ሁኔታን የሕዝብ ብጥብጥን ወይም መቅሰፍትን ይልቁንም እንደግርግር ቃጠሉ ጐርፍ ማዕበል የመሳሰለውን ሽፋን በማድረግ ሲሆን ነው አንቀጽ ድ ውንብድና ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት አስቦ የሌላ ሰው ንብረት የሆነውን ተንቀሳቃሽ ዕቃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ወይም በሚወስድበት ጊዜም ሆነ ከወሰደ በኋላ የገጠመውን ተቃውሞ ውጤታማነት ለማስቀረት ሲል በሌላ ሰው ላይ የኃይል ድርጊት ወይም ከባድ የሆነ የማንገላታት ተግባር ወይም ከባድ ዛቻ የፈፀመ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ይህን ሰው ለመከላከል እንዳይችል ያደረገው ሲሆን ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ድጳ ከባድ ውንብድና አድራጊው በአንቀጽ ድ የተመለከተውን ወንጀል የፈጸመው ሀ በሰዎች ላይ ወይም በንብረት ላይ የኃይል ተግባር ለመፈፀም በተቋቋመ የወንበዴ ቡድን አባል በመሆን ሲሆን ወይም ለ ተበዳዩን እገድልሀለሁ ብሎ እርግጠኛ የሞት አደጋ እንደሚያደርስበት በመቃጣት ይልቁንም በጦር መሣሪያ ወይም በተለይ አደገኛ በሆነ ሌላ ዓይነት መሣሪያ በማስፈራራት ወይም ስቃይ በሚያደርስ ሁኔታ በማንገላታት ወይም ከባድ የአካል ጉዳት በማድረስ ሲሆን ወይም ሐ በተለይ አደገኛነቱን በሚያሣይ በማናቸውም ሌላ ሁኔታ ሲሆን ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት በሚደርስ ፅኑ እሥራት ይቀጣል ጥፋተኛው ወንጀሉን የፈፀመው ወንጀል ለመፈፀም ከተደራጀ ቡድን ጋር በመሆን ወይም የጦር መሣሪያ ወይም ሌላ አደገኛ መሣሪያ በመያዝ የሕዝብ ፀጥታን አደጋ ላይ የሚጥል ወይም የተለየ ጨካኝነትን የሚያሣይ ዘዴን የተጠቀመ ወይም የተፈፀመው የኃይል ተግባር ዘላቂ የአካል ጉዳትን ወይም ሞትን ያስከተለ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የፅድሜ ልክ ፅኑ እሥራት ወይም ነገሩ እጅግ ከባድ በሆነ ጊዜ የሞት ፍርድ ለመወሰን ይችላል ቺ በጦር መሣሪያ አማካይነት በልማደኛነት በቡድን የሚፈፀም ውንብድና የሞት ቅጣትን የሚያስከትል ይሆናል አንቀጽ ድሮ ዘረፋ ማንም ሰው ዘረፋ የፈፀመ እንደሆነ በተለይም ድርጊቱ የተፈፀመው ሀ ለሕዝብ ሕይወት ለአገር ኢኮኖሚ ወይም ዕድገት ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጡ ምግቦች ስንቆች የሚታደሉ ዕቃዎች መሣሪያዎች ወይም ሌሎች ንብረቶች ላይ ሲሆን ወይም ለ በመሬት በባሕር ወይም በአየር በሚመጣ እንደመኪና አደጋ እንደ አይሮፕላን ድንገተኛ የመገደድ ማረፍ ወይም እንደመርከብ መስጠም የመሳሰሉት አደጋዎችን ምክንያት በማድረግ ሲሆን እንደነገሩ ሁኔታ ለተራ ወይም ለከባድ ውንብድና በተደነገጉት ቅጣቶች መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ድ ወይም ሮፅ አንቀጽ የወንጀል ሕግ ድ የባሕር ውንብድና ማንም ሰው በባሕር ላይ የውንብድና ተግባር የፈፀመ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከዚህ በላይ በተመለከቱት የተራ ወይም የከባድ ውንብድና ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ድ ወይም ሮፅነ አንቀጽ ሮድ ልዩ ሁኔታዎች የዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ተቃራኒ በሆነ መልኩ በጦርነት ጊዜ የውንብድና የዘረፋ ወይም የባሕር ውንብድና የሚፈጸሙ ለእነዚህ በተለይ በተወሰኑት ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣሉ አንቀጽ ሮድፎ አንቀጽ ቺ ሟ ድሮ እምነት ማጉደል ማንም ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የሌላ ሰው የሆነውንና ለአንድ ለተወሰነ አገልግሎት ወይም በአደራ የተሰጠውን ዋጋ ያለውን ነገር ወይም ጥሬ ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ለራሱ ያደረገ ወይም ለሌላ ሰው ያደረገ የወሰደ ያስወሰደ የሰወረ ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው አገልግሎት ያዋለ ወይም ይህን የመሳሰለውን ማናቸውንም አድራጐት የፈፀመ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል ተከሳሹ በእምነት እንዲሸጥ ወይም እንዲገዛ ወይም እንዲለውጥ ወይም ለተወሰነ አገልግሎት እንዲያውል የተሰጠውን ገንዘብ ወይም ዕቃ ወይም ዋጋ ያለው ነገር በተባለው መሠረት ፈጽሞ በምትኩ ያገኘው ገንዘብ ዕቃ ወይም ዋጋ ያለው ነገር የሌላ ሰው እንደሆነ ይቆጠራል ተከሳሹ ሲጠየቅ በእምነት ወይም በአደራ የተሰጠውን ዕቃ ወይም ጥሬ ገንዘብ ለመመለስ ወይም ለመክፈል ወይም ዕቃው ያለበትን ሁኔታ ለማሳየት ወይም ለተገቢው አገልግሎት ያዋለው መሆኑን ለማስረዳት ካልቻለ ንብረቱን ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም የማዋል አሳብ እንዳለው ይቆጠራል አንቀጽ ሮሄ ከባድ የእምነት ማጉደል ወንጀሉ የተፈፀመው በመንግሥት ወይም በሕዝባዊ ድርጅት ንብረት ላይ ከሆነ ወይም ወንጀሉን የፈፀመው የመንግሥት ባለሥልጣን ወይም ሹም ወይም የሕዝብ ባለአደራ ወይም ተመራጭ እንደሆነ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት የሚደርስ ኑ እሥራት እና ከብር አንድ መቶ ሺህ የማይበልጥ መቀጮ ይሆናል የወንጀል ሕግ ወንጀሉ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት ወይም ከአስራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት የሚያስቀጣው ሀ ወንጀሉን የፈፀመው ሞግዚት ወይም ንብረት ጠባቂ ሒሳብ አጣሪየሕግ ወይም የገንዘብ አማካሪ ወኪል ጠበቃ የንብረት አስተዳዳሪ ወይም በሥራው ወይም በተሰጠው ኃላፊነት ምክንያት ንብረቱ በእጁ የገባ ማንኛውም ሌላ ሰው እንደሆነ ወይም ለ ተከሳሹ በእምነት በተቀበለው ሰነድ ላይ ሰጪውን ባለዕዳ የሚያደርግ ግዴታ አስመስሎ በመጻፍ ወይም የገንዘብ መቀበያ ሰነድ በማስመሰል ወይም በፈራሚው ንብረት ላይ ጉዳት በሚያደርስ በማናቸውም ሌላ አይነት አድራጐት ሠርቶበት እንደሆነ ወይም ሐ ወንጀሉን የፈፀመው ስለገንዘብ መሰብሰብ ለሕዝብ ጥሪ የሚያደርግ ሰው ሆኖ ለራሱ ወይም ለአንድ የንግድ ማህበር ወይም ለባንክ ወይም ለሌላ ድርጅት ጥቅም ሲል ገንዘብ ወይም ዋጋ ያላቸውን ነገሮች የሚሰበስብ ሰው እንደሆነ ነው አንቀጽ ድሮኗ በመንግሥት ወይም በሕዝብ ንብረት ያለአግባብ መገልገል ወይም ማባከን ሙ ማንም ሰው አስቦ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌሳ ሰው ለማስገኘት ሳይሆን ሀ በመንግሥት ወይም በሕዝብ ንብረት ያለአግባብ የተገለገለ ያዋሰ የሸጠ ለሌላ ያሳለፈ የለወጠ ወይም በዋስትና ያስያዘ ወይም ለ በአደራ የተሰጡትን ወይም የተረከባቸውን ወይም በሥራው ወይም በሥልጣኑ ምክንያት ሊያዝባቸው ወይም ሊያገኛቸው የሚችለውን ማናቸውንም የመንግሥት ወይም የሕዝብ ንብረት አሳልፎ የሰጠ የጣለ ጉዳት እንዲደርስባቸው ያደረገ ያባከነ ወይም ያበላሸ እንደሆነ እንደነገሩ ከባድነት ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ድርጊቱ በቸልተኛነት የተፈፀመ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ይሆናል አንቀጽ ሮቿ በሌላ ሰው ሀብት ያለአግባብ መገልገል ማንም ሰው ራሱን ወይም ሌላውን ሰው ያለአግባብ ለማበልፀግ በማሰብ ሳይሆን የንብረቱ ባለቤት በመብቱ እንዳይጠቀምበት ለማድረግ ለማታለል ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ለጊዜው መጠቀሚያ ለማድረግ የሌላውን ሰው ንብረት የወሰደ እንደሆነ የወንጀል ሕግ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ነገሩ ከባድ በ አንቀጽ አንቀጽ ቺ አንቀጽ ሙ ቺ ሆነ ጊዜ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ድህ አግኝቶ መደበቅ ማንም ሰው የማይገባውን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ሀ የሌላ ሰው ንብረት ሆኖ በስህተት ባልታሰበ ድንገተኛ አጋጣሚ ነገር እንደ ውሀ ማዕበልና እንደነፋስ ባለ በተፈጥሮ ጠባዩ በመጣ ኃይል ወይም ከባለሀብቱ ፈቃድ ውጭ በሆነ በማናቸውም ሌላ ዓይነት ሁኔታ ከባለቤቱ እጅ ወጥቶ በእጁ የሚገኘውን ነገር ዕቃ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያደረገ እንደሆነ ወይም ለ ንብረትነቱ የሌላ ሰው የሆነ እንስሳ ሸሽቶ በመጠጋቱ ምክንያት በእጁ ስለገባ የራሱ ያደረገው እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል። ሦጻ ሎጻ የወንጀል ሕግ በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብና በወንጀሉ መርዳት ማንም ሰው በሙስና በአደንዛዥ ዕጽ ወይም መድኃኒት ዝውውር በሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ንግድ ወይም በዚህ ሕግ በአንቀጽ ማጣጠነ «ፀ ዛድ ድር እስከ ድ ድርድ ወይም በተመለከተው ወንጀል ወይም በማናቸውም ተመሣሣይ ከባድ ወንጀል አማካኝነት ያገኘውን ገንዘብ ወይም ንብረት ሕገ ወጥ አመጣጥ ሰውሮ በጥቅም ወይም በስራ ሳይ በማዋል በማዘዋወር ወይም በማስተላለፍ ሕጋዊ አስመስሎ ያቀረበ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ አስራ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራትና ከመቶ ሺህ ብር የማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ማንም ሰው በንዑስ አንቀጽ ፅ ከተመለከቱት የወንጀል ድርጊቶች በአንዱ የተገኘ መሆኑን እያወቀ ሕገወጥ የሆነን ገንዘብ ወይም ንብረት የለወጠ ያስተላለፈ የተቀበለ ይዞ የተገኘ ወይም በዚሁ ገንዘብ ወይም ንብረት የተጠቀመበት እንደሆነ ከላይ በንዑስ አንቀጽ ጳ በተመለከተው ቅጣት ይቀጣል ማንም ሰው ከላይ በንዑስ አንቀጽ ወይም የተገለፀው ወንጀል መፈፀሙን እያወቀ ወይም ለማወቅ የሚያስችለው በቂ ምክንያት እያለው አግባብ ላለው ባለስልጣን ሳያሳውቅ የቀረ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል ማንም ሰው ከላይ በንዑስ አንቀጽ እና የተገለፀውን ወንጀል በተመለከተ ፖሊስ ክትትል እያደረገ ወይም በቅርቡ ሊያደርግ መሆኑን ጥቆማ መቅረቡን ወይም በውስጥ ደንብ መሰረት ጉዳዩ ለሚመለከተው ሰራተኛ የተላለፈ መሆኑን አውቆ ወይም ጠርጥሮ በወንጀሉ ለተጠረጠረው ወይም ለሌላ ሰው መረጃ የሰጠ ወይም ወሬ ያቀበለ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት ይቀጣል ማንም ሰው ከላይ በንዑስ አንቀጽ በተገለጸው ወንጀል የተገኘ የወንጀል ፍሬ መሆኑን እያወቀ ወንጀሉን የሚፈጽመውን ሰው ለመርዳት ወይም ንብረቱ የተገኘበትን ሕገ ወጥ ምንጭ ለመደበቅ ወይም ለመሰወር በማሰብ ንብረቱ ሕጋዊ እንዲሆን ያደረገ ወይም ከአንድ ሥፍራ ወደ ሌላው ያዘዋወረ እንደሆነ ወይም ዕውነተኛ ባህሪውን ምንጩን የሚገኝበትን ቦታ ግብይቱን እንቅስቃሴውን ወይም ከንብረቱ የሚመነጭ መብትን እንዳይታወቅ ያደረገ ወይም የሠወረ እንደሆነ ከላይ በንዑስ አንቀጽ ጵጳ የተመለከተውን ቅጣት ይቀጣል የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት ከላይ ከተመለከቱት ወንጀሉች በአንዱ ተካፋይ ሲሆን ቅጣቱ የሚወሰንበት በዚህ ሕግ በአንቀጽ በተደነገገው መሠረት ነው በዚህ አንቀጽ መሰረት ከባድ ወንጀል ማለት የወንጀል ሕግ ሀ ወንጀሉ አስር ዓመት ጽኑ እስራት ወይም ከዚያ በላይ ሊያስቀጣ የሚችል ሲሆን ወይም ለ በወንጀሉ አማካይነት የተገኘው የገንዘቡ መጠን ወይም የንብረቱ ዋጋ ቢያንስ ሃምሳ ሺህ ብር ሲሆን ነው ክፍል ሁለት በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረጉ ወንጀሎች አንቀጽ በከብት መንጋ አማካይነት በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ ማንም ሰው አስቦ መብት ሳይኖረው በሌሳ ሰው መሬት ይዞታ የሚገኘውን ሣር ግጦሽ የእርሻ ስፍራም ሆነ ደን የአትክልት ቦታም ሆነ በማናቸውም ሌላ ዓይነት ሁኔታ በሚገኝ የይዞታ መሬቱ ላይ መንጋዎችን አሰማርቶ ያስጋጠ ወደዚሁ ስፍራ የወሰደ ወይም እንዲዘዋወሩ የለቀቀ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአምስት መቶ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ይቀጣል ሁኔታዎቹ ቀላል በሆኑ ጊዜ በተለይም በሚገባ ባለመጠበቅ እንደሆነ የደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ ቋቿለ አንቀጽ በሰው ንብረት ላይ ሁከት ማድረግ ማንም ሰው መብት ሳይኖረው ጥቅም ለማግኘት ሲል ሀ የሌላ ሰው ይዞታ የሆነውን መሬት ወይም ህንፃ የወረረ ወይም የያዘ እንደሆነ ወይም ለ በማናቸውም ሌላ አኳኋን የሌላ ሰው ሰላማዊ ይዞታ በሆነ መሬት ላይ ሁከት ያደረሰ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በመቀጮ ወይም በቀላል እሥራት ይቀጣል የሁከት ተግባር የተፈጸመው በኃይል ድርጊት በዛቻ ወይም በብዙ ሰዎች ተባባሪነት ወይም አደገኛ መሣሪያ በያዘ ሰው እንደሆነ በወንጀል ክስ አቅራቢነት ከአምስት ዓመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እሥራት ያስቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ በሰው ይዞታ ላይ ጉዳት ማድረስ ማንም ሰው መብት ሳይኖረው ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ሀ የሌላውን ሰው የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም ከዚያው ጋር የተያያዙትን ተንቀሳቃሽ ንብረቶች ሁኔታ የለወጠ እንደሆነ ወይም ለ የግል ወይም የሕዝብ የሆነውን የውሃዎች አወራረድ የለወጠ እንደሆነ ቢያንስ በሦስት ወር ቀላል እሥራት እና በመቀጮ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ የወሰን ምልክቶችን ከሥፍራቸው ማዛወርና ማጥፋት ማንም ሰው መብት ሳይኖረው በሌላው ሰው የንብረት መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የሌላውን ሰው የመሬት ወሰን ለመለየት የተተከለውን መከለያ ወይም ይህንን የመሳሰለውን ምልክት ከስፍራው ያነሳ ያዘዋወረ ወይም በሐሰተኛ ስፍራ የተከለ ወደ ሐሰተኛነት የለወጠ ወይም ምልክቱ እንዳይታወቅ ያጠፋ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከሦስት ወር በማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ኑ እሥራት ይቀጣል ቺ ተግባሩ የተፈፀመው ከዚህ በላይ በተመለከተው አሳብ ያልሆነ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ወር የማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም መቀጮ ይሆናል ክፍል ሦስት በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ አንቀጽ ጠቅላላ ድንጋጌዎች ማንም ሰው አስቦ የሌላ ሰው ንብረት የሆነውን ዕቃ መሣሪያ እንስሳ ዛፍ እፅዋት ሰብል የግብርና ምርት ደን ቤት የሕንጻ ስራዎች ወይም ማናቸውንም ነገር ወይም በይዞታው ሥር የሚገኘውን መሬት ያፈረሰ ወይም ዋጋ ያሳጣ ወይም እንዳያገለግል ያደረገ እንደሆነ በአንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በቀላል እሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል የወንጀል ሕግ አንቀጽ ከባድ ሁኔታ ቺ ሟ ወንጀሉ በወንጀል ክስ አቅራቢነት ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራትና በመቀጮ ሊያስቀጣ የሚችለው ሀ አድራጊው ይህን ተግባር የፈፀመው በክፋት በጠባየ ወራዳነት ወይም በተለይ ጉዳት ለማድረስ አስቦ በመነሳት ሆኖ በዚሁ ሥራው ከፍ ያለ ግምት የሚሰጠው ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም ይህ የተለየ አሳብ ባይኖረውም ተግባሩ እጅግ ከፍ ያለ ጉዳት አድርሶ እንደሆነ ወይም ለ ወንጀሉ የተፈፀመው በዛቻ በኃይል ወይም በብዙ ሰዎች ይልቁንም ሁከት የሥራ መዝጋት ወይም የሥራ ማቆም አድማ በተነሳ ጊዜ በሠራተኞች ወይም በአሠሪዎች እንደሆነ ነው አድራጊው ያወደመው ወይም ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰበት ንብረት የእምነት አምልኮ የሚደረግበት ዕቃ ታሪካዊ ሳይንሳዊ ወይም ኪነጥበባዊ የሆነ ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ፅቃ ወይም የሕዝብ የሆነና በህዝቡ ጠባቂነት በመተማመን ያለጠባቂ የሚኖር ሕንፃ ሐውልት ታሪካዊ የሆነ ሥፍራ ወይም ለሕዝብ አገልግሎት ለአገር ጥቅም አስፈላጊ ሆኖ የተተከለ የመሣሪያ ተቋም የተዘረጋ የቴሌ ወይም የመብራት ኃይል መስመር ወይም እርሻ እንደሆነ ቅጣቱ ከአስር ዓመት የማይበልጥ ኑ አስራት ወይም ነገሩ እጅግ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአሥር ዓመት እስከ ሃያ ዓመት ለመድረስ የሚችል ኑ እስራት ይሆናል ወንጀሉ የተፈጸመው ሰውን ለመግደል በአካሉ ላይ ጉዳት ለማድረስ ወይም ይዞ ለማቆየት በማስፈራራት ወይም መንግሥት የሕግ ሰውነት የተሰጠው አካልን ቡድንን ወይም ግለሰብን አንድ ነገር እንዲፈጽም ወይም ከመፈጸም እንዲቆጠብ ለማስገደድ ታስቦ በሆነ ጊዜ ከላይ በንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ቅጣት ተፈፃሚ ይሆናል አንቀጽ ቋ ከባድ ዘዴዎች አድራጊው የሌላውን ሰው ንብረት ለማፍረስ ለመጉዳት ዋጋ ለማሳጣት ወይም ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆን ለማድረግ በሕዝብ ጸጥታ ላይ አደጋ በሚያደርስ እንደ ናዳ ጎርፍ ፍንዳታ ወይም ቃጠሎ በመሳሰለ ነገር ተገልግሎ እንደሆነ ለነዚህ ጉዳዮች ከባድ ቅጣትን ለመወሰን የተደነገጉት አንቀጾች በተደራቢነት ተፈጻሚ ይሆናሉ አንቀጽ የወንጀል ሕግ ምዕራፍ ሦስት በንብረት መብቶች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ክፍል አንድ ማታለልን ያካተቱ ወንጀሎች አንቀጽ አታላይነት ማንም ሰው የማይገባ ብልጽግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ሙ አሳሳች የሆኑ ነገሮችን በመናገር የራሱን ማንነት ወይም ሁኔታ በመሰወር ወይም መግለጽ የሚገባውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት ወይም ግምት በመጠቀም በማድረግም ሆነ ባለማድረግ ሌላውን ሰው አታልሎ የራሱን ወይም የሦስተኛ ወገንን የንብረት ጥቅም የሚጐዳ አድራጐት እንዲፈፅም ያደረገው እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም እንደነገሩ ከባድነት እስከ አምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል በወስላታነት የሌላ ሰውን አገልግሎት እንደማግኘት በመሰለ አሰራር ሆኖ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት አነስተኛ የማታለል ተግባር በፈፀመ ሰው ላይ የደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች ቅጣት ይፈፀምበታል አንቀጽ ቋቿ እና ቋቷሀ አንቀጽ የሚያዝበት ገንዘብ ሳይኖር ቼክ ማውጣት ማንም ሰው ቼክ በሚወጣበት ወይም ቼኩ ለባንክ በሚቀርብበት ጊዜ የሚያዝበት በቂ ገንዘብ አለመኖሩን እያወቀ ቼክ ያወጣ የሰጠ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም እንደነገሩ ከባድነት ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራትና በመቀጮ ይቀጣል ቺ አድራጐቱ የተፈፀመው በቸልተኛነት እንደሆነ በመቀጮ ወይም ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ያስቀጣል አንቀጽ በተጭበረበረ ሁኔታ የአክሲዮን ገበያን ንግድ ማካሄድ ማንም ሰው በአክሲዮን ገበያ ወይም በሌላ ገበያ አማካይነት የአክሲዮን ወይም የአክሲዮን የገበያን ዋጋ በሚመለከት የሕዝብ አክሲዮኖች ንግድ እንዳለ የሚያስመስል ሐሰተኛ ወይም አሣሣች መልክ ለመፍጠር በማሰብ ሀ በአክሲዮን ባለቤትነት ላይ ምንም ጠቃሚ ለውጥ የማያመጣ የአክሲዮን ንግድ ያካሄደ እንደሆነ ወይም ለ አክሲዮኖቹ በተጠየቁት ተቀራራቢ መጠን ተቀራራቢ ጊዜ እና በተቀራራቢ ዋጋ በዚያው ሰው ወይም በሌላ ሰው እንደተገዛ ወይም ለዚያው ሰው ወይም ለሌላ ሰው የግዥ ጥያቄ እንደቀረበ ወይም እንደሚቀርብ እያወቀ አክሲዮኖቹን ለመግዛት ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ወይም የወንጀል ሕግ ሐ አክሲዮኖቹ በተጠየቁት ተቀራራቢ መጠን ተቀራራቢ ጊዜ እና ተቀራራቢ ዋጋ በዚያው ሰው ወይም በሌላ ሰው እንደተሸጡ ወይም ለዚያው ሰው ወይም ለሌላ ሰው የሸያጭ ጥያቄ እንደቀረበ ወይም እንደሚቀርብ እያወቀ አክስዮኖችን ለመሸጥ ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ በአክሲዮኖች ወይም በሸቀጦች መቆመር ማንም ሰው በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የተመዘገቡ ወይም ያልተመዘገቡ ኩባንያዎች ወይም የሌሎች የንግድ ድርጅቶች አክሲዮኖች ወይም ማናቸውም ዕቃዎች ወይም ሸቀጦች ዋጋቸው ዝቅ ወይም ከፍ ማለቱን ምክንያት በማድረግ ገቢ ወይም ትርፍ ለማግኘት በማሰብ አክሲዮኖቹን ወይም ዕቃዎቹን ወይም ሸቀጦቹን የራስ የማድረግ እውነተኛ ሐሳብ ሳይኖረው እነዚህን ነገሮች የሚሸጥ ወይም የሚገዛ በማስመሰል ማናቸውንም ዓይነት ውል በጽሁፍም ሆነ በቃል ያዘጋጀ ወይም የፈረመ እንደሆነ በቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ይቀጣል አንቀጽ ከባድ አታላይነት ከባድ የአታላይነት ወንጀል ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና እስከ ብር ሃምሣ ሺህ በማይበልጥ መቀጮ የሚያስቀጣው ሀ ጥፋተኛው በአንቀጽ ያድ እና ሀ በተገለፀው መሠረት እምነት በሚጣልበት የሥራ ደረጃ ወይም ኃላፊነት ላይ የሚገኝ እንደሆነ ወይም ለ አድራጊው የማህበር የባንክ የንግድ የአክሲዮን ገበያ ወይም የኢንዱስትሪ መሥሪያ ቤት አክሲዮን የዕዳ ሰነድ የቦንድ ወይም ማናቸውንም የዋስትና ሰነድ በማውጣት ከሕዝብ ገንዘብ ለመሰብሰብ ጥሪ ያደረገ ወይም ለራሱ ወይም ለድርጅቱ ወይም አድራጊው የአክሲዮን ባለድርሻ ለሆነበት ድርጅት የሸጠ እንደሆነ ወይም ሐ ወንጀሉ የተፈፀመው በሕዝብ አስተዳደር ወይም በሕዝብ አገልግሎት ላይ እንደሆነ ነው የወንጀል ሕግ አንቀጽ ሌሎች ወንጀሎች ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩት ወንጀሎች በቀር ስለአክሲዮኖች ስለዕቃ ሰነዶች ስለቦንዶች ወይም ስለማናቸውም የዋስትና ሰነዶች በሚወጡ አዋጆች ወይም ደንቦች ላይ የተደነገገ ወንጀል ሲኖር ሌላ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በቀር በቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ እንደሆነ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እሥራት ያስቀጣል አንቀጽ ኢንሹራንስ በሚመለከት የሚፈጸም የአታላይነት ድርጊት ፅ ማንም ሰው የማይገባ ብልፅግናን ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ቺ ሀ ኢንሹራንስ የተገባበትን አደጋ በመፍጠር ወይም ለ በውሉ ውስጥ በተገለፀው ጥቅም ሳላይ ተጽዕኖ በሚያደርግ አኳኋን የኢንሹ ራንሱን ገንዘብ ልክ የውሉን ዘመን ወይም የኢንሹራንሱ ተጠቃሚዎችን የሚመለከት ፍሬነገር በመደበቅ በማሳሳት በማረጋገጥ ወይም ይህንኑ በሚመለከት ሐሰተኛ መግለጫ በመስጠት አንድ የኢንሹራንስ ማህበርን ያታለለ እንደሆነ ወይም ሐ በማናቸውም ሌሳ መንገድ ከኢንሹራንስ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የአታላይነት ድርጊት የፈጸመ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም ሁኔታዎቹ በይበልጥ ከባድ ሲሆኑ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራትና ከብር ሃምሣ ሺህ በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል ወንጀሉን የፈጸመው የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት እንደሆነ በዚህ ሕግ በአንቀጽ መሠረት ይቀጣል አንቀጽ ሀ በሐሰተኛ ሰነድ ማታለል አንቀ ማናቸውም ዓይነት የማታለል ተግባር የተፈፀመው ወደ ሐሰተኛነት በተለወጠ ሰነድ አማካይነት ሲሆን አግባብ ያላቸው ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈጻሚ ይሆናሉ በሕዝብ እምነት በመጠቀም ማታለል ማንም ሰው ለራሱ ብልጽግናን ለማግኘት አስቦ መንፈስን እጠራልሃለሁ ጋኔን እስብልሃለሁ ደንቃራ እጥልልሃለሁ እጠነቁልልሃለሁ ዕድልህን እነግርሃለሁ ነገርህን እገልጽልሃለሁ ኮከብህን እቆጥርልሃለሁ ሕልምህን እፈታልሃለሁ የወደፊት ዕድልህን አውቅልሃለሁ ውስጥ እጅህን አነብልሃለሁ ከሞተ ሰው ጋር አነጋግርሃለሁ በማለት ወይም በሰው እምነት ያለአግባብ መገልገል በሚያስችል በማናቸውም ሌላ መንገድ ሌላውን ሰው ያታለለ እንደሆነ የወንጀል ሕግ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት አፈጻጸሙ በደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች የሚያስቀጣው ካልሆነ በቀር አንቀጽ ቿ በመቀጮ ወይም የተደጋገመ ወንጀል በፈፀመ ጊዜ በቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት ይቀጣል የአታላይነት ተግባር የተፈፀመው በአንቀጽ በተመለከተው ዓይነት ከሆነ በዚሁ በተጠቀሰው ሕግ የተደነገገው ቅጣት ተፈፃሚ ይሆናል አንቀጽ ሌሎች የማታለል ድርጊቶች ማንም ሰው ከባድ በሽታ ወይም ጉደለት አለብኝ ወይም ከፍተኛ አካላዊ ወይም ሟ ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact