Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የ እምነቴ ፈተና(ደበበ እሸቱ)trial-5.pdf


  • word cloud

የ እምነቴ ፈተና(ደበበ እሸቱ)trial-5.pdf
  • Extraction Summary

ለተባለው ጥያቄ ሲመልስ ይህን ውሳኔ በተመለከተ «አቃቤህግ» ሽመልስ ከጀርመን ፌ አኛም በጣም ገርሞናል አይከላከሉም ብለን ከልገመትንም ውሳኔው አስገርሞናል » ነበር ያለው ወዲያው በስልክ ይሁን በገጽ ተጠርቶ «ምን ማለትህ ነው። በማለት ግራ ያጋባቸውና እንዲያውም አንዳንዶቻችንን መርጦ እነዚህ ሌላ ቀጠሮ እንዳይሰጣቸው ብሉ ይወስናል ፃኪሞቹም ነርሶቹም ድሬሰሮቹም ሁሉም አሱን ለመገላገል ሲሉ ያላቸውን ይፈጽማሉ ለነገሩ እምቢ መታከም አለባቸው ቢሉም ከሱ ግልምጫና ቁጣ ባሻገር ወህኪ ቤት ባለው ተሰሚነት ህክምናውን ያቋርጠዋል ይህን ደሞ ደርሶብኝ አይቼዋለሁ ይህ ባለፈው ያጋጠመኝ ነው በተደጋጋሚ አሁን ደሞ የባሰ አጋጠመኝ ሁላችንም ከተሳፈርን በኋላ ከወህኒ ቤቱ ግቢ ወጥተን በቀለበት መንገድ ወደ ሆስፒታል በመሄድ ላይ ነበርን በቀኝ ሊያልፍ ሲሞክር እኛ ያለንበት መኪና ውስጥ ዋለ የማነ ከኔ ጋር ፊዚዮቴራፒ ክፍል ሲመጣም በጣም ለመንኩት ጉዳዩ ከቻይናዊው ሰው ጋርም ሊያስከትል የሚችለውን ቅሬታ በተመለከተ ለማስረዳትና ለሾፌሩ ይቅርታ ለማስገኘት ሞክሬ ተቀባይነት አላገኘሁም ህክምናችንን ጨርሰን ወደ ወህኒ ለመመለስ ስንሰባሰብ እንደገና ልመና ጀመርን በየተራ ሾፌሩም እራሱ ለመነገመጨረሻው ላይ የማነ ሾፌሩን መታወቂያውን አምጣ አሰውና አይቶ ሲያበቃ በጣም በለሰለሰ አንደበት ለምን ቀስ ብለህ ረጋ ብለህ አትነዳም አኛንም አደጋ ልታደርስብን ትችል ነበርበማለት ያ ሁሉ ቁጣ ብስጭት ቀረ ይህን ሁኔታ በመጠቀም እንደገና ለመንኩት ምን አንዳቀዘቀዘው ባላውቅም ቀዝቅኳልናጸበመጨረሻውም መኪናው ቆሞበት በነበረው ቦታ ስንደርስ መኪናውም ቻይናዊውም የሉምየማነ የሾፌሩን መሥሪያ ቤት ሲጠይቀው ከቆርኪና ጣሳ ፋብሪካ ፊት ለፊት መሆኑን ነግሮት እዚያ ስንደርስ ሾፌሩን መንጃ ፈቃዱንና መታወቂያውን መልሶለት አሰናበተውሾፌሩ በወህኒ ቤት እያለሁ ሁለት ጊዜ ፍራፍሬ ይዞ መጥቶ ጠይቆኛል የማነ ለምን ከቁጣው ባንድ ጊዜ መታወቂያውን ሲያይ አንደተለወጠ የገባኝ ሲጠይቀኝ ባገኘሁት መረጃ ነው ለካ ሾፌሩ የአድዋ ልጅ ነበር የማነ ከዚህ የባሰም ሲያደርግ ባየው አይደንቀኝምአንዳንድ ጊዜ ወደኛ ዞን ይመጣና ማንንም ሳያናግር የዞንን አስተዳደር ሳይጠይቅ ወይም የዞን ፃለፊውን ሳይዝ ዝም ብሎ መጥቶ በየክፍሉ ገብቶ ተሸከርክሮ ይወጣልፍተሻ በሚኖርበትም ጊዜ የተለየ ሁኔታ አይበታለሁና ጠባዩ አንዲሁ ነው ብዬ ማመን ይቸግረኛ ል ቅንጅት ስደት ላይ አይደለም አሳይለምም አልጠየቀም ስለዚህም ቤቱ ሃገሩ ነውና ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል እንደሊቀመንበር መጠየቅመጠየቅም ካለባቸው ወደ ፃገር ገብተው በስልጣን ወንበራቸው ተቀምጠው ጉዳያቸውን ለላአላይ ምክር ቤቱ አቅርበው በሚሰጠው ውሳኔ እንጂ መተዳደርያ ደንባችን ሊቀ መንበሩ አንዳሻቸው ይፈልጣሉ ይቆርጣሉ አይልምእኛ ደሞ ከቅንጅት ደንባችን ውጪ ንቅንቅ የምንል አይደለንምከማንም በላይ ቅንጅት ነውፊከምንም በፊት ቅንጅት ነውስለዚህም ለቅንጅት መተዳደርያ ደንብና ማኒፌስቶ ሲቀበል ያንን በተግባር ሊተረጉምና ለሱም ተገዢ ሊሆን ቃል ገብቶ ነው ያውም የማይታጠፍ ቃል ሕዝብን ከአኔ አውቅልዛለሁ የሞኝ ቋንቋ አላቆ እራሱ ለራሱ የሚያውቅ መሆኑን አምኖና ተቀብሎ ነው አባልም የሆነውወደ አመራርነትም የወጣውያን ሲያጥፍ ነገር ተበላሸ ማለት ያን ጊዜ ነው ለመምረጥ ሲልለቅንጅት የተንከራተተልንን የተወገዘልንን ሲልየተጎሳቆለልንን የተፈናቀለልንን የሞተልንን ክቡር የሆነውንና በቃሉ የጸናውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ነውመናቅ የተጀመረው በመተዳደርያ ደንቡ ላይ የሌለውን ጨርሶ ያልተባለውን ተብሏል ብሉ ሕዝብን ለማታለል መሞከር ምን መሆን ነው።

  • Cosine Similarity

ማንነቱ ሳይታወቅ ያውም ዳንኤልን የሚያህል ሕግን አብጠርጥሮ የሚያውቅ እንዲህ አይነቱን ተግባር በዚህ መልክ ፈጸመ ተብሎ ቢወራ ማመን አይቻልም ስለሕግና ፖለቲካ ምንነት ምንም የማያውቅ ሰው አንኳን ቢሆን እንዲህ አይነቱን የድብቅ ሥራ በዚህ መልኩ አያከናውንም ፍርድ ቤቱም ይህን እውነት ብሎ ይቀበለዋል የሚል አምነት ቀርቶ ጥርጣሬ ባይኖረኝም ከሂደቱ እንደተረዳሁት በዚህ ፍርድ ቤት የማይቻል ምንም ነገር የለም ከአቃቢያኑ አንድ ለታዛቢነት የተተመጠ አለ ከዳኞችም እንዲሁ ለታዛቢነት የተመደበው የግራ ዳኛው ይመስላል አንዳንድ ጊዜ የመፃልና የቀኝ ዳኞች ጭርሱን የግራውን አርግፍ አድርገው አስከመኖሩም ይረሱታል አልፎ አልፎ ትዝ ሲላቸው ድንገት ዳኛ አዲል ዘወር ብለው ያወሩታል የግራ ዳኛው ጆሮ ግንዱን ደግፎ ሲቀመጥ ሁለቱ የቅንጅት የምርጫ ጣቶች ቅርጻቸውን ሰርተው ስለሚታዩ በምልክት ክልክል መሆኑን ለመንገር አንሞክራለን አሱም አንዳንድ ጊዜ ያየናል መሰለኝ ቶሎ ብድግ አድርጎ አቀማመጡን ይለውጣል ችሎቱ ለምሳ አረፍት ካደረገ በኋላ ከቀትር በኋላ ቀጥሎ ተከታዩ ምስክር በአቶ በድሩ አደም ሳይ የሚመሰክረው ቀረበ መስካሪው ተከሳሾች የተያዝንበትን ቀን ጨርሶ የሚያውቅ አይደለም መስክር ያሉትም ይህንን ያውቀዋል በሚል እምነት አላስጠኑትም ሲመሰክር መርካቶ በሚገኘው ቀበሌ ስብሰባ ተጠርተን ፄደን ነበር እኔም እዚያ ነበርኩ አቶ በድሩ አደም አዳራሹ በድንጋይ እንዲደበደብ ሲያነሳሱ ነበር መስታወቱ ሲሰበር ሁሉ እቪያው ነበሩ በማለት የምስክርነት ቃል ሰጠ የመስቀልኛ ጥያቄ እድሉ ሲገኝ አቶ በድሩ ምስክሩን ይህ ሁኔታ የተከናወነው መቼ ነበር። የምስክር ማሰማቱ በተለያዩ ቀጠሮዎች ሲካሄድ ከቆየ በኋላ አቃቤ ሕግ የምስክሮቹን ቁጥር ቀንሻለሁ ነገር ግን አዲስ ምስክሮች ለክሱ በጣም አስፈላጊና ዋና ሊባሉ የሚችሉ ምስክሮች ስለሆኑ ይፈቀድልኝ አለ ተከሳሾች ክቡር ፍርድ ቤት ማስረጃ አቅርቤ ጨርሻለሁ ያለው አቃቤ ሕግ አሁን አዲስ ላቅርብ ማለቱ አግባብነት የሌለው ስለሆነ አይፈቀድብን በማለት ብናመለክትም ዳኛው አብዛኛዎቹን ምስክሮች አስቀርቶ መጠየቁ ለፍርድ ሂደቱ መፋጠን ያለውን ፈቃደኝነት ስለሚያሳይ አቃቤ ሕግ የጠየቀው ተፈቅዶለታል አሉ በቪህም መሰረት በ ሰአት ላይ በዋለው ችሎት በጣም ልዩ የሆነውንና አውነትን የመሰከረውን የአቃቤ ሕግ ምስክር እንመልከት ምስክሩ ቀደም ባሉት በተለይ ሽሮ ሜዳን በተመለከት በቀረቡት የአቃቤ ሕግ ምስክሮች ሽጉጡን ተቀምቶ በገጀራ ጭንቅላቱን ተመቶ ከፍተኛ ጉዳት ደረሶበታል ደሙ እንደጎርፍ ይፈስ ነበር በአናቱ ደሙ ሲንተከተክ ይታይ ነበር የተባለው ምስክር ነው ኑር ሁሴን ከሞት ተነስቶ እንደመጣ ነው የተቀበልነው አንዱ ምስክር ሞተ ካለ በኋላ ትዝ ብሎት ነው አልሞተም ያለው ያውም በመስቀልኛ ጥያቄ ላይ ኑር ሁሴን አድሪስ ልብስ ሰፊ የሸሬ ተወላጅ ለ ዓመታት ሽሮ ሜዳ ነዋሪ ነኝ በ ሽሬ ፄድኩ ካለ በኋላ ጭንቅላቴን ያመኛል ብሎ ማልቀስ ጀመረ ፍርድ ቤቱም አይዞህ ተረጋጋ ብሎ ማባባል ያዘ። አክሱም ጽዮን ደብረ ዳሞና ደብረ ቢዘን በያሬድ ዝማሬ ይጸልዩልናል አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ስደዶሙ ለአጋንንት ስደዶሙ እግዚኦ እምየማንነ ወእምዳግም ወእምዛቲ መካንነ ይርፃቁ እም ለአለ ይፀልእዋ ለነፍስየ «አጋንንትን የምታባርሩ አብወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከቀኛችንም ከግራችንም ከዚች ከቤታችንም ኢትዮጵያ ነፍሳችንን የሚጠሉትን ሁሉ አርቅልን ኛ የእውነት መዝገቧን በግራ እጂ የነጻነት ብአሩን በቀኝ አጁ ይዞ ታሪክ ይመዘግባል የክሳሸና የከሳሽ ጠበቃን ዓላማ የዛሰት ድር የአስረኞችንና የቤተሰቦቻቸውንም መጉላላት የዳኞቹን ጭንቀትና ፍርድ የኢትዮጵያን ሕዝብ ፃዘንና ጸሎት የዓለም አቀፉን ኡኡታና ተቃውሞ በመልክ በመልኩ እያነጠረ ለሚቀጥሉት ትውልዶች ለማስተላለፍ ይመዘግባል እያንዳንዳችን በታሪክ ፍርድ ነጻ የምንወጣውና ወይም የሚፈረድብን የልጅ ልጆቻችንን አክብሮት የምናገኘው ወይም የምናጣው በዛሬው ሥራችን ነው እንግዲህ ለፍርድ ቤቱ ያለኝ ክብር አነዚህን በአጭሩ የገለጽኳቸውን ሃይሎች ሁሉ በአንድ ላይ በማጠቃለል ነው ፍርድ ቤቱ ውስጥ ክሳሾችን ከበው የሚታዩ ጠመንጃ የያዙ ወታደሮች ለፍርድ ቤቱ ያለኝን ክብር አንደሚፈታተኑት አይካድም ከዚያ በላይ የከሳሽ ጠበቃ ያቀረበውን የክስ ድሪቶ በመቀበል የዋስትና መብት ለተከሳሾች መነፈጉ ያሳዝናል በዚህ ምክንያት እያንዳንዱ ተከሳሸ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ከሥራ ውጭ ሆኗልፅፁ ቤተሰቦቹ ብቻ ሳይሆኑ አገሪቱም ተጎድታለች አንድ ሺህ ያህል ሰዎች ለአንድ ዓመት ተኩል ከሥራ ውጪ ሲሆኑ አገሪቱ አንድ ሺህ አምስት መቶ የሥራ አመታት አጣች ማለት ነው ሁለተኛውን ሺህ የክርስትና ዘመን ሚሌኒየም እናከብራለን ብሎ በሰፊው በመደገስ ላይ ላላ ደሃ ሀገር አንድ ሺህ አምስት መዯ ፈሥራ ዓመታት ማጣት የሚያሳዝን ባይሆን ኖሮ ከ ምርጫ ጋር በተያያዘ የታሰርንበት የአንድ ዓመት ተኩል የግፍ እስር ከሌሎች እስረኞች ጋር ሲነጻጸር ኢምንት ነው ወጣቶችና ሽማግሌዎች ከአምስት አመታት እስከ አስር ዓመታት ያለፍርድ በቀጠሮ የሚመላለሱ ሞልተዋልእንደዚህ ያለው ግፍ በብዙ ሺህ ስዎች ላይ የሚፈጸም ነው ይባስ ብሎም የተፈረደባቸው ጊዜያቸውን ሲጨርሱና አንዳንዶቹንም ፍርድ ቤት ነጻ ሲሳቸው ለሳምንታትና ለወራት እንደታሰሩ የሚቆዩ ሞልተዋል በእኛ አንድ ዓመት ተኩል ከአስር ቤት ወደ ፍርድ ቤት መመላለስ የታዘብሁት የክሳሽ ጠበቃ ምን ያህል በሕግ የመጫወት ሥልጣን አንዳለው ነውየቪድዮ ክምር በማስረጃነት ያቀርባልቅንጣት ታህል እውነት ያለባቸው ቢሆን በጣም ጥቂቶች ይሆኑ ነበርከዚያም በላይ እያንዳንዱ ቪዲዮ ከመታየቱ በፊት የከሳሽ ጠበቃ የምታዩትን አትመኑ እኔ የምነግራችሁን ተቀበሉ የሚል አሰልቺሐሰት ጊዜ ከመፍጀት በቀር ምንም ዋጋ አልነበረውምፎማስረጃ ተብሎ የቀረበው የሚለውና የከሳሽ ጠበቃ የሚናገረው የሰማይና የመሬት ያህል የተራራቁና ተቃራኒዎች ናቸውከዚያም በላይ የቪዲዮውና የምስክሮቹ ብዛት የሚያስገርም ነውሁሉም ፍሬ የሌለውና መሳቂያ በመሆኑ ያስመዘገበውን ቁጥር በጣም ለመቀነስ ተገደደ አብዛኛ ው የሰነድ ማስረጃ የተባለው የሚያስቅ ነውበበኩሌ እንኳን ማስረጃዎች የተባሉትን ክሶቹንም አላነበብኋቸውም የክሳሽ ጠበቃ ክሶቹን ሲያነብ ስሰማው የትግሬን ዘር ማጥፋትን» ሲያነሳ ደንግጩ ደነዘዝሁ ይህንን ጽሁፍ የምደመድመውም በዚህ የሚያቅለሸልሸኝ ክስ ነው የትግሬ ዘር ጭራቅ እንደተነሳበት ለመገመት አያዳግትም ዕፅሰትራሠ ይሳ። አምባገነኖች ሕዝብን እንደባሪያ እነሱ እንደቅኝ ገዢዎች የሚጠቀሙበት ዋነኛ መንገድ የህዝብን ሕሊና ፍርፃት ውስጥ በመጨመር ነውር በቅድሚያ የሚያስቡለት የሚቆረቆሩለት በመምሰል ትናንሽ ጥቅሞቹን እያከበሩ ሕብረተሰቡ በነዛ ጥቃቅን ጥቅሞች ላይ ተመስርቶ ብዙ እንዲጠብቅ ካደረጉት በኋላ እነሱ የሚቻላቸውን ያህል ጉዳት ያደርሳሉ ለምን ብሎ የሚነሳን ዛኝይል በማሰር በመግደል ቤተሰቡን በመበተን ለሌላው ትምህርት እንዲሆን ያደርጋሉ ይህን የተመለከተ ሕብረተሰብ ደሞ ትንሽ ትንሽ መፍራት ይጀምራል ያን ጊዜ አምባገነኖች ትንሹ ፍርፃት ላይ በመንጠልጠል ትላልቅ ፍርፃቶች ይፈጥራሉ ለዚህ የሚሆናቸውንም መሳሪያ በገፍ ያዘጋጃሉ መሣሪያዎቹ የደህንነት ዛይል ወህኒ ቤት በየቦታው በገፍ የማሰር መብት ለተወሰኑ የቡድን አባላት መስጠት የፍትህን ሂደት ለራስ በሚጠቅም መልኩ ማዋቀር በፖሊስ ኃይሉ ውስጥ የራስ የሆኑ ወሳኞች ማስቀመጥ የሌለ ቀውስ ያለ በማስመሰል አዳዲስ ህጎችና ደንቦች በሕዝቡ ላይ ማውጣትና መተግበር የመሳሰሉት ሁሉ ተዳምረው ሕዝቡ መብቱን አንዳይጠይቅ አፍነው ይይዙታል ፈሪ ይሆናል በየአቅጣጫው ጥቂት ጥቂት ፈሪዎች በመፍጠር አጠቃላዩን ሕብረተሰብ ፈሪ ያደርጋል አምባገነኖች የፈሪ ሕብረተሰብ መፈልፈያ ፋብሪካዎች እስኪሆኑ ይህንኑ ተግባር ይቀጥላሉ ግድያውን ጫን ኑሮውን ወደድ ከማድረጉ ባሻገር እስራቱን በገፍ ያካሂዳሉ ሕዝብም የሚያደርገው ሲጠፋው የባሰ አታምጣ አያለ ከሁሉም በከፋውና በባሰው ላይ ሆኖ የባሰ አንዳይመጣ ይጸልያል ወደፈጣሪው አቤቱ የባሰ አታምጣብኝ ማለትን አማራጭ የሌለው መፍትሔ ያደርገዋል በፃገራችን በሁሉም መስክ የታየው ይፄው ነው ሕዝቡ ግን ፈርቶ ስለበቃውና ከዚህ የባሰም እንደሌለ በመረዳቱ የመጣው ይምጣ እንጂ ከእንግዲህስ በፍርፃት መብቴን አላስነካም ብሎ ታጥቆ የተነሳው አቃቤ ሕግ ደግሞ ይህን ውሳኔ ለማስለወጥ ነው የቅንጅትን አመራሮች ነጻውን ፕሬስና የሲቪክ ማሕበራት መሪዎች ለሞት ፍርድ የተመኛቸው ሕዝቡ መሪ ሲያጣ አርፎ ይገዛል አይነት አካሄድ ነው ሕዝቡ ግን በቃኝ ማለት በቃኝ ነው ብሎ አሻፈረኝ አለ ለመሪዎቹ መፈታት ተሟገተለፍትህ ሉአላዊነት ጥብቅና ቆመ በዛገራችን ታሪክ ታይተው የማይታወቁ አዲስ ባህል ተብለው የሚጠቀሱ ጉዳዮች አሉ የመጀመሪያውና አስገራሚው በግንቦት ቀን የተካሄደውን ምርጫ በተመለከተ ሕዝቡ አንዲት ድምጽ ያላትን ዋጋ በመረዳት ለዚያች ድምጽ የሰጠው ዋጋና ያገኘው ውጤት ነው ሁለተኛው አንዲት የምርጫ ካርድ አንግዛህ ላሉት መሸጥና በድጎማ ተታለህ እኛን ምረጥ ሲባል ያን ከማደርግ ሞቴን እመርጣለሁ በማለት በድምጹ ላይ የወሰደው ቆራጥ አቋም ነው ሌላው ከምርጫ በኋላ በተፈጠረው የካርድ ዝርፊያና ጉልበተኝነት ላይ ሕዝቡ የወሰደው ውሳኔ ነው በዚህ ውሳኔው የዴሞክራሲ ጠበቃ ተሟጋች በመሆን የተፈለገው ጦር ቢመዘዝ የመብታችን ጉዳይ ነውና ነጻነታችንን አሳልፈን አንሰጥም በማለት ለዴሞክራሲ የቆመበት የጥቅምት አዲስ ክስተት ነው አባቶች ሲተርቱ «በጥቅምት አንድ እሸት» ይባል ነበር በዘመነ ኢህአዴግ በቱ ጥቅምት ግን «በጥቅምት እስራት» ነው የተባለለት እንደ አውነቱ ከሆነ ወህኒ ቤት መግባት መጥፎ ነው መጥፎነቱ የአንድ ሰው ነጻነት ሰብአዊ መብት ዴሞክራሲ ሙልጭ ብሎ ጠፍቶ እንደ ከብት ያውም ሊሰለጥን እንደማይችል ከብት የሚነጠቅበት ቦታ ነው እያንዳንዱ የዞን ፃላፊ አልጋወራሽ ነው ለዚያ ላለበት ዞን ለምን ንጉሥ አልሆነም ቢባል ንጉሶቹ ከሱ በላይ በቢሮ ተቀምጠው በየጊዜው ከዞን ፃላፊው ሪፖርቱን እየተቀበሉ አስረኛው ምን ይደረግ ብለው የሚወስኑት ስለሆኑ ነው አኔ ብዙ የዞን ሃላፊዎች አይቻለሁ አንዳንድ የዞን ፃላፊዎች በእውነት የከብት ጠባይ ያላቸው ናቸው አንዳንዶቹ አስረኛ ማለት እቃ የሚመስላቸው አሉ እስረኛ አድርግ የተባለውን ብቻ የሚያደርግ ራሱ ሕልውና የሌለው አድርገው ያዩታል አዋቂ በሆኑት ስለሚቀኑና የበታችነት ስለሚሰማቸው አሱን ለማዋረድ ይቸኩላሉ በመጨረሻው ግን ተዋርደው የሚቀሉት አነሱ ናቸው በወህኒ ቤት ዓመት ታስሮ ገና ውሳኔ ያላገኘ ብዙ ነውፎ ዓመትና ክዚያም በላይ ታስሮ ፍርድ ቤት ጨርሶ ያልቀረበም በሽ ነው ዓመት ዓመት ታስሮ ፍርድ ቤት ቀርቦ ነጻ የሚባልም በርካታ ነው ያም ሆኖ ተመስገን ብሎ ታሳሪ ጓደኞቹም እንኳን ደስ አለህ ብለው ይጋብዙታል ይሸኙታል አንዳንዱ ዓመት ታስሮ ነጻ ተብሎ እንደገና መፈቻ ስላልመጣለት ወይም በሌላ ምክንያት በትንሹ ሳምንት የሚቆየው ከምንም በላይ ያሳዝናል በአስገድዶ መድፈር ተከሰው በወህኒ ቤት ያሉ በርካቶች ቢሆኑም የአንድ ሁለት ተከሳሾች እንቆቅልሽ ሆኖብኛል አንዱ የአይነስውሩ የአሸናፊ ጉዳይ ነውቤቱ ወደ ላፍቶ ገደማ ሲሆን አስገድዶ ደፈረ የተባለው ደሞ አውቶቡስ ተራ አልቤርጎ ውስጥ ነው ኦልለቤርጎ ለመያዝ ማወቅን ይጠይቃል ተደፈሪዋም ከሰፈሯ አውቶቡስ ተራ ድረስ ስትሄድ ተገዳ ከሆነ በየመንገዱ ላይ ያለው ሰው ሁሉ ጉዳዩን ስለሚያይ ብትጮህ የሚደርስላት አታጣም አልቤርጎውንም ሲይዙ በስምምነት ካልሆነ በስተቀር ለገንዘብ ተቀባዩ ወይም ለአልጋው ክፍል ብትናገር ሊያድኗት ይችሉ ነበር አሸናፊ ሴትዮዋ በስምምነት አብራው ታክሲ አስቁማ ከፍላ ሰው አንዳያይ ብላ ራቅ አርጋ ወስዳው ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ በሌላ ጉዳይ በተፈጠረ አለመግባባት ነው ክስ የተጀመረው ከዛም ተሰሚነት ስላላት አሳሰረችኝ ነው ያለው ሌላው የተሰማ ጉዳይ ነው ተሰማ በቦምብ ወገቡን ተመቶ በሁለት ዱላ በመከራ የሚራመድና ከወገቡ በታች ሰውነቱ የማይሠራ ሮጳሷ የሆነ የአካል ጉዳተኛ ነው እንደነገረኝ የሚኖረው በእናቱ ቤት ከእህቱ ጋር ሲሆን አህቱ ባል ስታገባ ቤቱን ልቀቅልኝ ትለዋለች ተሰማም አንዴት አድርጌ ከኔ ይልቅ አንቺ ትሻያለሽ እኔ ወዴት አፄዳለሁ ብሎ አይሆንም ይላል በዚህ ጊዜ ቤቱን ማስለቀቂያ ዘዴ ተፈልጎ አስገድዶ መድፈር ክስ ተመሰረተብኝ ያውም የእህቴን ልጅ ለመሆኑ በምን አቅሜ። ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ችግር በሕንድ ተክስቶ የሕንድ የፍትህ አካላት ችግሩን ከተመለከቱ በኋላ አንድ ውሳኔ አሳልፈው ችግሩን አቁመውታል በሕንድ አንድ ሰው ሚስት አጭቶ ሲያገባ ከሚስት ቤተሰብ ጠቀም ያለ ጥሎሽ ይከፈላል ይህ እውነት የሆነ ጉዳይ ነው ታዲያ የሕንድ ጎረምሳ ሁሉ ያገባና ሚስቱ የምታስገኝለትን ዳዋሪ በርከት አድርጎ ከበላ በኋላ ወዲያው ሚስቱ ትሞታለች ባል ገንዘቡን ተቀብሏል ሚስት ሞታለች ስለዚህ አንድ ስድስት ወራት ይቆይና ደሞ ከሌላ መንደር ሌላ ያገባል እንደገና ጠቀም ያለ ጥሎሽ ይበላል በዚህ አይነት እስከ አራት አምስት ሚስት የሚያገቡና ከበርቴ የሚሆኑ ስለበዙ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ይፄድና ሲጣራ ሚስጥሩ ይወጣና ባል ገዳይ መሆኑ ይታወቃል ስለዚህም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማስታገስና መልክ ለማስያዝ አንድ ባልና ሚስት ከተጋቡ በኅላ አምስት አመት ሳይሞላ ሚስት ከበሽታ ውጪ ሞታ ብትገኝ ባል ተጠያቂ አንዲሆንና የወሰደውን ጥሎሽ እንዲከፍል ህግ በመውጣቱ ጉዳዩ እልባት አገኘ የኛም አስገድዶ መድፈር ማጣራትን የሚጠይቅ ሊሆን ይገባል አለበለዚያ የቂም በቀል መወጫ የልዩ ፍላጎት ማሟያ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል እያንዳንዱ ታሳሪ የገባበት ቀን እንደመለያየቱ ወንጀሉም እንዲሁ ይለያያል የየታሳሪውም ጠባይ እንዲሁ ነው አንዳንዱ እስረኛ በዞን ፃላፊዎች የሚወደድ የአስራት ዘመኑ የሚቀነስለት ይመስለውና የሆነ ያልሆነውን ፈጥሮ በሬ ወለደ አይነት ወሬ ያቀርባል በኛ ዞን በሚስታቸው ጡት ላይ አራት ጥይት ተኩሰው በመግደል ሙከራ የታሰሩ ተሃይማኖት ሐጐስ የሚባሉ የቀድሞው ጦር አባል የነበሩ ታሳሪ የሚያደርጉት የጠፋቸው አይነት ናቸው አሁንም እዚያው ናቸው ተፈርዶባቸው ይግባኝ ብለው ሲቀርቡ አለመጸጸታቸውን ፍርድ ቤቱ ተገንዝቦ አጸንቶባቸው ተመልሰዋል ታዲያ ጋሽ መስፍን በሚስታቸው ላይ ያደረጉት ትክክል እንዳልነበረና ይቅርታ መጠየቅ እንዳለባቸው አንዲሁም ከፈቃዴ ውጪ አግብታ ጠላኋት ስለሚሏት ልጃቸውም ምርጫዋን ማክበር እንዳለባቸው ሲነግራቸው ቀስ እያሉ እየተቀየሙ በመጨረሻው አኮረፉት ለጥቀው አኔን ክሰሱኝና ወዳጅነታችን ቀረ ከዚያ ከኛ ጋር ያላቸው ግንኙነት ጨርሶ ከተቋረጠና አኛም አሳቸው አደረሱበት መድረስን ስንተው ከረምቦላ የሚያከራየው ገቢዬ ቀነሰ በማለት ክበብ የሚሰራውም እንዲሁ እያሏቸው ብቻቸውን ስለቀሩ በመጨረሻው «ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል» አንዲሉ የሰብቅ ሱስ አድሮባቸው የአስረኛ አስተዳዳሪውን ታሳሪ ከሰሱት አሳበቁበት በዚህም ለየላቸውና የፈሳች ዝንጀሮ ሆነው ወድቀው ተነሱ የሚላቸው በማጣታቸው አማላጅ ልከው ነበር አልባት ሳይገኝ የተለያየን ሰውየው ቀድሞ ከክነበሩበትም ኮን ተዛውረው ወደኛ ዞን የመጡት ወሬ ወዲያ ወዲህ እያሉ በማስቸገራቸውና እንደ ሰላይነትም ስለሚሰሩ በክልሉ ያሉ ጎረምሶች እንገላቸዋለን ስላሉ ነው አሁን እንዴት ሆነው እንደሆን ስጠይቅ ከዚያ ዞን ወጥተው መጥፎ ወደተባለው ዞን ፄደዋል ብለውኛል አንዳንድ ታሳሪዎች ደግሞ ከአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ወደ ዝዋይ ወይም ሸዋ ሮቢት አለያም ወደ ሌላ ቦታ ላለመዛወር በማለት ታሳሪውን ሁሉ የተለያየ ተግባር ፈጽሟል በማለት ጠዋት ጠዋት በድብቅ ሪፖርት በማቅረብ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የሚጥሩ አሉ ሌላው ታሳሪ እየደረሰባቸው ማስጠንቀቂያ በመስጠት ቢያስታግሳቸውም ጉዳቱ መድረሱ አይቀርም አንዱ ሲታወቅበት ደሞ ሌላው ይተካል በጣም የሚገርሙኝ አቶ አድማሱ የተባሉ ታሳሪ ናቸው አቶ አድማሱ አድሜያቸው ወደ ይጠጋል የተከሰሱበት ወንጀል አስገድዶ መድፈር ነው አቶ አድማሱ ሲጠየቁ አላደረግሁም ወይም ፍርድ ተዛባብኝ አይሉም ማድረጋቸውን ያምናሉ ምነው ስሳቸው «እኔ» በሕይወቴ የምወደውና ቢለየኝ የማልፈልገው ጥሩ ጠጅና ሴት ነው አሉኝ እንግዲያ አድርገውታላ ስላቸው «ምን ጥርጥር አለው» ነው መልሳቸው የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲፈቱ « አቶ አድማሱ በሉ ተመልሰው አንዳይመጡ ያቺን ነገር ሁለተኛ እንዳይደግሙ ብላቸው «አይ አሁን ወደ ቤትህ ሂድ ከሚሉኝ አዚሁ ሴቶቹ ዞን ወስደው ቢያስሩኝ ደስታዬ ነበር» ነው ያሉኝ እየቀለዱ አቶ አድማሱ ተፈተው ወጥተው አሁን ድረስ በሰላም ከምኑም ከምኑም ተጠብቀው በቤታቸው አሉ ይህን ይህን ስንጠይቅ ስንሰማ ምንም ያህል የፍርድ ቤት ቀጠሮ ቢረዝምም ቀኑ ቶሎ ይደርሳል ብዙዎቻችን ወህኒ ቤትን የምናውቀው ከውጭ በወሬ ወይም በአካባቢው ስናልፍ አለያም በአጋጣሚ ሰው ታስሮብን ለመጠየቅ ስንሄድ ነው የወህኒ ቤትን ምንነት በሚገባ ለማወቅ ግን መታሰርን ይጠይቃል እፄ ደሞ ባይታወቅ አድሜ ልክ ይቅር እንጂ የማንንም መታሠር አልመርጥም ይልቅስ ሁሉም ገብቶ የወጣ የወህኒ ቤት ልምዱን ቢችል በመጽሐፍ መልክ ካልሆነም በሌላ ለሕዝብ በሚደርስ ቢየስተላልፍ አማራጭነት አለው ወህኒ ቤት መማሪያ ካለፈ ስህተት መታረሚያ ሊሆን ሲገባው በዛሣገራችን ያለው ሁኔታ ግን ለበለጠ ወንጀል መዘጋጃ ለከፋ ተንኮል ማሠልጠኛ አዳዲስ ወንጀሎችና የወንጀል ጥበቦችን መቅሰሚያ ሆኖ ነው ያገኘሁት ከነዚህ አዳዲስ በሽታዎች ለመራቅ ወይም የትምህርት ተሳታፊ ሳለመሆን የግል ጥንካሬን ይጠይቃል ያን ደግሞ ለማግኘትና ጠንክሮ ለመውጣት አካባቢውና በወህኒ ቤት ያለው ሁኔታ ብዙ ጊዜ አይፈቅድም በወህኒ ቤት በፖለቲካ ስም ከመታሰር ይልቅ በነፍስ ግድያ በአስገድዶ መድፈር በዘረፋ ብቻ ከፖለቲካ ውጭ በሆነ ማንኛውም አሰቃቂ ወንጀል መታሠር የበለጠ ተቀባይነት የተሸለ አያያዝና ክብር ያሰጣል በፖለቲካ መታሰር ማለት ጠላት ሆኖ መታየትና ከማንኛውም የወህኒ ቤት «መብት» መታገድ ማለት ነው አንድ በነፍስ ግድያ ወይም በዝርፊያ ተወንጅሎ የታሰረ ሰው ትምህርት ለመማር ወይም በወህኒ ቤት ባለው የሕንዓ የሽመና የልብስ ስፌትና ሌላም ሥራ ላይ አነስተኛም ቢሆን እየተከፈለው እንዲሠራ ትምህርቱንም በተልእኮም ሆነ በግቢው ባለው ትምህርት ቤት የመማር አድል ይሰጠዋል በፖለቲካ የታሰረ ከሆነ ግን በተለይም ከቅንጅት ወይም ከኦሮሞ ነጻ አውጪ ጋር ግንኙነት ያለው ከሆነ ንክዚ አለው ከተባለ የዚህ ሁሉ መብቱ ይገፈፋል የወህኒ ቤት ደንብ በሚባለው ግን ወህኒ ቤቱ ሁሉንም ታሳሪዎች በአኩል አይን የሚያይ ለሁሉም ታሳሪዎች እኩል አገልግሎት የሚሰጥ ነው ይባላል ሌላው ይቅርና በቤተሰብ ጥየቃ እንኳን ማለት በአወደ በአልና ቅዳሜና እሁድ በሚካሄደው የቤተሰብ ግንኙነት ለቅንጅት አባላት የሚፈቀደው ሰአትና ለሌሎች ታሳሪዎች የሚፈቀደው በጣሙን ይለያያል ለሌሎች ታሳሪዎች ጠዋት ከ ሰአት እስከ ፅ ሰአት ከቀትር በኋላ ከ ሰአት አስከ የቤተሰብ ግንኙነት ሲፈቀድ አንድ ጠያቂ ለጥየቃ እስከገባ ድረስ በየዞኑ እንደፈቀደው አየተዘዋወረ የተለያዩ ታሳሪዎችን ይጠይቃል ገደብ የለበተም ለቅንጅት አባላት ደግሞ ከቀትር በኋላ ከዘጠኝ እስከ አስር ነው ለዚያውም አንድ ዞን ከጠየቀ ወደ ሌላ ዞን መሄድ አይፈቀድለትምይፄ ብቻ አይደለም አንድ የቅንጅት አባል ከተፈታም በኋላ የቀሩ አባሪዎቹንም ሆነ ሌሎች አብረውት ታስረው የነበሩ የዞኑን ታሳሪዎች እንዲጠይቅ ጨርሶ አይፈቀድለትም የቅንጅት ሰዎችን ሲጠይቅ የነበረ ሰውም ሲጠይቃቸው የነበሩ ከተፈቱ በኋላ ሌሎችን መጠየቅ አይቸልም ለነገሩ የወህኒ ቤት የቤተሰብ ጥየቃ የሚመራው በዚያው አካባቢ በጥበቃ ላይ ባሉ የጥበቃ አባላት ችሮታ የሚወሰን ስለሆነ ማን ምን እንደሚወስን የሚታወቅ ጉዳይ አይደለም ሁሉም አዛዥ ነው ሁሉም ከልካይና ፈቃጅ ነው አንዱ የፈቀደውን ሌላው ይከለክላል በበሩ ላይ ያሉት ደግሞ በተለይ በቤተሰብ ግንኙነት ወቅት የቅንጅትን ቤተሰቦች በማንገላታት ለአለቆቻቸው ታማኝነታቸውን የሚያረጋግጡበት መንገድ እየሆነ ነበር የሚሰማቸውይህም አንድ ወጥ የሆነ አመራር የሚያስፈልገው ነው በግንኙነት ሰአትም ቢሆን ጠያቂና እኛ ስንነጋገር ለያንዳንዳችን ሁለት ሁለት የፖሊስ አባላት ተመድበው የምንናገረውን በማዳመጥ ሪፖርት እየተደረገ በሚቀጥለው ሳምንት አንዳንድ ጠያቂዎች እንዳይገቡ ይከለከላሉ ጠያቂዎቻችን የውጪ ተወላጆችም ሆኑ የሀገር ውስጥ ከአማርኛ ሌላ መነጋገር ይከሰከላል ያ ጠያቂ ከሚናገረው ቋንቋ ሌላ አማርኝ ባያውቅስ አዎን አትናገር ተብለው ቢከለከሉም አኛም አሻፈረን በማለታችን የመጡትን ጠያቂዎች በሚችሉት ቋንቋ እያነጋገርን ሸኝተናቸዋል የወህኒ ቤት ፖሊሶች እንደ ማንኛውም ሰው አንደማንኛውም ፍጡር ስሜት አላቸው በዚህ ስሜታቸው በመመራትም አንዳንድ ጊዜ ወደ ዞኖች ሲገቡ ሰላምታ ይሰጣሉ ጥያቄ ይመልሳሉ ቆም ብለው ቅሬታ ወይም ችግር ያዳምጣሉ ለምሳሌ የዞኑ ዛላፊ ከአካባቢው ዘወር ብሎ አንደሆን አንድ ፖሊስ ወደ ዞኑ ለተለያየ ሥራ ከመጣ አባክህ ጥራልኝ ወይም ለሌላ ፃላፊ ንገርልኝ ሊባል ይችላል ፖሊሶች ለተለያየ ጉዳይ ወደዞኖች ይገባሉ ልብሳቸውን ለማስተኮስ ሲጃራ ለስላሳ ለመግዛት ቡና ለማዘዝ ይገባሉ በዚህን ጊዜ ከአስረኞች ጋር ይገናኛሉ ሰላምታ ይለዋወጣሉ በዚህም ተወንጅለው ተገምግመው ከሥራ አስከመባረር የደረሱ አሉ አበዛኛዎቹ እኔን ከቴሌቪዥን ውጪ ወይም የተሳካላቸው ከቴያትር መድረክ ውጪ አይተውኝ ስለማያውቁ እዚያ ሲያዩኝ ስላም ይሉኛል ያ ግን በቅንጅትነቴ ሳይሆን በጥበብ ሞያዬ ነው አንዳንዶቹ ቪዲዮህን አይተናል ይላሉ ጥቂቶች ደሞ የተለያየ ሥራ ስሰራ ያዩኝ ናቸው ይህም እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ከሥራ ለመባረር ሰበብ ሆኗል በስርቆት በግድያ በሌላ ሌላ ወንጀል ከታሰረ ጋር ግን ሰላምታ አይደለም ስለፈለገው ጉዳይ ሲያወራ ቢውል የሚጠይቀው የለም ታዲያ ወህኒ ቤቱ ሁሉንም እኩል ነው የሚያየውና የሚያስተዳድረው የሚባለው እንዴት ው። ይህ የተለየ አመለካከት ይደርስብን የነበረው በወህኒ ቤቱ ብቻ ሳይሆን በፍርድ ቤትም ነው ፍርድ ቤቱ የራሱ የሆነ የስነስርአት ተቆጣጣሪ ስለአለው አንደ ደንቡ የወህኒ ቤት ፖሊሶች ለፍርድ ቤት ፖሊሶች አስረክበው እንደገና ችሎቱ ሲያልቅ ነበር መረከብ ያለባቸው በኛ ላይ ግን የፍርድ ቤት ፖሊሶች አንዳችም መብት የላቸውም ነበር በዚያም ፈላጭ ቆራጮቹ እነዚያው የወህኒ ቤቶቹ ነበሩ ፍርድ ቤት አንደሚለው ታሳሪዎችን ለወህኒ ቤት በአደራ መልክ ነው ያስረከበው በተለይም እስኪፈረድባቸው ድረስ ከተፈረደባቸው በኋላ ሙሉ በሙሉ ይረከባል ታዲያ ያልተፈረደብንን ሰዎች ያውም በአደራ የተቀበለንን በልዩ ልዩ ዘዴ ማሰቃየትን ምን አመጣው። አካሄዱ የተንኮል እንደሆነ ስለገባን ግድ የለም ለፍርድ ቤቱ አቤት እንላለን በሚል የፍርድ ቤት መፄጃውን ስንጠብቅ ሰዓቱ ደረሰና እንሂድ ተባለ አሁንም የደረሰው የኛ ወደ ፍርድ ቤት መሄጃ ሰአት ነው እንጂ ዳኞች የሚሰየሙት በጣም አርፍደው ነው ልክ ሰአት ከሩብ ሲሆን ከቃሊቲ ወህኒ ቤት ወጣን ዛሬ ጥበቃው ሌላ ነው በየመኪናው ውስጥ ያለው አጃቢ ቁጥሩ ናር ያለ ነው በየመኪናው ውስጥ የአጅ ማሰሪያ ካቴና አለ የአጃቢ መኪናዎችም ቁጥር በጣም በርክቷል የወህኒ ቤት ባለሥልጣኖች አንዱም በግቢ የቀሩ አይመስልም እነሱ ይወሰናል ብለው ሲያስቡ እኛ ደሞ ያላየነውን ቪድዮ ለማየት ፈቃድ እንጠይቃለን ያንን ዕድል ስለማይከለክሉንና ሕጉም ስለማይፈቅድላቸው ባይሆን ቀጣዩን ቀጠሮ ያረዝሙብናል እንጂ ወደ ውሳኔ አይፄዱም በሚል ነው ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ የተዘጋጀነው እነሱ ከአደራ ጠባቂነት ወደ አስረኛ አስተዳዳሪነት ሊዘዋወሩ እኛ ደሞ እስከሚቀጥለው ቀጠሮ ድረስ በአደራ ለመቆየት ከቃሊቲ ወህኒ ቤት ግቢ የመውጫው ሰአት ደረሰ በመውጫው ላይ ያለው መንገድ ተዘጋ ሞተረኛ ው ቀድሞ በምንሄድበት ጎዳና ላይ ትራፊኩን አያስቆመና ጥግ እያስያዘ ፍርድ ቤት ደረስን ከሰሞኑ የተለየ ጉዳይ ቢኖር ቤተሰብ በሙሉ ገብቶ በአዳራሽ ቦታውን ይጂዚል ታዛቢዎችም ገብተዋል አካባቢው በፖሊስ ታጥሯል በየማቋረጫው ላይ ያየነው የጥበቃ ፃይል ከሌላው ቀን በተለየ መጠናከሩን ያሳያል ግቢው እንደደረስን እንደተለመደው መኪና ውስጥ ሆነን የዳኞቹን የአቃብያትን መምጣት አንጠብቃለን ወዲያውም የዛሬው የፍርድ ሂደት ምን ሊሆን አንደሚችል ሁላችንም የየራሳችንን ግምት እየተናገርን ነው አብዛኞቻችን ያላየነውን ቪድዮ ለማየት ስንጠይቅ ያንን ሰበብ አድርጎ ለመስከረም ይቀጥረናል ስንል ጥቂቶቻችን ደሞ የለም ዛሬ አያችሁም አሳያችሁም ተከራከሩ ይለናል ከኛ ምንም ሲያጣ አጭር ቀጠሮ ይሰጥና በሚቀጥለው ሳምንት ይፈርዳል እንላለን ሁሉም የግምቱን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሰበቡን ያቀርባል ይህን አያልን የዛሬው ከሌላው ቀን በተለየ በጣም በመርፈዱ ለሽንት የሚፄደው አግሩንም የሚያፍታታው አብሮ አያስፈቀደና እየታጀበ እየሄፄደ ይመለሳል የዳኞቹና የአቃብያኑ ማርፈድ የሁሉንም ግምት ወደ አንድ ወገን አሰባሰበው ዳኞች ስላልተሟሉ ሌላ ቀጠሮ ይሰጡናል ተባለ እስካሁን በግቢው ሲደርስ የታየው ዳኛ አዲል ብቻ በመሆኑና ዳኛ መሃመድ አሚን ከአዲል ጋር ስለሚመጣ ሳናየው ገብቶ ይሆናል ብንልም ልኡል ግን ስላልታየ ቀጠሮው አይቀሬ ነው ተባለ አቃብያኑም አልታዩም ልክ አራት ሰአት ከሩብ ገደማ ሲሆን ፖሊሶች ግቡ ትአዛዝ ሰጡና ሁላችንም እየወረድን ናፍቆታችንን በመሳሳም ሰላምታ አየተወጣን ወደ ፍርድ ቤቱ አዳራሽ ገባንኝ ቤተሰብም ተመልካቾችም ቆመው ጠበቁን በተለመደው ኢትዮጵያዊ አክብሮት የሰላምታ ሰጥተን ወደ የመቀመጫችን አመራን ሁሉም መቀመጫ ያበክ በምልክትና በአፍ እንቅስቃሴ ከቤተሰብ ጋር መነጋገር ሰላምታው ቀጠለ ትንሸ እንደቆየን አቃብያኑ በሰልፍ ሸመልስን አስቀድመው ከኋላ እየነዱት እየተጀነኑ ገቡ ሁሉም በትዝብትና በመገረም ይመለከታቸዋል አቃቤ አብርሃም ተጠምቀ ድሮ በጣም ዱሮ የአራዳ ልጆች ሲጀነኑ መነጽራቸውን በጥርሶቻቸው ነክሰው እንደሚይዙት ሁሉ ዛሬ ወደኋላ ቀርተው መነጽራቸውን ነክሰው ነው የገቡት ሁልጊዜም ያንን እያየን አንስቃለን በመጨረሻ ዳኞች አልተሟሉም ስንል ተሟልተው ገቡ ወዲያው እንደተለመደው የዳኞች ስም ተዘርዝሮ አቃብያኑም ስማቸውን ተናንገሩ የዳንኤልና የነጻነት ጠበቃም አስመዘገቡ ተከሳሾች ተሟልተው ቀርበዋል። አሉ ዳኛ አዲል የወህኒ ቤቱ ተወካይ ተሟልተዋል አለ ዳኛ አዲል «ዛሬ ያደረው ጉዳይ» ሲሉ ዶር ብርፃኑ ሁላችንንም ወክሎ «የተከበረው ፍርድ ቤት አቤቱታ አለን» ሲል ዳዮ አዲል ድንገት ቱግ ብለው አልተፈቀደልህም» ሉ ዶር ብርፃኑም አንደቪያ ቱግ የሚያደርግ ምንም ሰበብ አልነበረምና በደንብ ያላዳመጡት መስሎት የተከበረው ፍርድ ቤት አንድ አቤቱታ ስላለን ሲል «አልተፈቀደም አልኩ እኮ አሉ «ክቡር ፍርድ ቤት ከጉዳያችን ጋር የተያያዘ አቤቱታ አለን የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ስላልተከበረ » እንዳለ ዳኛ አዲል ይብሱን ቱግ ብለው ጥርሳቸውን ነክሰው በአልህ እየተርገፈገፉ «ብርፃኑ» አሉ ቁጣቸው ዶር የሚለውን ማንጠልጠያውን እያስጣላቸውና ማን ይፈራሃል አይነት ብስጭት እየታየባቸው «ብርፃኑ አንተ እንደፈለከው አይደለም አልተፈቀደም አትናገርም በቃ ይፄው ነው» ብለው ሊቀጥሉ ሲሉ ሻለቃ ጌታቸው የተከበረው ፍርድ ቤት። አሁንም ከየአቅጣጫው ተከሳሾች አካፄዱ ግራ ሰለሆነባቸው የ«እንደመጥ» ጥያቀ አነሱ በዚህ ጊዜ ዳኛ ልኡል የማዳመጥ ፍቃደኛነት ሲያሳዩ ዳኛ አዲል ግን ከዚያው ከሚፍለቀለቅ ንዴታቸው ሳይወጡ በቃከአስር ደቂቃ በኋላ እንመለሳለን » ብለው ተሸቀዳድመው አንዱ በሌላው ላይ ተደራርበው ወጡአወጣጣቸው የፍርድ ቤቱን ስነስርአት የተከተለ ሳይሆን በእኔ እይታ የአጭር ሩጫ እሽቅድድም ነበር የሚመስለው ተክሳሾችም ቤተሰብም ተመልካቾችም ጠባቂ ፖሊሶችም የደህንነት ሠራተኞችም ሁሉም ትእአዛኩዙን ተቀብሎ ይጠብቅ ጀመር ተከሳሾች የጠየቁት ቪዲዮውን የማየት ውሳሄ ይሰጠናል የሚል ተስፋ አደረብን አሁንም ግን የዳኞቹ ውሳኔ የተለየ ሊሆን አንደሚችል የጠረጠሩ አልጠፉም ሰአቱ አለፈ ደቂቃ የተባለው ወደ ደቂቃ ፄደ አልመጡም ደቂቃ አንድ ሰአት ምንም የለም ሁለት ሰአት ሲሆንም ዳኞቹ ብቅ አላሉም ድንገት ግርግር ተፈጠረ አንድ የወህኒ ቤቱ መለስተኛ ፃላፊ በተለይ የቅንጅትን ታሳሪዎች ለህክምናና ለአንዳንድ ጉዳይ ፈጻሚነት የተመደበውና በእለቱ የወህኒ ቤት ተወካይ ሆኖ ፍርድ ቤት የቀረበው ፖሊስ ተጠርቶ ወደ ዳኞች ክፍል ገባ ጥቂት ቆይቶ በገባበት ሳይሆን በጀርባ ወጥቶ ተጨማሪ ፖሊሶች ያሰማራ ጀመር በተለይ ወደመጸዳጃ ቤት ሄደው የተመለሱ አባሎቻችን እንዳዩት ፖሊሶቹን በከፍተኛ ተጠንቀቅ ማሰማራቱን አይተዋል ምን እንደመጣ ምን እንደተፈጠረ ማንም ያወቀ የለም ዳኞቹ ከፀ ደቂቃ በኋላ አንመለሳለን ብለው ችሎቱን ጥለው ከወጡ ከሁለት ሰአታት በኋላ ተመልሰው በቅድም ተከተል ገቡ ቤተሰቦች ተመልካቾች አኛም እንደተለመደው በፍርድ ቤቱ ሥነስርአት አስከባሪ ፖሊስ ትዕዛዝ ተነስተን ተቀበልናቸው ዳኛ አዲል አሁን ንዴት ሳይሆን ድንጋጤና አለመረጋጋት ነበር የሚታይበት ከእንግዲህ አንቱታዬን ጥየ አንተ ልለው መርጫለሁ ኛ በዕድሜ እበልጠዋለሁ ኛ በዕውቀት አበልጠዋለሁ ኛ በልምድ አበልጠዋለሁ ኛ በሙያ ስነምግባር አክብሮት አእበልጠዋለሁ ኛ ቃል በመጠበቅ እበልጠዋለሁ ኛ ሰአት በማክበር አበልጠዋለሁ ኛ ፈጣሪን በመፍራትና ትእዘዛቱን በማክበር እበልጠዋለሁ ኛ ለሰብአዊ መብት በመቆም አበልጠዋለሁ ኛ ለዴሞክራሲ ማበብ በመታገል እበልጠዋለሁ ኛ ለሕዝብ በመገዛትና ሕዝብን በማክበር አበልጠዋለሁ ስለዚህም እሱንና እሱ የሚመራቸውን ዳኞች ጨምሮ አንተ ማለትን መርጫለሁ መሐመድ ላኒም ያው ነው ከዘወትር ሁኔታው የተለወጠ ነገር ቢኖር ድንጋጤ በገጹ ላይ ይታያል ዳኛ ልኡልም ቢሆን የቁጭትና የቂም በቀል ስሜት ቢታይበትም «ሊሠራላችሁ ነው» በሚል ስሜት ነበር የሚመሰከተን ዳኛ አዲል ተቀመጡ አለንና ተቀመጥን ወዲያው የመከሳከል መብታችንን ሙልጭ አድርጎ በመሻር በኢትዮጵያ ታሪክ በየትኛውም የዛገሪቱ የፍትሕ ስርአት ላይ ታይቶ የማይታወቅ ውሳኔ አሳለፈፁ በፍትሕ ስርአት መሰረት አንድ ተከሳሽ አከላከላለሁ ወይም አልከላከልም የሚለው ካለ ያንን በጽሁፍ አድርጎ ያስገባል እንጂ በዘፈቀደ መከላከልን ዳኛ ው የሚሰጠው ወይም የሚከለክለው ጉዳይ አይደለም ተከሳሾች አቤቱታ አለን የመደመጥ እድል ይሰጠን በማለታቸው ዳኞች ተናደው ችሎቱን ትተው ወደቢሮ ፄደው ስልክ ደውለው ምን እንደሚያደርጉ ፈቃድ የሚጠይቁበት ሳይሆን አቤቱታቸውን ሰምተው ተገቢውን ውሳኔ የመስጠት ሙያዊ ግዴታ አለባቸው የዛሬው የፍትሕ ስርአት በየትም ያልተከናወነ በተለይ ለኛ ለቅንጅቶች አንዲሆን ዳኛ አዲልና ግብረ አበሮቹ ቀርጸው ያመጡት ነው ለመሆኑ አንከራከርም ያልንበትን ማስረጃ ችሎቱ ሊያቀርብ ይችል ይሆን። ነገር ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሕግ ዓምላክም ሳይሆን በፈረንጆቹ በሕግ መገዛትም ሳይሆን በጠመንጃ መገዛትን እንደባሕል እንዲቀበል ተገደደ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቤተ እግዚአብሔርንና ፍርድ ቤትን ያከብራል በአንድ በኩል ሁለቱም የእግኢአብሔርን የበላይነትና የእግዚአብሔርን ሕግ የሚቀበሉ ናቸውበሌላ በኩል ሁለቱም የሰው ልጆች ሁሉ በእኩልነት እንዲታዩ የሚያደርጉ ናቸውበቪህ ባህል ውስጥ ያለፍሁ በመሆኔ እኔም ለሁለቱም ከፍተኛ አክብሮት አለኝየሚያረክሳቸውም ሁኔታ ሲፈጠር በጣም ያሳዝነኛልያሳፍረኛል ከውስጤ ያለ አንድ ክቡር ባሕርይ የጠፋ ይመስለኛልቤተ እግዚአብሔርንና ፍርድ ቤትን የሚያረክስ ነገር ሳይ እኔም አብሬ መርከሴ ይሰማኛል በአፄኃይለሥላሴ ዘመን ቤተክርሰቲያን ውስጥ ጠመንጃ ሳይ ቤተአግዚአብሔር የረከሰ መስሎ ይታየኝ ነበርአሁን በወያኔ ዘመን በፍርድ ቤቶች ውስጥ ጠመንጃ ሳይ የፍርድ ቤት መርክስ ይሰማኛል እኛ በተከሰስንበት ችሎት ለ ወራት ያህል ወታደሮቹ ጠመንጃቸውን ትተዋልበሌላው ፍርድ ቤት ግን ያው ነውየመርክሱ ስሜት የግል ብቻ አይደለም ማሕበረሰባዊ ነውሃገራዊ ነው ግንቦት ቀን ዓም በከፍተኛው ፍርድ ቤት የነበረ ሰው ሁሉ የፍርድ ቤቱን መርከስና መዋረድ እስክ ነፍሱ ጠልቆ ተሰምቶታል በሁዋላ አንደታወቀው አቃቤ ሕግ የተባሉትንም አስገርሟል ጠመንጃ ፍርድ ቤትን የሚያረክሰውን ያህል ባቃቤ ሕግ ስም ባጌጠ ካባ ተሸፍነው ፍርድ ቤቱን የሚያነቃንቁት ሎሌች ፍርድ ቤቱን ያረክሱታልአቃቤ ሕግ ማለት ሕግን ለመጠበቅና ለማስጠበቅ የቆመ የሕዝብ የፃገር አገልጋይ ነው በኛ ክስ አቃቢያነ ሕግ ተብለው የቀረቡት ሶስቱ ቢያንስ ሁለት ተኩሉ የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል ቁም ነገሩ የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው ሳይሆን የወያኔ ማሕበር አባሎችና ሎሌች መሆናቸው ላይ ነው በዚህም የተነሳ በትእቢት ተሞልተው ለፍርድ ቤቱ እንደአዛዥ ለመሆንም ይቃጣቸው ነበርዋናው ሥራቸው አድርገው የያዙት ዕውነትን መደበቅ ፅውነትን ማጣመምና ውሸትን ማምረት ነበር በምርጫ የተነሳ ባጣሪ ኮሚሽኑ መረጃ መሠረት ሰዎች በግፍ መገደላቸውንና ከሰባት መቶ በለይ መቁሰላቸውንና አከለ ጎደሎ መሆናቸውን ለመጥቀስ የመንፈስ ወፄም ሆነ የሕግ ግዴታ አልተሰማቸውም ተከሳሾችን አድመኞችና ወንጀለኞች እያሉ ሲናገሩ የሕጉ መንፈስ በአእምረሯቸው እንዳልስሰረጸ ያሳይ ነበርለሕጉ ታማኝ መሆንን ትተው አሳዳሪያቸውን ለማስደሰት ተከሳሾቹን በጭፍን ውሸት ሲወነጅሉ መስማት የፍርድ ቤቱን መዋረድ የሚያመለክት ነበርፍርድ ቤቱ ውስጥ ባዛዥነትና በበላይነት መገኘታቸውን በተጨባጭ የሚያሳየው የከሳሽ ጠበቃዎች ፊት ያለው ጠረጴዛ ደማቅ ጨርቅ የለበሰ ሲሆን በተከሳሾች ጠበቃች ፊት ያለው ግን አራቁቱን ነውይህ በጠረጴዛዎቹ ልዩነት የሚታየው አድል በሥራቸው ላይም ይንጸባረቃል «እኛ አኮ የምንወክለው መንግሥትን ነው» በማለት ለማስፈራራት መሞከራቸው ሕግን ለመወከል ሃላፊነት እንዳለባቸው የማያውቁና በድፍረታቸው ብቻ የተመረጡ መሆናቸውን በግልጽ ያሳያል ፍርድ ቤቱ በነዚህ ሰዎች ተጽእኖ ሥር ሆኖ ባለጉዳዮች ያቀረቧቸውን ጉዳዮችና ጥያቄዎች ሁሉ ውድቅ እያደረገ ከ ወራት በላይ በአስር እንዲቆዩ አደረገ በዚህ ረጂም ጊዜ ውስጥ ፍርድ ቤቱ በከሳሽ ጠበቃች እየተመራ ዓለም እያየው አዘቅት ውስጥ ገባየከሳሽ ጠበቃዎች አዘቅቱ አፋፍ ላይ ሲደርሱ ዘወር አሉና በመዳናቸው ተገርመው ያልጠበቅነው ነበር» አሉ አዚህ የደረሱት እንዴት ነው ሁለት አጠቃላይ አስተያየት ብዙ አጃቢ ክሶች ቢደረደሩም ዋናው ክስ የሕገ መንግሥቱን ስርአት በአመፅ ለመገልበጥ መሞከር የሚል ነው ለከሳሽና ለተከሳሽ ሕገመንግሥቱ አንድ ከሆነ ተከሳሾች ሕገመንግሥቱን በዛሃይል ለማፍረስ አንድም ምክንያት የላቸውም አቅምም የላቸውም አንዲያውም ተከሳሾች ሁሉ ሕገመንግሥቱ የሚያጎናጽፈውን መብትና ነጻነት ሁሉ ተመርኩዘው የተነሱ ናቸውአለኝታና መከታ ያደረጉትም ሕገመንግሥቱን ነበር ከሳሽሸና የከሳሽ ጠበቆች ሕገመንግሥቱን አያውቁትም ወይም ክደውታል ለማለት የሚያስደፍሩ ብዙ ምክንያቶች አሉ ከሁሉ በፊት ሕገመንግሥቱ የመደራጀት የመሰብሰብና ፃሳብን ያለምንም ገደብ የመግለጽ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ የመምረጥና የመመረጥ መብቶችና ነጻነቶች በእኩልነት ያጎናጽፋል የመንግሥት ስልጣን ባለቤትና ምንጩ የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን ሕገ መንግሥቱ ያስታውቀል አንቀጽ በድምጽ ብልጫ የሕዝቡን ድጋፍ ያገኘ የፖለቲን ቡድን ሥልጣንን በሰላም እንደሚረከብ ይደነግጋል አንቀጽ ፁፀ በዚህም መሰረት አዲስ መንግሥትን መፍጠር እንደሚቻል ይናገራልዛክንቀጽ ዐ በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ከተደነገገው ውጪ በዛይል ወይንም በጉልበት የመንግሥት ስልጣን እንዳይያዝ ይከለክላል አንቀጽ ሕገመንግሥቱ ፍጹምና ዘለአለማዊ ባለመሆኑም የሚሻሻልበትን መንገድ ደደነግጋል አንቀጽ ዐ ባጠቃላይ በመብቶች ጉዳይ ሕገመንግሥቱ ይህ ቀረው የሚባል የሌለበት ሰነድ ነው በሚያዝያ ወያኔኢህአዴግ ከመንግሥት ጋር በመተባበር በመስቀል አደባባይ ሕዝባዊ ስብሰባ ጠርቶ በነበረ ጊዜ ሊቀመንበሩና የመንግሥት ጠቅላይ ሜኒስትር ስብሰባውን «ሕዝባዊ ማዕበል» ብለውት ነበረ «ማዕበል» የሚለውን ቃል የመረጡበትን መነክንያት ማብራራት አያስፈልግም ሆኖም በሚያዝያ ፀ ቅንጅት በዚያው ቦታ በጠራው ስብሰባ አዲስ አበባን በሙሉ አጨናንቆ « ሕዝባዊ ማዕበል» ከተባለው እጥፍ ድርብ የሆነ ሕዝብ ታየ ይህ ስብሰባ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተከሂዶ አንድም እንከን ሳይገኝበት የኢትዮጵያን ሕዝብ ጨዋነት አስመስክሮ ተጠናቀቀ የተክሳሾቹን ሕጋዊነትና ሰላማዊነት ከዚህ ስብሰባ የተሸለ ተጨባጭ ማስረጃ ሊገኝ አይቻልም በምርጫው ጊዜስ። የከሳሽ ጠበቃ የውሸት ቋት መሆኑን በተደጋጋሚና በተጨባጭ አሳይቷል ነገር ግን ፍርድ ቤቱን እንዲህ ያሳስታል የሚል ጥርጣሬም አልነበረኝምብይኑ በውሸት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ያሳዝነኛልበጣም ያሳፍረኛል በቪዲዮዎቹ ላይ ሁሉ እንደተሰማው እኔም ሆንሁ ሌሎች ተከሳሾች ከሕጋዊና ከሰላማዊ ንግግር ውጪ አልተዛነፍንምበሕገ መንግሥቱ ከተፈቀደውፃሳብን የመግለጽ ነፃነት ውጪ በነቢብም በገቢርም ቅንጣት ወንጀል አልፈጸምንም በበኩሌ ደሞ አንድም የምከላክለው ነገር የለም ተከላከሉ ያለው ፍርድ ቤት ለመከላከል ብንሞክርም ያዳምጠናል ለማለት አያስደፍርም አስራ ዘጠኝ ወራት ያህል ስንታሰር የከሳሽ ጠበቃ እንደልቡ በፈለገ ጊዜ ሲናገር ለእኛ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ጥያቄችንና አቤቱታችንን ለማዳመጥ በወር አንድ ደቂቃ ሂሳብ እነኩዋንጊዜ አልሰጠንም በግንቦት ቀን ጥያቄዎቻችንን አድምጡን የሚል የሁሉም ጥያቂ በመቅረቡ ፍርድ ቤቱ ተረበሸችሎቱን አቋርጠው ዳኞቹ በንዴትና በችኮላ ሊወያዩበት ወጡሁለት ሰአት ተኩል ያህል ተከሳሾቹንም ተመልካቾቹንም የተከሳሽ ቤተሰቦችንም ከአቆዩ በኋላ በሰባት ሰአት ተኩል ግድም እንደተናደዱና እንደተበሳጩ ገብተው የጥፋተኛነት ውሳኔና የሚቀጥለው የብይን ቀጠሮ ሐምሌ መሆኑን ነግረውን በችኮላ ሲወጡ ተከሳሽ ሁሉ አግዚአብሔር ይስጣችሁ»በማለት ተሰናበትናቸው በኋላ እንደተገነዘብነው ሐምሌ ዕሁድ ነው። አውነት እውነት አላችኋቷለሁ እኔ ታዘብኳችሁ እንጂ አልተቀየምኳችሁም ውድ የቀድሞ ወዳጆጴጵ ትዝብትን አትከልክሉኝ ቢያንስ እውነቱን እየነገርኳችሁ ነውና በሙያዋና በጠባይዋ የማከብራት ከማንም ጋር ፍቅር እንጂ ጠብን የማታውቀው ቀድምትና ተወዳጂ የጥበብ ሰው አሰለፈች አሽኔ አሰለፍ ከማእከላዊ እስከ ቃሊቲ ሳትለየኝ ከጎኔ ቆማለችና ከነበረኝ አክብሮት የበለጠ እንዳከብራት እንድመካባት አድርጎኛል የሚገርመው ከብዙዎቻችሁ የተሸለ ደምወዝ የሚያገኘ ውና ጥሩ ቦታ የሚሰራው ዮሐንስ ወንድምጓደኛነቱን በችግሬ ወቅት ደጋግሞ ያረጋገጠልኝን ጆኒንዮሐንስብርፃኑን አከብረዋለሁከማአከላዊ ጀምረህ ሳትለየኝ ቤተሰቤንም በማበረታታት ምንግዜም ወንድሜ እንደሆንክ አረጋግጠህልኛል ከናንተ ዝቅ ያለ ደምወዝ የምትከፈለውን ኑኑ አሰፋን አትንኩብኝ እግሯ እስከሚቀጥን የጠየቀችኝ ግን ከናንተ ያነሰ ውለታ የሰራሁላት የክፉ ቀኔ ነች እናንተም ብትሆኑ አሁንም ክፉ አይንካችሁምንም ችግር ቢያጋጥማችሁ ቃል ለምድር ለሰማይ ከጎናችሁ እንደምሆን ቅንጣት ታህል አትጠራጠሩ እኔ ታዘብኳችሁ እንጂ አልተቀየምኳችሁም ቅንጅት ያስተማረኝ ትልቅ ነገር ቢኖር አለመቀየምን ነውባላችሁበት መጥቼ «ታዲያስ» አንዳልላችሁ ምናልባት ብትሸሹኝ የበለጠ ስለምታዘባችሁ ነው ያላደረግሁት ከቃሊቲ መልስ ጋዜጣዊ መግለጫ ሐምሌ ከእሥር ከመፈታታችን ቀደም ብሎና ከወጣንም በኋላ ለጥቂት ቀናት እኛን ከሕዝብ ለማጋጨትና ለማስጠላት የመንግሥት መገናኛ ብዙሃንና አንዳንድ ዳረጎት በላዎች ሲያብጠለጥሉን ነበርአንድም ቃል አልወጣንም ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በድርድሩ ላይ ማንኛውም ወገን ይህን ጉዳይ በተመለከተ ለፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ እንዳይደርግና አንዱ ባንዱ ላይ የጥላቻ ስሜት ከመንዛት እንዲቆጠብ የተደረሰበት ስምምነት ስለነበረ ዝምታው ያንን በማክበር ነው ቅንጅት ምንግዜም ቃሉን ያከብራልይህንንም ግልፅ ለማድረግ ጋዜጣዊ መግለጫ አወጣ ያውም ውሎ አድሮ በጥንቃቂ ሐምሌ ዓም ከአሥር ከተፈቱት የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራር አባላት የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የግንቦት ምርጫን ተከትሎ በአገራችን በተፈጠረው የፖለቲካ ምስቅልቅል ምክንያት የለው ሕይወት ጠፍቶአል የብዙ ዜጎች ነጻነት ተገፎአል የድፃ ፃገር ንብረት ወድሞአል በተጨማሪም በቀላሉ ሊሽር የማይችል የሥነ ልቡና ቁስል በማሕበረሰባችን ላይ ደርሷል ይህንን አጠቃላይ ችግር በአንድ ጊዜ መፍታት ባይቻልም ቀስ በቀስ ከጊዜ ጋር እንደ ማሕበረሰብ እያገገምን ወደፊት እንሄዳለን ብለን አንደ ዛፃገርና ሕዝብ ማመን የወደፊት ሥራችን መሰረት ነው የዚህ ሰፊ አገራዊ ቀውስ ሰለባዎች አንዱ እኛ የቅንጅት አመራሮች ነን ከ ወራት እሥር በኋላ ሐምሌ ሀ ዓም ከእስር ተለቀናል ክእስር እንድንለቀቅ የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ሃይሎች ከፍተኛ ጥረት አድርገዋልብዙ ኢትዮጵያዊያን በፃዛገር ውስጥና ከፃገር ውጪ በየፃይማኖት ቤታቸው ጸሎት አካሂደዋልሴሌሎችም ከእኛ ጋር ያላቸውን አጋርነት ለፀሃይ ግለትና ለብርድ ሳይበገሩ በተለያየ ቦታ በሕዝባዊ ሰልፎች ገልፀዋል ለረጂም ቀናት በፆም ምህላ አድርገዋል የፃገር ሽማግሌዎች ችግሩን በሰላምና በእርቅ ለመፍታት ላይ ታች ብለዋል በቅድሚያ ለእነኘ ህ ሁሉ ዜጎቻችን እንዲሁም ኢትጵያውያን ላልሆኑ የመብት ተክከራካሪችና የዴሞክራሲ ጠበቆች በአደረጉት ጥረት በእስር እያለን ይሰጡን የነበረውን የሕሊና እረፍት በማስታወስ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ሕይወታቸውን ላጡት ዜጎቻችን ያለንን ከፍተኛ አክብሮት የምንገልጸው እኛም ሆንን ሌሎች ኢትዮጵያዊያን መቼም የማንረሳቸው የዴሞክራሲ ሰማእታት መሆናቸውን በማስታወስ ነውለቤተሰቦቻቸውም ፈጣሪ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ሁሌም በጸሎታችን አንዘነጋቸውም አኛን ከአስር ለማስፈታትም ሆነ በፀብና በእልህ አጣብቂኝ ውስጥ የገባውን የኢትዮጵያን ሰላማዊ የፖለቲካ ሂደት ከገባበት ለማውጣት የተወሰኑ የፃገር ሸማግሌች ቢያንስ ላለፈው አንድ ዓመት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ይታወቃል የጥረቱ መሠረታዊ መንፈስ እኛን ከአስር ማስፈታት ብቻ ሳይሆን ሀዲዱን የለቀቀውን የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ጉዞ ወደ ተገቢው መስመርና አቅጣጫ መመለስ ነው ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ሽማግሌቹ አስፈላጊ ነው ብለው ያመኑበትንና እኛም ከልባችን የተቀበልነውን የአገራችን ባሕል በሆነው ይቅርታ መባባል መንፈስ ችግሩን ለመፍታት ተስማምተናል ያለፈውን በሚመሰከት ጥፋት ያጠፉትን ዛይሎች ሁሉ ይቅር በማለትበዚህ ሂደት የተጎዱትን ከጉዳታቸው የሚያገግሙበትን መንገድ በመሻት በዋነኛ ነት ደግሞ የወደፊቱን በመመልከት ከእርቁ በኋላ በሚፈጠረው አጠቃላይ ሁኔታ ላይ በማተኮር ሁኔታች ከሁከቱ በፊት ወደነበሩበት መመለስ አሰፈላጊ መሆኑን ተማምነናል ጥረቱም በይበልጥ በዚህ ሁኔታና ከዚያም በኋላ በተፈጠረው የተበከለ መንፈስ ምክንያት ሁላችንም የምንወዳት ፃገራችን የበለጠና በኋላ ልትወጣ ከማትችልበት ማጥ ውስጥ እንዳትገባ ለመከላከል ያለመ ነውከክከጅምሩም እኛ የቅንጅት አመራሮች በተቻለን መጠን በጥላቻ ባለመመራትና ተጎዳን የምንለውን ሁሉ በትእግስት በመያዝ እስከመጨረሻው ተጉዘናል ዘላቂ የሆነ የእርቅ መንፈስን ለማስፈን አስፈላጊ ናቸው በተባሉ የተለያዩ ነጥቦች ላይ ከሽማግሌች ጋር ለሰፊ ውይይቶችን አድርገናልበብዙ ነጥቦችም ላይ ተስማምተናል የደረስንባቸው ስምምነቶችም የእኛና የሽማግሌች ብቻ ሳይሆኑ ጉዳዩ በሚመለከተው ሌላው አካል ዘንድም ስምምነት እንደተደረሰባቸው በሽማግሌች ተገልጾልናልምንም እንኳን በመጨረሻው በመንግሥት በኩል ስምምነት ተብሎ የተገለጸው ከዚህ ከሽማግሌች ጋር ከተደረሰው ስምምነት የተለየ ቢሆንም የስምምነቱን እውነተኛ ይዘት ወደፊት አነሺሁ የዛገር ሽማግሌች አስፈላጊ በሆነ ጊዜና በሚመቻቸው ሁኔታ ለሕዝቡ ይገልጹታል ብለን እናምናለን ስምምነቱ ከተፈጸመም በኋላ በመንግሥት መገናኛ ብዙዛን በሰፊው እየተሰጠ ያለውን የፕሮፓጋንዳ ምንነት የኢትየጵያ ሕዝብ በቅጡ እንደሚያውቀው በውል እንረዳለን በዚህም ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ቅንጅት በሕዝቡ ዘንድ ያለው ተሰሚነት ቅንጣት ታህል እንኩዋን ዝቅ ይላል ብለን አክንገምትምይህንንም ከተፈታን በኋላ ሕዝቡ ያሳየን አክብሮትና የሰጠን አስደናቂ ፍቅር አረጋግጦልናል ስለዚህም ለተሰነዘረው ፕሮፓጋንዳ አጸፋ መልስ መስጠቱ ሽማግሌችም ሆኑ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲፈጠር የፈለጉትንና እኛም ያመንበትን መንፈስ የበለጠ ከመበከል ውጪ ምንም ፋይዳ የለሴለው መሆኑን ተገንዝበን አልፈነዋል ይልቁንም እኛ አንደ ፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ባለፈው ላይ ከማተኮር ወደፊት ማየትን መርጠናልይህም የኢትዮጵያ የወደፊት አጣ ድርጅታችን የተመሰረተበትንና የታገለለትን የኢትዮጵያ ሕዝብም ከልቡ የሚፈልገውንና የሚገባውን ዴሞክራሲያዊ ስርአት በእግሩ ለማቆም የሚደረግ ትግል ነውእኛ የቅንጅት አመራሮች ለዚህ ትግል ያለንን የማይነቃነቅ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለንየዚህ ሂደት የመጀመርያው እርምጃ በስምምነታችን መሰረትና የዛገር ሽማግሌች ለማስፈጸም ቃል ከገቧቸው ጉዳዮች አንዱና ለአሁኑ ጊዜ ዋና የሆነው ከምርጫ ጋር በተያያዘ በእስር የሚገኙት በሙሉ ከእስር ተፈትተው ማየት የእኛም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ አጀንዳ ስለሆነ ይህንን ጉዳይ የዛገር ሽማግሌዎች በአስቸኳይ እንዲያስፈጽሙ እናሳስባለን ይህ ከመሆኑ በፊት ግን በሌሎች አጀንዳዎች ላይ ወደፊት መፄድ አስቸጋሪ መሆኑን እንገነዘባለን በመጨረሻም አኛ የቅንጅት አመራሮች ኢትዮጵያችን አሁን ከገባችበት የፖለቲካ አጣብቂኝ ወጥታ አውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ስርአት አንዲፈጠር የጀመርነውን ትግል እንደምንቀጥል ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ስርአት በፃገራችን መፈጠርአኛ ከያዝነው አቋም ጋር ከሚስማሙ ከማናቸውም ፃገራዊ ሃይሎች ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናችንን እንገልጻለንበቀጣይነትም ቅንጅቱ አሁን በሀገራችን ባለው ሁኔታ ላይ በሰፊው መክሮ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለሕዝቡ ይገልጻል ብቻ ነው ያሰው በቅድሚያ መፈታታችን ዱብ እዳ ነበር ማንም ያልጠበቀውሸማግሌዎቹ ከቀሩ ድርድሩም ከተቋረጠና ከሽማግሌዎቹ ጋር ክፉና በጎ ተነጋግረን ከተለያየን ከወራት በኋላ በመፃዛል ላይ መጥተው ዝም ዝም ተብሎ ያለቀ ጉዳይ ነበር ያን አለት ሐምሌ ቀን ዓም ድንገት ፃላፊዎች ሽር ጉድ አበኩ የዞናችን በር ያለወትሮው ከውጭ ተቆለፈ የተለያየ ወሬ ነበር የምንለሰማውአንዱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ግቢውን ለመጎብኘት ስለመጡ ነው ይላል ሌላው ደሞ የለም የውጭ ዛገር ሰዎች ናቸው ይላል ሌለኛው ደግሞ የቀይ መስቀል አባላት ናቸው ሲል በመጨረሻው ላይ ትልቁ ቡሽ የምንለውመጥቶ ዶር ብርነኑንአቶ አባይነህን እኔን ጠራን ወዲያው ደሞ ቆዩ ተባሰለደሞ እንደገና ሁላችሁም ተዘጋጁ ተባልንተዘጋጀን ተቆልፎ የነበረው በር ተከፈተ ከሌሎችም ዞኖች ሌሎች አባሎቻችን ሲሰባሰቡ አየንእኛም ወጥተን በአዳራሹ ተቀላቀልንአሁንም ለምን እንደተሰባሰብን ግልጽ አልሆነልንምሁሉም ተጠቃሎ ከገባ በኋላና የሚጠበቁት ስው ከመጡ በኋላ የተሰበሰብንበት ጉዳይ ለመፈታት እንደሆነ ተነግሮን ወረቀታችን ተሰጠን ከአስር እንደተፈታን ተነግሮን ወደየቤታችን እንድንሄድ መመርያ ሲሰጠንና በፕሬዜዳንቱ የተፈረመው የመፈቻ ደብዳቤ ሲሰጠን አብሮ አንድ ያላሰብነው ሁኔታም ተፈጠረሁላችንም ወደየቤታችን የምንሄደው በተዘጋጀልን መኪና መሆኑንና ከቤተሰቦቻችን ጋር ከበር ውጪ እንደማንገናኝ ተነገረንሌላው ቀርቶ እቃችንን እንኳን የምናዘጋጅበት ጊዜ አላገኘንም ለምን ቤተሰብ ጠርተን አይወስዱንም የሚል ጥያቄ አንስተን አይሆንም መኪና ተዘጋጅቷል በዚያ ነው የምትሄዱት ተባለሌላው ቢቀር የሚያስፈልገን እንደመድሃኒት የመሳሰለ እቃችንን እንኳ እንድንወስድ ጊዜ ይሰጠን ብንልም ነገ መጥታችሁ ትወሰዳላችሁ አሁን ግን በቅርብ ያለ እቃችሁን ብቻ ተብለን በጥድፊያ ያገኘነውን ብቻ ነው ይዘን የወጣነው ከቤተስብ ደግሞ የጥቂቶቻችን የመፈታታችንን ወሬ ሰምቶ ኖሮ ቀድሞ መጥቶ ቃሊቲ ወህኒ ቤት በር ላይ ቆሞ ይጠብቃል የቅንጅት አባላትና አንዳንድ ወዳጆቻችንም አሉከወህኒኪ መውጣታችን ሲነገረንና የመፈቻው ደብዳቤ ሲሰጠን ስንወጣ እቃ ስናስር ስንጭን ስንጫን ዝርዝር ወሬ ለመቅረጽ የተዘጋጀው የቴሌቪዥን ካሜራ አጠገባችን እንዳይደርስ በማለታችን ሌላውን ሁፄታ ሳያነሳ ቢቀርም በድብቅ ትንሸ ብጣሸ ወሬ አግኝቷል ወደቤታችን የምንፄደው በመንግሥት መኪና ብቻ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ በሰፈር በሰፈር ተቀናጅተን በየተመደበው መኪና ገብተን ከግቢው ወጣን በር ላይ በተዘመድና ወዳጆች ደጋፊዎቻችን አሉግማሹ ይስቃል ሌላው ያለቅሳል ደስታም ያስለቅሳል የተባለውን እያየን ባጠገባቸው በጨረፍታ እየተያየን ፄድንበቃሊቲ በር ላይ የነበሩት ወዳጆቻችን መውጣታችንን ሲያዩ ለቤተሰቦቻችን እየደወሉ መጡ ሲሉ ወደ ቃሊቲ መንገድ ጀምረው የነበሩት ወደየቤታቸው ተመለሱ አንዳንዶቻችን ግን ቤተሰብን ቀድምን ቤት ደርሰናል ስንደርስ ምናልባት በሚል ቤተሰቡ ገሚሱ ወደ ቃሊቲ ቀሪው ቤት ስለነበር ሁሉም ሲደርስ በየመንደሩ ሕዝብ ተሰብስቦ አልልታው ቀልጦ እንኳን ደስ ያላችሁ አንኳን ለቤታችሁ ያበቃችሁ የሚለው የደስታ መግለጫ የየአንዳንዱን ግቢ አጣቦት ነበርሰላምታ ለመስጠት ወረፋው አላደርስ ብሎ ጊዜ ያስጠብቅ ነበርሕብረተሰቡ ለኛ ያለውን ፍቅር አክብሮት ከምርጫው በኋላ ከነበረውየበሰጠ ሆኖ አገኘነው ገና ግቢውን ሳይገቡ አልልታው በሴቱ ብቻ ሳይወሰን ወንዱም አልል ብሏልልክ እንደታቦት እግራችን ላይ አየወደቁ ነበር አግዚአብሔርን የሚያመሰግኑትፎሁሉም «ስለታችን ሞላ ምኞታችን ተሳካ ሕልማችን ደረሰ» ነበር የሚለው ይህ ነው ለካ የሕዝብ ፍቅር። ወደ መጸዳጃ ቤት በሚኬድበት ሰአት አይጦች ሲሸሹና ወደ ጉድጓቸው ሲገቡ መለስተኛ ሰልፍ ያመስሉታልበብዛት ስለሆነ የሚንቀሳቀሱት ያስፈራሉአንዳንድ ጊዜ ሰዎች ለመጸዳዳት ከተቀመጡ በኋላ ከጉያቸው ተስፈንጥረው ወጥተው ሲሄዱ በጣም ያስደነግጣሉይህ ያጋጠመው አንድ ጓደኛችን ደንግጦ ሉሪውን ሳይታጠቅ ዘሎ በመውጣት ለጥቂት ቀን መሳቂያ ሆኖ ነበር ለነገሩ ሳይታሰብ የሚያጋጥም እንዲህ አይነት ዱብ እዳ ያስደነግጣል ለነዚህ አይጦች ቀንም ሆነ ማታ ከመጠንቀቅና መግቢያ ሊሆን የሚችልን ቦታ ሁሉ ከመዝጋት ሌላ አማራጭ የለውምየየመኝታ ቤቱ በር ከተዘጋ በኋላ ቀዳዳውን ሁሉ መጠቅጠቅ ያስፈልጋል በአይጥ በኩል ቃሊቲም ያው ነውማእከሳዊ የሚበልጠው በአይጦቹ ትልቅነት ሲሆን ቃሊቲ ደሞ ማእከላዊን የሚበልጠው በብዛት ነው በቃሊቲ እንደገባን ምድባችን የቀይ ሽብር ተፋራጆች ግቢ ስለነበር በዚያ አይጥ አልነበረም ማለት ይቻላልቢኖርም በመንገድ ተላላፊ እንጂ ነዋሪ የለምቃሊቲ ካሉት ዞኖች ሁሉ ትልቁ የህብረት ሱቅ ያለው በዚሁ ግቢ ሲሆን አይጥን ለመከሳከል ባጀት ተመድቦላት የምትጠብቅ አንዲት ድመት አለች ወተትና ምግብ አታስብም ፍለጋም አትዞርም ደምወዝተኛ ናትሌሎችም የሷ ልጆችና ያልሆኑም አሉበየክፍሉ ድመቶች አሉና አይጦች አካባቢውን አይሞክሩትም ከዚያ ግቢ ፍቅራችሁ በረታ ብለው ካስወጡን በኋላ በተለያየ ዞን ሲመድቡን የአይጥ መንጋው ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ ጀመርንበዞን የገባን ለት መተኛት በፍጹም አልቻልኩም ነበር ቀደም ብለው የነበሩት ተለማምደውት ችግሩን ተወጥተውታልይተኛሉአኔ መልመድም ተቸገርኩ ገና ገብተን ጋደም ስንል በጣራው ውስጥ ከድምጹ አኳያ ቁጥሩን ገምት ብባል በአንድ ጊዜ የሚሰማው ድምፅ አይጥ ብዬ እገምታለሁሁኔታው በጣም አስቸጋሪ ስለሆነብኝ ሻለቃ አፈወርቅን ሻለቃ እንኳን ሲሉት አይወድም ቀድሞ ክነበርንበት ዞን እንዲለምንልኝ ጠይቂው አንድ ድመት አመጣልኝ ትንሽ ነበረችምግብ መብላት ስላልጀመረች የግድ ወተት እየገዛሁ ማሳደግከኔው ጋር ማስተኛት ካርቶን አዘጋጅቼ አሸዋ አድርጌ በዚያ ላይ ባጠገቤ መተኛትን ሁሉ ሰለጠነች ስሟም «ቃሊቲ» ተባለሁሉም የወደፊት ጥቅሟን በማሰብ ይመስለኛል በጣም ይንከባከባት ጀመር ከቃሊቲ ተጨማሪ አንድ አሳዳጊዎቹ የሞቱበት ድመትም መጣና በማደጎነት ለኔው ተሰጠኝጋሽ መስፍን ከመልኩ ቀለም የተነሳ ነብሮ ብሎ ሰየመውነብሮ እንደቃሊቲ አይደለም ዘገምተኛ ይመስላልምግብ ላይ ግን አይታማምቃሊቲና ነብሮ በአንድ ላይ ቢያድጉም አንድ አይነት ጠባይ የላቸውም ቃሊቲ አይጥ አይታ አታልፈውም ውላም ቢሆን ትይዘዋለች አንዳንድ ቀን ሙሉ ቀን አፍጥጣ ጠብቃ ትይዘዋለችነብሮ በዚህ አይታማም ተይዞለት አንዲሰጠው ነው የሚጠብቀውበግድ እንዲይዝ ልትሞት ትንሽ የቀራት አይጥም ብትመጣለት ሲጫወትባት ታመልጠውና አከኪ ዘራፍ ማለት ይጀምራል እንጂ ተዘዋውሮ አድኖ መያዝን አልፈጠረበትምአይጥ ከመያዝ ይልቅ ዛፍ ላይ ያሉትን ወፎች ተንጋጦ በማየት ሲቋምጥ መዋልን ይመርጣል እንዲያውም አንድ ሁለት ጊዜ እርግብ ይኮ ጉድ አሰኝቶናል ጋሽ መስፍን ግን ሰላማዊው ነበሮ» ነበር የሚለውፎለነብሮ አንድ ሌላ ጠላት መጥቶበት ቃሊቲ ታግዘው ነበር በኋላ ግን ሰለቻትና ተወችውአዲስ አበባው ዓለም በቃኝ ያደገና ፄርሜላ የሚባል ድመት ነው አከባቢውን የግሉ ለማድረግና ሁሉንም ለማስገበር ያቀደ ቢሆንም ከነብሮ በቀር ገባሪ አላገኘምቃሊቲ የማትሞከር ሆነችበት ነብሮ ገና ድምጹን ሲሰማ መግቢያ ነው የሚያጣውአንድ ቀን ሁላችንም ባለንበት ነብሮ በሜዳው ላይ ይንጎማለላልወደ በሩ መሄድ ይወዳልና ወደበሩ በመፄሄድ ላይ ሳለ ድንገት ፄርሜላ ከየት መጣ ሳይባል ከኋለው ከቸች አለበትአላወቀምና ሲጎማለል ድንገት ዘወር ቢል ፄርሜላወዲያው ግቢውን ሁሉ ቅዘን በቅዘን አድሮጎት ቤት ውስጥ ገብቶ ተሸሸገ አንድ በጣም የሚያዝኑለት እስረኛ ገረሟቸው «ከምንጊዜው ቀጠነለት» ያሉት መተረቻ ሆኖ ነበር ነብሮ በመኖሩ ብቻ ፍርፃዛቱን የማያውቁ አይጦች ይሸሻሉ በሚል በቁጥር መኝታ ቤት ያሉት ቦታ አዘጋጅተውለት ደባል ገብቶ ይኖራል ያው ለምግቡ እኔ ጋ መጥቶ በልቶ ወተቱን ጠጥቶ ለመጨዋቻነት ይወጣል ሲመሽ ወደ ቁጥር ይሄዳል ሄርሜላ የነብሮን ፍርሃት በሚገባ ስላወቀበት የሚያድርበት ቤት ሁሉ እየገባ ያንደፋድፈው ነበርበቁጥር ያሉ ታራሚዎች ነብሮን ከፄርሜላ ለማዳን» የሚል ፕሮጄክት አውጥተው ፄርሜላ በተገኘ በት ይወገር ብለው ወሰኑ ሌላው ቡድን ደሞ ነብሮ በቅምጥል እያደገ ተሞላቆ ራሱን መጠበቅ ባለመቻሉ ደካማ ስላሸነፈው ለምን ፄርሜላ ይወቀሳል መተውና ነብሮ ራሱን እንዲጠብቅ አንዲከላከል ማድረግ ይሻላል አሉ ያም ሆነ ይህ ነብሮ ከመልኩ ቀለምና ጋሽ መስፍን ከሰጠው ሰላማዊ ነብሮነት ባሻገር ምንም የነብር ጠባይ አልነበረውም ከነብሮ ጋር ሁሉም የከረረ ፍቅር ቢኖረውም እንዳረጉት ስለሚሆንና ተኝቶ እያለ አቅፈው አንስተው ሌላ ጋ ወስደው ቢያስተኙት በዚያው ፎርም ይተኛ ል። ለሚለው ጥያቄ በፃገር ውስጥ ያሉ አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን ስለሚያዳምጡ ምን እያደረግን እንደሆነ እንዲያውቁ ይረዳልና በአስቸካይ ጉዞው አንዲደረግ ላእላይ ምክር ቤቱ » ይወስን የሚል ነበር በዚህ ጉዳይ ላይ በርካታ ሰአት የፈጀ ውይይት ተደርጎ በሊቀ መንበራችን የተነሳው ነጥብ አሳማኝና ትክክልም በመሆኑ ከዚህ ቁጭ ብሎ ፍቃድ በመጠበቅ መንግስትም ዛሬ ነገ እያለ ጊዜ በማጥፋት ከአባሎቻችንና ከደጋፊዎቻችን ሊያለያየን ስለሚጥር በቀረበው ሃሳብ ላይ መወሰኑ አማራጭ የሌለው ሆኖ ተወሰነ በአለቱ ስብሰባው ሲጠናቀቅም ኢንጅነር ኃይሉ በሚቀጥሉት ስብሰባዎች የህክምና ቀጠሮ ስላለኝና ያንንም መከታተል ስለአለብኝእናንተ እየተሰበሰባችሁ የምታሳልፉትን ውሳኔ አቀበላለሁ ሆኖም እንዳውቀው ብታደርጉ የተቀላጠፈ አካፄድ ስለሚሆን እነማን ያሳውቁ የሚለውን ወስነን የዛሬው ስብሰባ ያበቃል» በማለታቸው ጉዳዩ ልክ ባይሆንም በጤንነት ምክንያት የተነሳ ነውና ይሁን በሚል ተምሊቀ መንበር ብርቱካን ጸፃፊያችን ሙሉነህ ኢዮኤል ዶር ኃይሉ አርአያ ፉ ስለሺ ጠና በየምሽቱ የስብሰባውን ውጤት እንዲያሳውቁ ተወስኖ የአለቱ ስብሰባ ተጠናቀቀ እስከዚህ ድረስ የላእላይ ምክር ቤት መሟላት አለመሟላት ጨርሶ አልተነሳምደግሞም ሊሟላ የሚችልበት መንገድም የለም ምክንያቱም ላ ገሚሱ ከሃገር ወጥቷል ላ ሌላው ከሌላ ፓርቲ ጋር ግንባር ፈጥሮ በመንቀሳቀስ ላይ ነው ተራፊው ከእንግዲህ በምንም መልኩ ስሜ ከቅንጅት ጋር እንዲነሳ ስለማልፈልግ አትድረሱብኝ ብሎ ወስኗል አነዚህ በአንድነትሲደመሩ ከእስር የተፈታነው የላእላይ ምክር ቤት አባላት አብላጫ እንሆናለንይህም ታምኖበት ነው ወደ ስብሰባ የገባነውይህ ታምኖበት ነው ያልታሰሩት ተጣርተው ክኛ ጋር ይቀላቀሉ የተባለው በዚህ ሁኔታ ስብሰባው ለበርካታ ቀናት እየተካሄደ ውጤቱም በየምሽቱ ለሊቀመንበራችን እየደረሰና እሳቸውም እየተስማሙበት ቀጠሰበስተመጨረሻው ላይቆይቶ ግልፅ እንደወጣው ከዋሽንግተን በተላከ መልእክት ሳቢያ ችግር ይሰማ መር ሁለቱም ኮሚቴዎች እንዲፈርሱ የሚለው ደብዳቤ በሊቀመንበራችን ከተላለፈና አንደኛው መፍረሱን በጸጋ ሲቀበል አንደኛው ግን በጭራሽ የመፍረሱ ነገር እኔን አይመለከተኝም በሚል አቋም በመያዙና ከዋሽንግተንም በሻለቃዎቹ በዮሴፍና አድማሱ በዶክተሮቹ በዘብህና ታዬ ለሊቀመንበራችን የተላከ መልእክት ነገር ማደፍረስ ጀመረበየትኛውም የቡድን አወቃቀር ላይ ስምምነት የነበራቸው ኢንጅነር መልእክት ከደረሳቸው በኋላ የአሜሪካ ልኡክ አባላት ይቀየር የሚል ዛሳብ አመጡየእለቱን ውሳኔ ይዞ የሄደው ቡድንም ይህ እንደማይሆንና ውሳኔው የላእላይ ምክር ቤቱ እንደሆነ ቢነገራቸውም በፍጹም በማለት ጉዳዩ ለላእላይ ምክር ቤቱ በድጋሚ ይቅረብልኝ እንዲያውም በነገው ስብሰባ መጥቼ አስረዳለሁ» በሚል ከኮሚነው ጋር ተለያዩበበነገታው ስብሰባ ላይ ሊቀመንበራችንን ስለሚመጡ እንጠብቅ ተብሎ እየጠበቅን እያለን ሰአት በማለፉ ይደወልላቸው ተብሎ ሲደወል በመታመሜ መምጠት አልቻልኩምና ቀጥሉ ተብሉ ፃሳባቸው ለምክር ቤቱ ሲቀርብምክር ቤቱ « ወስነን ወደጨረስነው ጉዳይ ለምን ትመልሱናላችሁ ይህ ያለቀ ስለሆነ አንመለስበትም» ተባለይህ ለሊቀ መንበራችን ሲነገር የተሰጠው መልስ «የአሜሪካው ቡድን ተለውጦ እኔ ማለት ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል አባይነህ ብርፃኑ ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ በሚጓዘው ኮሚቴ ውስጥ የማንካተት ከሆነ ጉዞው መተላለፍ አለበት እኔም ለህክምናዬ ቅድሚያ ስለምሰጥ ወደ አሜሪካ አልፄድም» የሚል አቋም ያዙአዚህ ላይ መታየት ያለበት ልኡካኑ ከተለወጡ የህክምናው ጉዳይ ላይነሳ ካልሆነ ግን ሰበብ ሆኖ ሊቀርብ ማለት ይመሳላል እዚህ ላይ እንግዲህ የላአላይ ምክር ቤት ያሰለፈውን ውሳኔ የማፍረስ ጅምር መጣይህ ደግሞ ቅንጅት ካለው የመተዳደርያ ደንብ ጋር ጨርሶ የማይጣጣም ነው በማለት ለማስረዳት ቢሞከርም ኢንጅነር ኃይሉ ፍንክች ያባ ቢላ ልጅ አሉ ኢንጅነር ጉዞው ይተላለፍ ሚሌንየምን አዚህ አክብረን እንሂድ የሚል ያልነበረ አዲስ ፃሳብ ሲያመጡ «ቀደም ሲል ስብሰባው የሚካሄድ ልኡካኑም የሚሄዱ መሆናቸው ታምኖበት ደብዳቤ በየዛገሩ ላሉ ቻፕተሮች ተጽፎ አስፈላጊው የዝግዖትያዳራሽ ክፍያ ተከፍሎዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ስለሆነ አሁን መለወጡ ችግር አለበት» ቢባሉም አልስማማም አሉምክንያት ያደረጉትም ጤናቸውን አየሆነ መጣና እንዲያውም ጀርመን ያለው ፃኪሜ አሁን በያዝኩልህ ቀጠሮ ካልመጣህ ሌላ ቀጠሮ በአጭሩ አልሰጥህም ስላለኝ አልፄድም» በማለታቸው በቪህ ምክንያት ከሆነ «ቡድኑ በተያዘለት ፕሮግራም ይሂድ እርስዎም በችግራችን አብረውን ለቆሙት ወገኖቻችን የጽሁፍ መልእክት ያሰተላልፉና ህክምናዎን እንደጨረሱ ይምጡልን» ቢባሉም «ብመጣም ከናንተ ጋር አልቀላቀልም» በማለት ወሰኑይህ ለላእላይ ምክር ቤት ሲቀርብ ላእላይ ምክር ቤቱ ታጋሽ በመሆንና የቅንጅትን አንድነት ቅድሚያ በመስጠት ይበጃል ባለው መሰረት አንድ ተጨማሪ ሰው በማድረግ አቶ ክፍሌ ጥግነህ አብረው ሂደው ለማስረዳትና ፃሳባቸውን ለማስለወጥ እንዲሞክሩ ተወስኖ ሄፄደው አነጋገረው ይዘው የመጡት መልስ ግን እጅጉን የሚያሳዝን ሆነ ኢንጅነር የሰጡት መልስ «አላደርገውም ደሞ እኔ በሌለሁበት አሜሪክ ያለውን ችግር አትፈቱትም» የሚል ሆነ ይህ ሰላአላይ ምክር ቤቱ በቀረበ አለት ተጨማሪ ኢንፎርሜሽን ተብሎ በአቶ አባይነህ የተነገረው «የልኡኩ አባላት ወደ አሜሪካ ቢሄዱ በገማ እንቁላልና በበስበሰ ቲማቲም የሚደበደብ መሆኑ» ተነገረ ይህን መሰረት የሌለው ሪፖርት ወደ ጎን ተትቶ ልኡካኑ ወደ የተመደቡበት ፃገራት እንዲሄዱ መመርያ ተሰጠበዚሁ እለት ቤተሰቦቻቸው ስለሞቱባቸው ደጋፊዎቻችን ጉዳይ ቀደም ሲል ተነስቶ አሁን ሄደን ብናነጋግራቸው በአል ከመሆኑም ከብዛተቸውም ለማሰባሰብ ከማስቸገሩም የተነሳ ቸግር ስላለው ጊዜም በቂ ስለሌለ አንድ ዘላቂ ገቢ የሚያገኙበትን ጥናት እንዲያጠና የተመደበው ኮሚቴ ሪፖርት አቀረበ የዚህ ኮሚቴ አባላት ብርቱካን ሚዴቅሳ ሙሉነህ ኢዮኤል ደበበ እሸቱ ነበርን የጥናቱንም ውጤት በተመለከተ «ዘላቂ ገቢ በሚያስገኝ መልኩ ቀርጸን ከጉዞ መልስ ተግባራዊ እንዲሆን» በአቶ አባይነህ ሃሳብ ቀርቦ በዚሁ ተወስነ ጨርሶ ወደ አሜሪካ አልመጣም ያሉት ሊቀመንበራችን አስቀድመው በቤታቸው ባካሄዱት የሚስጥር ስብሰባ የመኢአድን የሥራ አስፈጻሚ አባላት የነበሩትን ግን በአሜሪካው ጉዞ የተካተቱትን ኢንጅነር ግዛቸውን አቶ ብሩክ ከበደን ከከሰመው መኢአድ አስወጥተው ሌሎች ተተኪዎች መረጥኩ ያሉት አስቀድሞ የዚህ ችግር ፈጣሪ የሆኑት ሻለቃ አድማሱ ቅድመ አፍራሽ ተግባር የነበራቸውና እምነት ሊጣልባቸው የማይችሉ መሆናቸው ሲነገር የነበር ቢሆንም ማንም ሳያውቅ በሚስጥር በተከናወነ ስምምነት በሊቀመንበራችን ብቸኛ ውሳኔ በእስር ላይ እያለን ማንንም ሳያማክሩና ለማንም ሳይነግሩ ያውም አብረዋቸው በአንድ ቤት የታሰሩት ዶክተር ያእቆብ ሃይለማርያም ዶክትር ዛይሉ አርአያ ዶክተር በፈቃዱ ደግፌ ኢንጅነር ግዛቸው አቶ ብሩክ አቶ ታምራት ታረቀኝ ሁሉም የላእላይ ምክር ቤት አባላት አብረዋቸው እያሱ ወደ አሜሪካ ለማስታረቅ እንዲመጡ የተወከሉትን በማስቀረት ለማንም ሁኔታውን ሳያሳውቁ ሻለቃ አድማሱንና ዶር በዘብህን ላኩይህ ደግሞ ከኢንጅነር ኃይሉ በስተቀር ሁሉንም ያሳዘነና አያደርጉትም የተባለ ጉዳይ ነበር ድውሦዶሥ ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact