Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የ እምነቴ ፈተና(ደበበ እሸቱ)trial-3.pdf


  • word cloud

የ እምነቴ ፈተና(ደበበ እሸቱ)trial-3.pdf
  • Extraction Summary

ለዚህ መልስ አላገኘሁም ያገኘሁት ነገር ቢኖር ነው የሚለው ዛሳብ ደሞ ያዘኝያም ሆነ ይህም ማለት ከሕብረተሰቡ ጋር መገናኘት አከተመ ማለት ነውኢህአዴግ ግን አዳራሹ በጁ መስተዳድሩ በጁ ሁሉ ነገር በደጁ ስለሆነ እንዳሻው ሕዝብን እየሰበሰበ ያሻውን ፕሮፓጋንዳ ያካሂድብናል ይሁንና የራሱ ደጋፊ ከሚባሉት የቀበሌ መስተዳድርና አባላት ከሚላቸው በስተቀር የሚሰበሰብ አልነበረም እኛም ይህ አግባብ አለመሆኑንና ሕገመንግሥቱ የሚፈቅደውን መብታችንን እየተነፈግን መሆኑን ለሚመለከታቸው ሁሉ አቤት ብንልም መልሰው ወደ አዲስ አበባንም መረከብ የለብንም የሚል አቋም ያኩዙ በአንግባ አንግባ ውይይት ላይ ልደቱና ሞሼ ከኔ ኋላ ነበር የተቀመጡትና የሚያወሩት ሁሉ ይሰማኝ ነበር።

  • Cosine Similarity

እኔ እንደገመትኩትና በአንድ ጋዜጣ ላይ እንዳነበብኩት ንዴቱና አንዲያ መወራጨቱ የመጣው ምናልባት አቶ መኮንን ወይም ምርጫ ቦርድ በጥቅሉ በዚያ የምርጫ ስርአት ላይ ድምጽ እንዲቆጥርና ምርጫውን እንዲመራ በክብር እንግድነት ባለመጋበዙ ይሆናል ይህን ደሞ ቅንጅት አያደርገውም ደሞ ምርጫው ውስጥ የሌለበትንና የቅንጅት ተመራጭ ያልሆኑ ግለሰቦችን ተመርጣችኋል ብሎ እንዲያስቀምጥ ካልሆነ ካለፈው ትምህርት አግኝተናልና አንደግመውም ከዚህ ውጪ የሚያናድደው «ምርጫውን አንቀበልም» ማለቱ ነው ሌላ ስውር ደባ ከሌለው አለቦታው የተሸነቀረ ጉዳይ ነው ይህ በሆነ በሳምንቱ ቅንጅት ለመራጩ ሕዝብ ለድምፅ ባለቤቱ ሕዝብ «ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን አሁንም ለኛ ከሰላማዊ ሂደት ውጪ ሌላ አማራጭ የለንም የደረስንበት ይህን ይመስላል ገዢው መንግሥት ከኔ ወዲያ ገዢ ላሳር በሚል የጉልበተኝነት ስሜት ድጋሚ ምርጫውንም አንድም የቅንጅት ተወዳዳሪ እንዳይገኝ ታዛቢ በቦታው እንዳይደርስ በተደረገበትና በአብዛኛው የቅንጅት ተወዳዳሪዎችም በምርጫ አሸናፊ ለመሆናችን የተፈራረምንበት የገዢው ተወካዮችም የፈረሙበት ሰነድ በጃችን እያለ አለአግባብ በምርጫ ቦርድ በተሰጠ የግፍ መብት እንደገና ለውድድር አንቀርብምአቤት ተብሎበት እያለ የምርጫ ቦርድ አሻፈረኝ በሚል ወገናዊነት የፈጠረው ነው» ባሉበት ሁኔታ ምርጫው ተካሂዶ ልክ የምርጫ ቦርድ ባጠላለፈው ሂደት ገዢው መንግሥት አሸናፊ ሆኖ ቀረበ ይህንን ነው ለሕዝብ ያቀረብነው በሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ጥያቄ ተነስቶ ውይይት ተካሄደለጥያቄዎች መልስ ተሰጠየተነገረ ነገር ቢኖር በምርጫው ሂደትና ምርጫው አለአግባብ እንዴት እንደተከናወነ በተጨባጭ ማስረጃ የቀረበበት ውይይት ነበርከዚህ ውጪ ምንም አይነት ሂደት አልነበረምእንዴት ሆኖ በመስተዳድሩ ፃላፊዎች ሕግ የጣሰ ፀረ ሕዝብ ቅስቀሳ ሊሆን እንደቻለ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ነው እርግጥ ለወያኔ ኢህአዴግ ካድሬዎች የማይጥም ሁሉ እንደፀረ ሕዝብ ሊቆጠር ይችላል ምክንያቱም በነሱ አስተሳሰብ ሕዝብ ማለት ወያኔ ኢህአዴግን የመረጠ ወይም ለሱ ያደረ ብቻ ነው ሕዝቡ በስነስርአትና በኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወደየአዳራሹ መጥቶ ወንበር ሲሞላም በግቢው ውስጥና ሊያዳምጥ በሚችልበት ቦታ ሆኖ ጥያቄውን በፅሁፍ እየላከ መልስ የሚያገኝ ነበር አንጂ ጨርሶ ከስነስርአት ውጪ የሆነበት አንዳችም ቦታ አልነበረም ይልቅስ የወያኔ ኢህአዴግ ካድሬዎች መሳሪያቸውን በማስፈራሪያነት በመጠቀም በሕዝብ መፃል እየተንጎራደዱ ነገር በመፈለግና ብጥብጥ እንዲነሳ ለማድረግ በመነካካት ቢደክሙም ሕዝቡ የሰጠው ምላሸ የደንብ ልብስ ለለበሱ የፖሊስ አባላት በማስታወቅ እርምጃ እንዲወሰድና ስብሰባው በሰላም እንዲጠናቀቅ ማሳካትን ነው ይህ ኢትዮጵያዊ የሕዝብ ጨዋነት ነገር ፈላጊ ካድሬዎችንና አለሥራቸው ገብተው በስልጣናቸው ሊባልጉ የሞከሩትን ጥቂት የደህንነት ሰዎች አበሳጭቷል ይህ ነው ፀረ ህዝብ የተባለውና አዲስ መመሪያ ወጥቶ የቅንጅትን ስብሰባ ያሰናከለው ይህን መሰል ስብስባዎች ከተካፄደና የሕዝቡ ስሜት ለቅንጅት መሆኑ ሲታይ የተወሰደው አማራጭና የማጨናገፊያ መንገድ የቅንጅትን ስብሰባ መከልከል ሆነ። አሁን ገባኝ አንድ ጊዜ ዱሮ ማጅራት መቺ የሚባል በአዲስ አበባ ተስፋፍቶ በነበረበት ወቅት አኔም የዚህ ቡድን ስለባ ሆፔ ነበር የዚያን ጊዜው ማጅራት መቺ አንዱ በሰንጢ ከፊት ለፊት ሲያስፈራራ ከኋላ ያለው ማጅራትን መቶ ጥለው ይዘርፋሉ ማጅራት ይባል እንጂ ያገኙት ቦታ ላይ ነው የሚመቱት እኔን አጋጥሞኝ የነበረው ጆሮ ግንዴ ላይ ነው ያሁኑም ሁኔታ ከዚያ ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም የመሳሪያው አይነት ይለያያል የሚፈለገውም ውጤት የተለያየ ነው አነዚህ ሁለት ጀግኖች» ጨለማን ተገን አድርገው ሰዋራ ቦታ መርጠው ሆነ አንጂ ቀን በአካባቢው ሰው በሚተላለፍበት ሰአት ቢሆን ኖሮ ምን ሊፈጠር ይችል እንደነበር ሳስበው አንኳንም መሸ ብያለሁ ያ ባይሆን ኖሮ በአካባቢው ከፍተኛ አምባጓሮ ተነስቶ በኔ ብቻ ሳይሆን በርካታ ጉዳት ይደርስ ነበር መንግሥት የሕዝብንና የዛገርን ደህንነት እንዲጠብቁ ያስታጠቃቸው በዚህ ዓይነቱ ተራ የከተማ ሸፍትነት ላይ ተሰማርተው በግለሰብ ላይ ይህን አይነት አሳፋሪና ነውር ተግባር ለመፈጸም ደመወዝ መክፈላቸው ያሳዝናል በያዙት መሳሪያ እኔን ቢገድሉ ቅንጅት ምንም አይሆንም እኔ የቅንጅት አባል ነኝ እንጂ ቅንጅት አይደለሁም ቅንጅት ሕዝብ ነው ቅንጅት ኢትዮጵያ ነውና በግለስቦች ሞትና ጉዳት ይበልጡን ቢጠናከር እንጂ አይዳከምም ይልቅስ ይህን መሳይ ተግባር ገዢውን ፓርቲ ለትዝብት የሚያጋልጥ ነውርና ተራ ሥራ ነው ይህ ድርጊት እንደተፈፀመ ዜናው ለ«ኢፍቲን ጋዜጣ በምን መንገድ እንደደረሰው ባይታወቅም ደህንነትን አነጋገርኩ በሚል «ደበበ ተደበደብኩ ይላል ግን ማስረጃ የለውም» በሚል ርዕስ ዘገባ ብሎ አቀረበ በጣም የሚያስገርመው ወሬ የማያጣው ኢፍቲን ምናልባት ድርጊቱን ከፈጸመው ቡድን ጋር ግንኙነት ኖሮት ካልሆነ በስተቀር ሌላ የሚያገኝበት መንገድ ሊኖረው አይችልም የወንበዴ ተግባር የሚፈጸም አካል ጨለማን ተገን አድርጎ ጥቃትና ኢሰብአዊ ተግባር የሚያካሂድ ማስረጃ በማይገኝበት መንገድ መሆኑን ከማንም በላይ ኢፍቲን የሚያውቀው ጉዳይ ነው የሚያሰማራውም ፃዛይል ይህን መመሪያ ሰጥቶ አስጠንቅቆ አንደሚያሰማራ ኢፍቲን አያወቀ ማስረጃ የለም ማለቱ «ከጋዜጠኛ» የማይጠበቅ ድምዳሜ ነው ደሞስ ኢፍቲን የሚሉት ጋዜጣ» አኔን ባለጉዳዩን ለማነጋገርና ሁኔታውን ለመረዳት ለምን አልሞከረም የሚል ጥያቄ መጣብኝና መልሱንም እኔው አገኘሁት የቅንጅት አባል ስለሆንኩ ሊያደርገው አልፈለገምና ነው ያንድ ወገን ዘገባ ያቀረበው በዓይኔ ስር የደረሰብኝ ጉዳት ይህነበር። ነገሩ የሚያሳዝንም የሚያስተዛዝብም ነው ለነገሩ ማንም ሰው ሃሳቡን በነጻ የመግለጽ የየትኛውም ሕጋዊ ፓርቲ አባል የመሆን በሃሳብና በዓላማ ደረጃ መቃወም በሕገ መንግሥቱ ላይ ተደንግጎ የተሰጠው መብቱ ነው የቅንጅት ውህደት በፊርማ ከጸደቀና አባላቱም ያንን በጭብጨባ ካረጋገጡ በኋላ የስልጣን ሽግግሩ ያለአንዳች ውጣ ውረድ አንድም ድምፅ ሳይሰረቅ ኮረጆም ሳይገለበጥየካርድ ውዝግብ ሳይታይ በፍቅርና በሰላም ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ሆነጉ በዚህ ጊዜ ነበር ወደ መፀዳጃ ቤት ስፄድ ብርቱካን ሚዴቅሳ ብቻዋን ቁጭ ብላ በትንሽ ወረቀት ላይ ስትጽፍ ያየኋት ስመለስ ቶሎ እንድትመጣና ተራዋ መድረሱን ነግሬያት ወደ አዳራሸ ገባሁ ስገባ ትፈለጋለች ተመልሼ ጠራቷት ንግግሯን ለማድረግ ወደ መድረኩ ስትወጣ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ በዚህ ወቅት ባደረገችው ንግግር ውስጥ ነበር ቅንጅት ከምንምነት አልፎ አሁን መንፈስ ሆኗል ያ መንፈስ ነው ለእኛም ለደጋፊ ዎቻችንም ብርታትን የሚሰጠን» ያለችው እውነት ነው ትክክለኛ ስያሜ ነው እውነትም ቅንጅት መንፈስ ሆኖ ነው በዚያ ፍጥነት በያንዳንዱ የሕበረተሰብ አባል ህሊና ውስጥ በፍቅርና በአክብሮት ሊቀረፅ የበቃው ከውህደቱ ማግስት ጀምሮ በየአንዳንዱ የአመራር አባልና በሌሎችም የቅንጅት ሰራተኞች ላይ ደህንነት ትኩረት በማድረግ ተስፋ ለማስቆረጥ ግራ ለማጋባት ለማስፈራራት መሯሯጡን እየተከታተለ ማስቸገሩን ቀጠሰለ በመስከረም ሕዝባዊ ስብሰባ ለማካፄድ የመስቀል አደባባይን መጠቀም አንዲቻል ሕብረትና ቅንጅት ለመስተዳድሩ ጥያቄ አቀረቡ ለጥያቄው የተስጠው መልስ «ሕገ መንግሥቱን መቀበላችሁንና ማክበራችሁን የምርጫውን ውሳኔ መቀበላችሁን ፓርላማም እንደምትገቡ በማመልከቻው ላይ በግልጽ ካላስቀመጣችሁ አንፈቅድም» የሚል ነበር ይህን ማድረግ ደሞ ጨርሶ የማይሞከር ነውሕዝባዊ ስብሰባ ማድረግ በሕገ መንግሥቱ ላይ በግልፅ የተቀመጠ መብት ነው ስብሰባም ለማድረግ ፈቃድ መጠየቅ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው በሕገመንግሥቱ ላይ ባልተጠቀሰ መልኩ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጥ ልክ እንደ ሰኔ አንዱ ዓይነት እልቂት ለመፈጸም የተሰመረ «ቀይ» መስመር መሆኑ ተቃዋሜሚ ዎች ገባቸው ሕዝብን ከእልቂትና ከመክራ ለመጠበቅ ሕዝባዊ ስብሰባውን በመተው ሌሳ አማራጭ እንዲፈለግ ተወሰነ መንግሥት ሰልፉን በጽሁፍና በግልጽ ያንን ቅድመ ሁኔታ ተቀብላችሁ የምርጫውን ውጤት ተቀባዮች የሚያደርጋችሁን ቃላችሁን ካልሰጣችሁ አልፈቅድም ማለቱን በተመለከተ የተሰጠውን የተቃዋሚዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ልክ የነአና ጎሜዝንና የካርተር ማዕከልን የምርጫ ሪፖርት ለራሱ በሚበጀው መልክ እንዳቀረበው ሁሉ ተቃዋሚዎች ሰልፉን ሰረዙት በማለት አጣጥሎ አቀረበው ሕዝብ ግን ያውቃል ይረዳልና ፃሃቅ እንዳልተዘገበ ተገንዝቧል ሰልፉ በመሰረዙ በርካታ አባሎችና ደጋፊዎች በስልክም በግምባርም በመምጣት ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉም በፋክስ በስልክና በኢሜይል ኢህአዴግ እንደማይፈቅድ የታወቀ ነው ለምን ሰልፉ ይሰረዛል። የኢትዮጵያ ህዝብ በነፃነት አጦት አጅግ ከተሰቃዩት አና በዚህም ምክንያች አጅግ መሠረታዊ የሚባሉ ቁሳዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ተስኖት የውጭ እርጥባን ከሚያሰፈልጋቸው ጥቂት የዓላማችን ህዝቦች አንዱ ነው ነፃነትና ብልፅግናን በመሻት ከአፄው አሰተዳደር ጋር ያደረገው ትግል ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ብዙ ክብር በማይሰጡ የግራ ኃይሎች ተነጠቀ አነዚሁ ኃይሎች በአብዛኛው ለስልጣን ባደረጉት ትግል የበለጠ ጉልበት ባለውና ክነሱም በባስ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ምንም ደንታ በማይሰጠው የወታደር ኃይል ተቀማ በማህበረሰቡ ላይም ዝግናኝ የሆነ ጭፍጨፋና በገዛ አገሩ ላይ ባይተዋርነት እአስከሚሰማው ድረስ በጥቂት የስልጣን ሱስ ባስከራቸው ወገኖቹ ስር ማቀቀ ይህ የ ዓመት የባርነት ዘመን በሌሎች ወገኖቹ ቆራጥ ችግል ሲገረሰስ ምንም እንኳን እነዚህ ወገኖቹ ይዘውት የመጡት አጀንዳ ሙሉ በሙሉ ባይስማማውም የደርግን አስከፊ ስርዓት መዋጋታቸው ስልጣኑን ሲረከቡ የነበረውን የዓለም አቀፍ የነፃነትና የዲሞክራሲ አዝማሚያ ከግምት በማስገባትና ይህም አዝማሚያ ድርጅቱን በመጠኑም ቢሆን ወደ ለዘብተኝነት ይገፋዋል በሚል በተወሰነ ደረጃ ድጋፉን ቸሯቸው ነበር ከዚህ በተጨማሪም ሥልጣኑን የተረከበው ኢህአዴግ የዓለምን ሁኔታ መቀየር ከግምት በማስክባት በትግሉ ውስጥ ይዞት የነበረውን አክራሪ የኮሚኒስት ርዕዮተ ዓለም ቢያንስ በዕለት ተዕለት ፕሮፓጋንዳው በመተው ስለ ነዓነትና ዴሞክራሲ መሰበኩ ህዝቡ ለድርጅቱ ቀላል የማይባል አወንታዊ አመለካከት እንዲኖረው አድርጓል ይህንን የመጀመሪያ የህዝብ ድጋፍ ኢህአዴግ በዘላቂነት ይዞት ሊጓዝ አልቻለም ምንም እንኳን በኢኮኖሚ ፖሊሲ ደረጃ ለዘብተኛ ፖሊሲ ለመከተል ያለውን ፍላጎት ቢያሳይም ለፖለቲካ ስልጣኑ ያለው ቀናኢነት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኛነት ጥያቄ ውስጥ ከመክተቱም በላይ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉትን ልዩነቶች ከማጥበብ ይልቅ ማስፋትን አንደየሥልጣን መቆያ አስትራቴጂ መውሰዱ ብዙውን የህብረተሰብ ክፍል አላስደሰተውም ከ ዓመት የሥልጣን ቆይታ በተግባር ጠብ የማይል የዲሞክራሲ ዲስኩርና ሁለት የይስሙላ ምርጫ በላ ኢህአዴግ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለው ቁርጠኛት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ወዳጆቹም ጭምር ክፉኛ ጥያቄ ውስጥ በመግባቱ በአንድ በኩልና የዓለም የፖለቲካ አካሄድ የዴሞክራሲና መልካም አስተዳደርን እንደ ሁነኛ የእርዳታ መስፈርት አድርጎ መውሰዱ በሌላ በኩል ተደማምረው ኢህአዴግ በወሬ ደረጃ የሚያውቀውን ዴሞክራሲ በተመጠነና ሊቆጣጠረው በሚችለው ዐዐ ከ መልኩም ቢሆን ለመተግበር መሞከር በስልጣን ለመቆየት አስፈላ እንደሆነ በመረዳት ነበር ወደ ግንቦት ዓም ምርጫ የመጣውወደ ምርጫው መዳረሻም ላይ ይህንን የተመጠነ ዲሞክራሲ ለመፈተን የተለያዩ ምርጫዎች በመጠኑም ቢሆን ፉክክር ያለበት ለማድረግ የሚረዱና ምናልባትም ሳይታወቅ እግረ መንገዳቸውን የማህበረሰቡን ስነልቦና ለዲሞክራሲ ቀስ በቀስ የሚያዘጋጁ አርምጃዎች ተወስደዋል የኢትዮጵያ ህዝብ በደርግ የ ዓመት የጨለማ ዘመን ፍፁም ተነፍጎት የቆየውን ሰላም ዲሞክራሲና ብልፅግናን በኢህአዴግ የ ዓመት የአገዛዝ ዘመን አገኛለሁ ብሎ በተስፋ ሲጠብቅ የማይጨበጥ ጉም ሆነውበት እያደር ተስፋውም እየደበቨሸዘ ለኢህአዴግ የሰጠውንም ከዛሬ ነገ ይሻሻላል የሚል በትፅግስት የመጠበቅ ስሜት አያሟጠጠ በሌሎች አገሮች በወሬ ደረጃ የሚሰማውን የነፃነትና የዲሞክራሲ ሂደት በአገሪቱ ተፈፅሞ ለማየት እየናፈቀ ባለበት ሁኔታ ነው የግንቦት ምርጫ መዳረሻ ላይ የደረሰው በሌላ በኩል የኢህአዴግን የ ዓመት አገዛዝ በአንድ ምክንያት ወይንም በሌላ በተደራጀ መልኩ ሲቃወሙ የነበሩ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች በተናጠል የሚያደርጉት ትግል ውጤታማ ሊሆን እንዳልቻለ የተገነዘቡበትና አውነተኛ ለውጥ ለማምጣት በመሀከላቸው ያሉትን ልዩነቶች አስወግደውና ተባብረው በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ትግሉ ህዝቡን ማሳተፍ እንዳለባቸው የተረዱበት ይህንንም ለማድረግ አንዲያስችላቸው በራሳቸውና አንዳንዴም በሲቪክ ማህበረሰቡ ግፊት የትብብር ውይይቶች አድርገው በጋራ አብሮ ለመስራት ከምንግዜውም በላይ ቁርጠኝነት ባሳዩበት ሁኔታ ነው ወደ ግንቦት ምርጫ የተዳረሱት የእዚህ ሁሉ ሁኔታዎች ድምር ውጤት የኢትዮጵያ ህዝብ የ ዓም ምርጫን በተለየ መልክ አንዲያየው አድርጎታል ምርጫው ፕኘቀድሞዎቹ የተለየ እንደሚሆን በሌሎች አገሮች ያየውና የሰማው የነፃነትና የዲሞክራሲ ዘመን በአገሩም አውን ሊሆን አንደሚችል የተገነዘበበች አስከምርጫው አለት ድረስ በነበሩት የምርጫ እንቅስቃሴዎች ጊዜ በተወሰነ ደረጃ የነባነትን ልዩ ጣዕም ማጣጣም የጀመረበት ስለወደፊቱ ኑሮው በልቡ ውስጥ ትልቅ ተስፋ የተጫረበት ከሁሉም በላይ ደግሞ ምናልባትም በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ እውነተኛ የወሳኝነት ስሜት ፀሀዕፀበበፀበ ያገኘበት በውስጡ ተብትቦ ይዞት የነበረውን የመንግሥትን የመፍራት ስሜት በፍፁም አውልቆ የጣዘበት ደረጃ ላይ አድርሶታል። በጊዜው በህዝቡ ዘንድ የታየው የተስፋ ስሜትና ከዚሁ ጋር የተያያዘው ከውስጥ የመነጨ ደስታ ማንም በፈለገ ጊዜ የሚያጠፋው ጊዜያዊ ስሜት ሳይሆን ከመሰረታዊ ማንነቱ ጋር የተያያዘና የዚሁ አዲስ ማንነቱ መግለጫ ነበር ይህንን ህዝብ ወደቅድመ ምርጫ ነፃነትአልባ ህይወቱና ማንነቱ ለመመለስ በፍፁም የሚቻል አይሆንም ይህንን ለማድረግ መሞከር ውጤቱ ለአገሪቱ አጅግ አስከፊ ነው የሚሆነው ይህን የምንለው የምርጫውን ውጤት በተመለከተ ያለውን ችግር በሚመለክት ብቻ አይደለም የምርጫውን ውጤት በተመለከተ ያለው ችግር የመንግስትን በትረ ስልጣን ማን ይይዘዋል የሚለውን ጉዳይ የሚመለከተው አንዱና በኛ ግምት ትንሹ ጉዳይ ሲሆን ለቅንጅታችንም ሆነ ለህዝቡ ዋናውና ምናልባትም ወሳኙ ጥያቄ ከአሁን በኋላ በኢትዮጵያችን ውስጥ የሚኖረው የመንግስት አይነት ምን አይነት ይሆናል የሚለው ነው ለዚህም ነው ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው ችግር ቅንጅቱ ሁሌም የሚያተኩረው እዚህ ወሳኝ ጉዳይ ላይ የሆነው ምርጫውን ተከትሎ የተፈጠረው በቅንጅቱ አይታ ብዙ የሚያከራክር አይደለም አመለካከታችን ነፃ ከሆኑ አለም አቀፍ ታዛቢዎች ትዝብት ጋር አብሮ የሚሄድ ነው ይህም እስከ ግንቦት ድረስ የነበረው አካሄፄድ የተከሰቱት ችግሮችና በጊዜው በተለያየ መንገድ የገለፅናቸው ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በአብዛኛው ያሉንን አመለካከቶች ለህዝቡ ለመግለፅ ምርጫው ሊደርስ አንድ ሁለት ሳምንታት እስኪቀረው ድረስ ብዙ አገቅፋት ላለይገጥወን ለማቅረብ የቻልንበት ስለቪህም ፉክክሩ በአብዛኛው በሀሳብ ላይ የነበረና ዴሞክራሲያዊ የሚባል እንደነበር በምርጨው ዕለት በተወሰኑ ዞኖች ከተከሰቱት ግልፅ ችግሮች ለምሳሌ ምስራቅ ጎጃም ደቡብ ጎንደር አፋር ሲዳማ ወላይታና ሌሎችም የተወሰኑ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ውስጥ ባሉ ወረዳዎች ወዘተ በስተቀር በአብዛኛው ቦታ በሰላማዊ መንገድ የተካሄደ አንደነበር ይህም ሆኖ በእነዚህና በሌሎች ቦታዎች የምርጨ ታዛቢዎቻችንን የማዋከብና የማባረር አርምጃ በተለይ ለምርጫው አንድ ሁለት ቀን ሲቀረው በብዛት የተክሰተ መሆኑን የምርጫው ዋና ችግር የተከሰተው ከሰኞ ግንቦት ቀን ጀምሮ እንደነበር በዚህም ጊዜ የምርጫ ህጉ በሚያዘው መሰረት አሁድ ማታ ቆጠራ በተጀመረባቸውና ሰኞ ጠዋት በምርጫ ጣቢያው ውጤት በተገለፀባቸው ቦታዎች ላይ ብዙ ችግር አለመክሰቱ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ተቃዋሚዎች በተለይ ደግሞ ቅንጅቱ በአብዛኛው ቦታ እየመራ እንደሚገኝ ዝርዝር መረጃ ከየጣቢያው እያገኘን ነበር በዚህም መሰረት እስከ ስኞ ሰዓት በደረሱት ወደ ግማሽ ያህል በምርጫ ውጤቱ መሰረት ተቃዋሚዎች በአርግጠኛነት እያሸነፉ አንደሚገኙ ግልፅ ነበር ይህ በዚህ ሁኔታ እንዳለና የቀሪውን ግማሽ ውጤት በመጠባበቅ ላይ እያለን ሰኞ ማታ ኢህአዴግ ግልፅ በሆነና ምናልባትም አንድ ተመልካች በጊዜው እንዳለው አይን ያወጣ መፈንቅለ መንግስት በሚመስል መልኩ ምርጫውን ማሸነፉን በሬዲዮና በቴሌቪዥን መግለፁ ከዚያች ማታ ጀምሮ በቀሪዎቹ የምርጫ ውጤት ባልተገለፀባቸውና ቆጠራ ባላለቀባቸው ቦታዎች ላይ የሚገኙ የተቃዋሚ ምርጫ ታዛቢዎች መባረራቸው ተቃዋሚዎች ከታዛቢዎቻቸው የሚደርሳቸው ውጤት መቆሙና አንደማንኛውም ሰው በሚቀጥሉት ቀናት ግድም ውጤቱን ፍፁም ማወቅ አንደተሳናቸው ቆይቶ ደግሞ «ጊዜያዊ ውጤት» በሚል ሽፋን በሬዲዮና በቴሌቪዥን የኢህአዴግን አሸናፊነት ውጤት ሲነገር መስማታቸው በአጠቃላይ ግን እስከ ስኞ ግንቦት የነበረው ግልፅ ሀ ቪ የምርጫና የቆጠራ አሰራር ፈፅሞ ተቀይሮ ኢህአዴግ አንደፈለገ በሚደርገው ዝግ አሰራር መለወጡ በዚህም ምክንያት በአብዛኛው ከሰኞ በኋላ ተቆጠፋ የተባሉትና ተቃዋሚዎች ያልተገኘ ባቸው የምርጫ ወረዳ ውጤቶች በምንም የነ ምርጫ መስፈርት ተአማኒነት እንደሌላቸው ግልፅ መሆኑ በአጠቃላይ በትልቅ ተስፋ የተጀመረው የግንቦት ምርጫ ከሰኞ ግንቦት ቀን ጀምሮ በገዢው ፓርቲና አርሱ በሚያዛቸው ታጣቂዎች በፈፀሙት ግልፅ ዝርፊያ የህዝቡ ድምፅ ተቀምቷል እንግዲህ የግንቦቱ ምርጫ ተአማኒነት ችግር ውስጥ መግባቱ ግልፅ ከሆነበት አለት ጀምሮ በቅንጅቱና በህዝቡ በኩል የነበረው ጥያቄ የህዝብ ድምፅ ይከበር» የሚለው የማያሻማ ጥያቄ ነበር በዚህ ወቅት ቅንጅቱ ይከተለው የነበረው መስመር በአንድ በኩል መንግስት በጉልበት የምርጫውን ውጤት ለመቀልበስ የሚያደርገውን አንቅስቃሴ አጥብቆም አምርሮ መቃወም በሌላ በኩል ደግሞ በዚሁ ምክንያት በህዝቡ ውስጥ የተፈጠረው እያደገ የመጣውን ቁጭትና ንዴት መንግስት ሆነ ብሎ ከሚወስዳቸው የትንኮሳ ስራዎች ጋር ተደማምሮ ህብረሰተሰቡን አጉል ግጭት ውስጥ እንዳይከተውና በዚሁ ምክንያት የአገሪቱ አንድነትና ዘላቂ ሰላም እንዳይታወክ አብሮም የተጀመረው ዴሞክራሲያዊ ሂደት ጭራሹኑ እንዳይቀለበስ መከላከል ነበር በዚሁም ዙሪያ ግልፅ የሆነ የምርጫ ችግር የተፈጠረባቸው ቦታዎች በገለልተኛ ወገን እንዲጣሩ መግፋትና በዚህም የዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ተአማኒነት እንደገና አንዲረጋገጥ መሞከር ይህ እስከሚሆን ድረስ ደግሞ ህዝቡ እንዲረጋጋ መማፀን በጊዜው ቅንጅቱ ይወስዳቸው የነበሩ የትግል መስመሮች ነበሩ ይህም አካፄድ ድርጅቱ ከምንም በላይ ለአገሪቱ ሰላምና ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ያለውን ጥልቅ አምነት የሚያረጋግጡ ናቸው። ቅገጅት ስስገደነትና ሰዴሞክራሲ ሰሞኑን ደሞ ጉንፋን ያዘኝና ያ ሰበበኛ ወገቤ ምስቅልቅሉ ወጥቶ በሕክምና ላይ ብሆንም ለዶክተር ቀጠሮ ወደ አሜሪካ የምፄድበትም ጊዜ በማለፉ እዚሁ በሃገር ልጆች ህክምና እየተደረገልኝ በቀን ለጥቂት ሰአታት ወደ ቢሮ እገባለሁ ወደ ቢሮ ስገባና ስወጣ ከወንድም ጓደኛዬ ምናሴ ወንድም አገኘሁ ጋር ነው ጠዋት መኪናቸውን አእቢሯችን ያቆሙ የጸጥታ ሰራተኞች የአመራር አባላት በገቡ በወጡ ቁጥር እየተከተሉ ሰላም ነስተው ተመልሰው እነበሩበት ይቆማሉ ቀደም ሲል ወደ ቢሯችን ጠጋ ብለው ነበር የሚጠብቁት አሁን አሁን በሁሉም መውጫ በሮች ላይ ይቆሙና አንዱ ለሌላው ባንተ በኩል መጣ በመባባል በሞባይል አየተጠቋቋሙ ነው የሚጠብቁት ቅዳሜ መከረም ወደ አራት ሰአት ላይ ከሃኪም ቤት መልስ ወደ ቢሮ ስገባ ጠባቂው ከነመኪናው ጥግ ይዞ መግቢያው ላይ አለ ቢሮ ገብቼ ወደ ስድስት ሰአት ላይ ወደ ቤቴ ስሄድም ያ ጠባቂ ጸሀይ ቀቅሎት ከፊት ወንበር ወደኋላው ወንበር ፄዶ በሩን ሁሉ ክፍት አድርጎ ተኝቷል አጠገቡ ስንደርስ ቀና ቢልም ይህን ያህልም ትኩረት አልሰጠንም ደክሞታል ለዚህ ተብሎ የሚወጣው ነዳጅ የመኪናው መጉላላት የሰዎቹ የቀን ወጪ ጉልበታቸው ለፃገር በሚጠቅም ተግባር ላይ ቢውል ምን ያህል ጥቅም ባስገኘ ነበር ሌላ ሙያ ባይኖራቸው እንኪን በልማት ሥራ ላይ ቢሰማሩ የተሻለ ነበር በዚሁ እለት ቢሮ እንደገባሁ ውጭ ጉዳይ ሜኒስቴር አጠገብ ካለው የደህንነት ቢሮ አንድ ወዳጄ ደውሎ አንድ ወረቀት በቅንጅት ስም የሚበተን ተዘጋጅቶ አንድ ኮፒ አውጠቼልፃለሁ ሰው ላክና ከተለመደው ቦታ አስወስድ አለኝ ቀደም ብሎ ወረቀቱ የደረሰኝ ቢሆንም ምናልባት ሌላ ሊሆን ይችላል በሚል ሰው ልኬ አስመጣሁት ያው ነው የመስቀል በዓልን ግርግር የፈጠሩት የቅንጅ አባላት ናቸው ለማለት በሚያዙ ሰዎች ኪስ ውስጥ አየተክተተ ፊልም አስነስቶ ቅንጅትን ከሕዝብ ለማጣላት ለመወንጀል የተዘጋጀ ወረቀት ነው እንዲህ አይነቱን ተንኮል ደርግ በኢህአፓ አባላት ላይ ሲጠቀምበት የነበረና ሁሉም ያወቀው ያረጀ ያፈጀ ብልጥነት በመሆኑ ሰሚና ተቀባይ አያገኝም ለወረቀት ለቀለም ለሚበትኑት ሰዎች ያንን ታይፕ ላደረጉት የሚከፈለው ገንዘብ በችግር ለሚቆሉት ወገኖች መርጃ ቢሆን አይሻልም ነበር። ምናልባትም ዶር ያፅቆብ የተጣሰበት ሕዝባዊና ዛገራዊ አደራ ከብዶትኢትዮጵያዊ ጨዋነት ይዞት አባባሉን ወደጎን ባይተወውና ውልቅ ብሎ ቢወጣ አለያም ካልፈለግህ አንተው ውጣ እንጂ እኔስ ፃገሬን ጥዬ አልወጣም ቢል ኖሮ ምን ሊከተል ይቸል ነበርን ምንልባትም ምን ጊዜም በተጠንቀቅ የሚጠብቁት ሰዎች ዶር ያእቆብን ከመሰብሰቢያው ቦታ ሲወጣ አፋፍሰው ገቢ ያደርጉት ነበር ማለት ይቻላል ከገባ በኋላ ደሞ ይረሳል ወይም በጊዜ ቀጠሮ ዓመታት ያሳልፍ ነበር በትእግስት ታለፈ በበነጋው ድርድሩ ሊከፄድ ወደታቀደበት ቦታ የተቃዋሚ ፓርቲ ተደራዳሪዎች ሲደርሱ በገዢው ፓርቲ በኩል የጠበቋቸው ተደራዳሪዎች ሳይሆኑ የተገኘ ት አቶ በረከትና አቶ ሴኮ ነበሩ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በኩል ደሞ ዶር በየነዶር መረራ ዶር ብርዛኑ ዶር በፈቃዱ ኢንጅነር ግዛቸው ሲሆኑ በገዢው ፓርቲ በኩል የቀረቡት ተደራዳሪዎች የጉልበት የሥልጣንና የማርክስና አብዮታዊ ንቃት እንጂ ሌላ የሚታይባቸው አይደሉምይህም ለጉዳዩ የተሰጠውን ክብደት ምን ያህል አናሳ ሆኖ አንደተወሰደና ለይስሙላ የተደረገ መሆኑን አሳዬ ወይም ታማኝና ብቃት ያላቸው ሰዎች ከእነዚህ በላይ ወይም ከነዚህ ውጪ ማግኘት እንዳልተቻለ ጠቆመ ድርድሩ ቀጥሎ በዕለቱ አጀንዳ ላይ ተወያይተውበት ወደፊት እንደአስፈላጊነቱ ይታከልበታል በሚል ግንዛቤና ከጠቅላይ ሚኒስትሩም «በማንኛውም ጉዳይ ላይ» የተባለውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለጊዜው ስምምነት የተደረሰባቸውን ነጥቦች በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ ያ በሆነ ማግሥት ተቃዋሜ ዎች ተጨማሪ ያሉትን የመደራደርያ አጀንዳ ይዘው በመቅረብ ይጨመሩልን ሲሉ የገዢው ፓርቲ ተደራዳሪዎች መሬት ከፍ ሰማይ ዝቅ ቢል ከትላንቱ ውጪ አንድም አይታሰብም በማለት በምንም ጉዳይ ላይ መወያየት እንችላለን የተባለውን ቃል ናዱት ብዙ ማግባባትና ንግግር ሊደረግ ቢሞከርም ተቀባይነት ባለማግኘቱ ተቃዋሚዎች አንግዲያው ድርድሩ ይቋረጥ እንጂ በዚህ መልክ መቀጠል አንችልም አሉ ትናንት «በቀረበው የመደራደሪያ ነጥብ ላይ ተስማሙ ተብሎ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረት ድርድሩ መቋረጡንም እናሳውቅ ቢባል በገዢው ፓርቲ በኩል አያስፈልግም ተባለ ሕብረትና ቅንጅት በቅንጅት ጽቤት በመገናኘትና የነጻውን ፕሬስ አባላት በመጥራት ድርድሩ የተቋረጠ መሆኑን ገለጽ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ይህን ጉዳይ በተመለከተ አንዳችም ዘገባ ሳያቀርቡ አደሩ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዘገባውን በጥሩ ሁኔታ በማቅረብ ሕዝብ እንዲያውቀው አደረገ የፓርላማው መክፈቻ ወቅት ተቃርቧል ተመዝገቡ እየተባለ ለተመራጮች ጥሪ እየተደረገ ነውበተለይ በቅንጅት በኩል ስለመግባት አለመግባት ውሳኔ በላአላይ ምክር ቤቱ የሚወሰን በመሆኑ አስቸኪይ ስበሰባ ተጠርቶ በጉዳዩ ላይ ለመወያየት ተወስኖ ለአባላት ጥሪ ተላለፈ ጋብ ብለው የነበሩት የደህንነት አባላት ድርድሩ ለምን ተቋረጠ። በሚል ይመስላል እንደገና የቅንጅትን አመራሮች በወከባ መከራቸውን ማሳየታቸውን ቀጠሉ ቅዳሜ በጠዋቱ ነው ወደስብሰባ አዳራሽ የገባነውሁሉም ይህን ወሳኝ የሆነ አጀንዳ ለመቋጨት በፃሳብ ተለያይቶም ቢሆን «የቱ ነው የሚሻለውን» አንግቦ ያንን ለመወሰን ነው የሚጠብቀውበቅድሚያ እንዴት እንሂድበት የሚል ሃሳብ ቀርቦ ገሚሱ በድምጽ ብልጫ እንወስን ሲል ሌላው ወገን ደሞ ይህ ለፃገራችንና ለመራጭ ወገናችን ከፍተኝ ዋጋ ያለው ጉዳይ በድምጽ ብልጫ የሚወሰን ሳይሆን በሙሉ ድምጽ ያለምንም ተቃውሞ ወይም ድበጸ ተአቅቦ የሚያልፍበትንአንድ የሚያደርገንንየሚያስማማንን መንገድ መሻት ይኖርብናል የሚለው ዛሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ በዚሁ ልንሄድበት እንድንችል እንዴት ይከናወን የሚለውን ዶር ብርፃኑ በቫቲንን የምርጫ አካፄድ እናድርገው የሚል ዛሳብ አቀረበበርንታዎች ምን ማለት እንደሆነ ስለማናውቀው ሲያስረዳ «በመጀመርያ ምርጫ ድምጽ እንሰጣለን ሙሉ ድምጽ ካልተገኘ ደሞ እንደገና ተወያይተን ዳግመኛ ድምጽ እንሰጣለን አሁንም ሙሉ ድምጽ ካልተገኘ ለሶስተኛ ጊዜ ድምጽ ይሰጥና ያ በአብላጫ ድምጽ ይወሰናል ሙሉ ድምጽም ከተገኝ እሰየው» አለን ይህን አካሄድ አብላጫው ቤት ስለተቀበለው በዚሁ ቀጠለአንድ ጊዜ ለመጨረሻ ሃሳባችንን እናንሸራሽር ተብሎ ከሁሉም አቅጣጫ ፃሳብ ከተሰነዘረ በኋላ የመጀመርያው ድምጽ ተሰጥቶ የተፈለገው ባለመገኘቱ ለሌሳ ድምጽ አንደገና በጉዳዩ ላይ ውይይት መካፄድ ጀመረና ብዙ ዛሳብ ወጥቶ ወርዶ ጉምጉምታም ተካሂዶ ውስጥ ውስጡን በሹክሹክታ ፃሜትና አሉባልታም ተወርቶ እረፍት ሆነና ለምሳ ወጣን በምሳ ወቅት ሁሉም የቻለውን ያህል አንዲወያይና እንዲነጋገር በፃሳብም መቀራረብ እንዲችል አድሉ ቢገኝም ከምሳ በኋላም በተደረገ የድምጽ ቆጠራ የተፈለገው መገኘት አለመገኘቱን ከፈጣሪ በቀር የሚያውቅ አልነበረምአርግጥ በመፃላችን መግባት የሚፈልግ መኖሩ ጨርሶ አያጠያይቅምመግባቱ የሚሰጠው ጥቅም ምንድን ነው ሲባል ግን አለመግባት ያገኘውን ማስረዳትና ማሳመን መግባት የሚለው አለማግኘቱ ይታያልጥቂቱ ደምወዝ ከማግኘትና ሥራ ከማግኘት ጋር ያያይዘዋል ሌላው እንሞክር ይላል አብዛኛው ግን የሚታይም የሚሞክርም የለም ሕጉ ሁሉ ተለውጦ ደንቡ ሁሉ ፈርሶ በአዲስ ተተክቶ ለገዢው ፓርቲ በሚጠቅም መልኩ የተሠራ ቤት ውስጥ ብንገባ ጠቀሜታ የለውም መሳቂያ ነው የምንሆነው የሚል ው ስለዚህም ውይይቱ ብቻ እንዲቀጥልና ወደ አንድ ወገን የሚያሰባስብ ሁኔታ ለመፍጠር ተሞክሮ በመጠኑ ከጠዋቱ የተለየ ሁኔታ በታይም ጥቂት አሁንም መግባት ይሻላል የሚሉ በጣት የሚቆጠሩ በመኖራቸው ጉዳዩ እንዲሁ ድምጽ ሳይሰጥ እንዲያድርና ነገ በጠዋት ተገናኝን እንድንደመድመው ስምምነት ተደርሶ ያየን ቅዳሜ ሙሉ ቀን ከተካፄደ የላአላይ ምክር ቤት ስብሰባ እንደወጣን ዶር ብርፃኑ በየዓመቱ የመስቀልን በአል ምክንያት በማድረግ በሚያዘጋጀው የመገናኛ ምሽት ለመገኘት ወደቤቱ ስንሄድ በግብዣው ላይ ያልተጠሩት የደህነነት አባላት ከፊት ከሄላ አጅበውን ደረስንፈ ከተጠራነው መዛል ሞሼና ልደቱ አልተገኘ ም። በሚል ነጻ የሆነ ምርጫ ቀርቦ «እንዲያውም አሁን በስፋት በቀረበው ሃሳብ መሰረት ውይይቱ ተከሂዶ ሰውሳኔ ግን ሁላችንም የሰማነውንና የውይይታችንን ውጤት ይዘን አድረንበት ከራሳችንም ጋር በበቂ መክረንበት ለነገ ተገናኝተን ብንወስን» የሚለው ፃሳብ ተቀባይነት በማግኘ ቱ ውይይቱ ቀጠለ ውይይቱ በመካፄድ ላይ እንዳለ አንድ አባል ካጋጠማቸውና ከስብሰባው አዳራሽ ውጪ ተኮልኩለው ሰው አላስገባ አላስወጣ በማለት በማስፈራራት ነውር ተግባር በመፈጸም የሚያደርጉትን ያሳጣቸውን የደህንነት ሰዎች ነን ባዮችን አሰመልክቶ በጊዜ እንፈሂድ አጉል ነው በማለት ፃሳብ አቀረቡ ማሳሰቢያው ጥሩ ነው ግን እነሱም የሚፈልጉት አለመሰብሰባችንንና ውሳኔውን በወከባ ግራ ለማጋባት በመሆኑ ስብሰባችንን እንቀጥል ተብሎ ስብሰባው ቀጠለ ያሁኑ የቀትር በኋላ ስብሰባ ከጠዋቱ በጣሙን በተለየና መግባባትና ተጨማሪ የሆኑ ፃሳቦችና አመለካከቶች የተመላለሱበት ሆኖ ከማታው በሁለት ሰአት ተኩል ለውሳኔ ቀረበ ወደ ውሳኔ ለመድረስ እንዲያስችልና ድምጽ አሰጣጡም ቀደም ሲል በተደረሰበት ውሳፄ መሰረት ሶስት ጊዜ ድምጽ ተሰጥቶበት በሁለቱ የሚገኘው ድምጽ ሁለት ሶስተኛ ማስገኘት ካልተቻለ በሶስተኛው ድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚገኘው ድምጽ ወሳኝ ሆኖ በዚያው እንዲያልፍ ተወስኖ ወደ ድምጽ ተገባ ሁለቱ የውሳኔ ፃሳቦች በተሰጠው ማብራሪያና በተደረገው የዛሳብ ልውውጥ መሰረት መግባት ወይም አለመግባት ለሚለው ድምጽ ሲጠየቅ መግባት የሚለውን የሚደግፍ ሲባል አንድም ድምጽ አልተገኘ ም ተቃውሞ ሲባልም ምንም ድጋፍ በመጥፋቱ በዚያ ታልፎ አለመግባት የሚለውን የሚቃወም ሲባል አንዳችም ድምጽ ጠፋ። ብርታት ጥንካሬም የሆነኝና የተነዛብኝን ተራ ፕሮፓጋንዳ ትኩረት አንዳልሰጠው ያደረገኝ ይፄው ነው ከሳሼ የሆኑት ወሮ አባይነሽ በየነና ስሙን የማላውቀው ወንድማቸው ይህን ፃሰት የተሞላበት ውንጀላ ለመፈጸም ለምን ቅጥረኝነትን አንደመረጡ ያልገባኝ ጉዳይ ነው ወሮ አባይነሽ እኔን በፃሰት ወንጅለው ቃላቸውን ሰጥተው ለጥቂት ቀናት ከሳሰሩ በኋላ በየደረሱበት አልከሰስኩም» የሚል የዳግም ክህደት ቃላቸውን ሲያስተጋቡ ነበር እውነት ያልክሰሱ ቢሆንማ ኖሮ ጋዜጠኞች ስለጉዳዩ ሊያነጋግሯቸው ሲፈልጉ ከቤቴም አልወጣ የሰውም አይን አላይ ብለው ባልተደበቁ ነበር ሴትዮዋ ፃሰት የማውራትና እየተቀጠሩ መወንጀልን እንደሙያ የያዙ ናቸው ሌላው ቀርቶ ከፈልኩ ከሚሉት ገንዘብ ለድርጅቱ ደረቅ ቼክ ሰጥተው በዚሁ ተወንጅለው አሁንም ጉዳዩ በፍርድ ቤት ያለ ጉዳይ ነው ለፃሰት ውንጀላቸው ማካካሻ እንዲሆን ያ ወንጀል እንኳን አልተነሳላቸውም ከተያዝኩበት ቀን ጀምሮ ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው እውነቱን በፍርድ ቤትም በመገኘት የዘገቡትን ነጻ ፕሬሶች ውለታና ፃቀኛነት ምን ጊዜም የማልረሳው ነው የአዲስ ዜና አዘጋጅ ላደረገው ክትትልና ላቀረበው ዘገባ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባለውለታ መሆኑን ሳልጠቁም ማለፉ ውለታ ቢስ ያደርገኛልና ምስጋናዬ ይድረሰው ዳኛው ጉዳዩን ከተመለከቱና ግራ ቀኙን ካገናዘቡ በኋላ «ጉዳዩ ምንም የወንጀል ጠባይ የሌለው በመሆኑና ፍትሐ ብሔር ስለሆነ በሌላ በኩልም ተከሳሹን የማያስጠይቅ በመሆኑ ተከሳሹ ተጨማሪ ማስረጃ በፖሊስ በኩል የሚቀርብ ከሆነ ሲፈለጉ እንዲቀርቡ የፀ ብር ዋስ ጠርተው በውጪ ሆነው ጉዳያቸውን ይክታተሉ ግን ተከሳሹ ዛሬውኑ ይፈቱ» የሚል ትዕዛዝ ነበር የሰጡት ግን አልተፈጸመም የሚቀጥለው ቀጠሮ ለጥቅምት ሆነና እኔም ሁለት ተጨማሪ ቀን ከፍርድ ውጪ የሆነ እስራቴን ጨርሼ ሰኞ ወጣሁያስያዝኩትን የዋስትና ብር እስካሁን አላገኘሁትም ለማግኘት ግን እየሞከርኩ ነው የውሕደት ክደቱ በእነ አቶ ልደቱ ጥቅምት ወደ ቢሮ ስገባ ቀደም ብሎ ተጀምሮ የነበረው የቅንጅትን አንድነት ለማረጋገጥና በአንድ ረድፍ ተሰልፎ በተቀናጀ ውህደት ትግሉን ለመቀጠል የቀረበው የውህደት ሰነድና ማመልክቻ ላይ የአራቱ ፓርቲዎች ማህተም አርፎ አራቱም ድርጅቶች ቀድሞ የወሰዱትን የምስክር ወረቀት መመለስ አለባቸው የተባለው ጉዳይ በኢዴፓመድህን በኩል ማህተሙን ለማድረግ ችግር ተፈጠረ ተባለ ውህደቱን በመቀበልና ጥቅሙን ከጉዳቱ በማገናዘብ ለውህደቱ ተግባራዊነት ፊርማቸውን በኢዴፓመድህን በኩል ያሰፈሩት የድርጅቱ ሊቀመንበር ዶር አድማሱ ገበየሁ ሲሆኑ በዚያን ሰአት አንድም ተቃውሞ ወይም የተለየ አስተሳሰብ ያለው አልነበረምአሁን ከየት መጣ። » የሚል አመለካከትም ነበር የዚህ የማሕተም ጉዳይ ሂደትና ያጋጠመው ችግር በዝርዝር ለአባላቱ ከቀረበ በኋላ ውይይት ሲጀመር የቀድሞው ኢዴፓመድህን አሁን የቅንጅት የላእላይ ምክር ቤቱ አባላት የሆኑት ይህን ጉዳይ ምክር ቤቱ ከመወያየቱና ውሳፄ ከማሳለፉ በፊት እኛ ከኢዴፓመድሕን የመጣን የምክር ቤት አባላት በጉዳዩ ላይ መክረንበት ውሳኔ አንድናመጣ ምክር ቤቱ ይፍቀድልን ይህ ጉዳይ የአንድ ሁለት ሰው ጉዳይ ሳይሆን የቀድሞው የኢዴፓመድህን አባላት ሁሉ ጉዳይ ስለሆነ እድሉ ይሰጠን» በማለታቸውና ይህ ደግሞ ሰላሚዊውን ግንኙነት የሚያጠናክርና ምናልባትም ልዩነትን የሚያጠብ ሊሆን ስለሚችል በዚህ በቀረበው ሀሳብ ላይ ውይይት ተካሂዶ ካለው የጊዜ ጥበት አኪያ በአጭር ጊዜ ውስጥ መልስ አንዲያመጡ ሆኖ ተፈቀደ በስብሰባው ላይ ከቀረበው የነአቶ ልደቱ ቅሬታ በተቀዳሚነት የተነሳው የሥልጣን ክፍፍል ላይ ተጎድተናል የሚል ነበር የምክር ቤቱ አባላት ይህን ሲያዳምጡ በምርጫው ሂደት ወቅት የነበረውን ሂደት የግድ ማንሳት በማስፈለጉ ተነሳ ከቀረቡት የሥራ አስፈጻሚ ቦታዎች መፃል አቶ ልደቱ በእጩነት በድርጅቱ የቀረቡበት ለሊቀመንበርነትለዋና ጸሐፊነትለተምሊቀመንበ ርነት ለምክትል ሊቀ መንበርነት ሆኖ ሳለ ክ እስከ ላሉት ቦታዎች በድምጽ ብልጫ ተሸንፈዋል ድምጽ የሰጡት ደሞ በአጠቃላይ የላእላይ ምቤቱ አባላት ናቸው በኛው ቦታ ላይ ድምጽ በማግኘ ታቸው በዚያ ተመድበዋል ይህ ደሞ ከምንከተለው ዴሞክራሲያዊ ሂደት አኪያ ትክክል ነው ታዲያ በድምጽ ያጡትን ቦታ እንዴት ሊያገኙ ይችላሉ። » የሚል ሌላ ፃሳብ ተሰነበረ በሁለቱም ፃሳብ ላይ ጥቅምና ጉዳቱን በማመዛዘን የተለያየ ፃዛሳብ ከተደመጠ በኋላ አንድ አድል» የሚለው ፃሳብ በአብላጫው ድምጽ ስለተደገፈ ይሄው ጸድቆ የሚያናግሩ አራት አባላት ከምክር ቤቱ ተመረጡ ፃሳቡን በቅድሚያ ያቀረቡት ዶር ዓለማየሁ ለሥራ ጉዳይ አስፈቅደው ወጥተው ቢሄዱም ያቀረቡት ፃሳብ ተቀባይነትም ስላገኘ ከሚሄዱት አንዱ አንዲሆኑ ሲጠቆሙ ወሮ ለኔሲል ከቀድሞው ኢዴሊን ዶር ዓለማየሁ አይሆንም የሚል ተቃውሞ አቀረቡ ዶር ዓለማየሁም አይቀበልም» በማለታቸው አራሳቸው ዶር ዓለማየሁ በስልክ ይጠየቁ ተብሎ ሲደወልላቸው በደስታ ተቀበሉ አሳቸው ያሉበት አራት አባላት ያሉት ቡድን እንዲያነጋገርና መልስ አንዲያመጣ ከዚያ በኋላ ምክር ቤቱ ወደ ውሳኔ አንዲሄድ ሁኖ ስብሰባው በዚሁ አበቃ የመልሱ ቀነ ቀጠሮ ደርሶ መልሱ መጣአቶ ልደቱ አራሳቸው ተገኝተው ፃሳባቸውን እንዲያቀርቡ በመስማማታቸው ስብሰባው ተጀመረ አቶ ልደቱም ተገኙ ዛሳባቸውንና ስጋታቸውን አቀረቡ ችግር ተብሎ የቀረበው የስልጣን ጥያቄ ቢሆንም ለቅንጅት ደህንነት ሲባል ሊስተካከል የሚችል ነው ሲባልና የምክር ቤት አባላት ይህንኑ በማስረገጥ ፃሳብ ሲሰጡበት አቶ ልደቱ ግን ከዚህ በፊት ይሆናል ተብሎ አቶ ሞሼ የድርጅት ጉዳይ ዛላፊነት ሳይሰጣቸው ቀርቷልና ያሁኑም እንደዚያው ሊሆን ስለሚችል የሚለውን ማመን ያስቸግረኛል በማለት አሻፈረኝ አሉ የምክር ቤት አባላትም አሁን በስልጣን ጥያቄ የተነሳ ቅንጅትን ችግር ውስጥ ማስገባት የኢትዮጵያ ሕዝብ በእርግጠኝነት ተስፋ አድርጎ የሚጠብቀውን ሁሉ ማበላሸት ስለሚሆን ችግሩን እንፍታና ለተነሱት ችግሮች አብረን አንቆማለን ቢባልም አቶ ልደቱ ለመቀበል ሳይፈቅዱ ስብሰባውን ጥለው ወጠ ቀደም ሲል ከሳቸው ጋር ወግነው ከነበሩትም መፃሃል የቅንጅትን መጠናከር እንደግፋለን ያሉ ከሳቸው ተለዩ። ከጥቂት ቀናት በኋላ አንድ ለሳቸው በጣም ቅርብና እንዲያውም እስከመጨረሻው ድረስ ከጎናቸው የቆመና በመጨረሻው ሰአት ላይ ነገሩ አላምርህ ሲለው የሕዝብ ጠላት ሆኖ ከሕዝብ ጋር መኖር አስቸጋሪ መሆኑን ተረድቶ ያፈገፈገ ወዳጃቸው በዚሁ ጉዳይ ላይ ስንነጋገር አልገባኝም ሁኔታው ስለበዛበት ይመስለኛ ል «አሁን አይደለም የተጀመረው ቡግና ነጻ ወረዳ በነበረበት ጊዜ የተወጠነ ነው የሱ የቅርብ ተጠሪና አስተማሪ ሪፖርት ተቀባይ እኮ አሁን የገዢው ፓርቲ ዋና ሰው ነው አሁንም ሆነ ቀደም ብሎ ለሚፈጠሩ ችግሮች ሁሉ መመሪያውን ከዚያ ነው የሚቀበለው አኔ ይህን ካወቅሁ ጀምሮ በጥንቃቄ አበሬው ብቆይም አሁን ግን በተለይ የዛሬው ስብሰባ ነው ለውሳኔ ያበቃኝ» አለኝ ጉዳዩን በዝርዝር ሊነግረኝ ባይደፍርም ዙሪያውን ሲጠቃቅስልኝ በመጠኑም ቢሆን የሰዎች እጅ እንዳለበት ገባኝበዚህ ላይ ደሞ በሼራተን የሚሰሩ የቅንጅት ደጋፊዎችና አባላት አቶ ልደቱ ከዲታዎች ጋር እንደሚውሉና ለረጂም ሰአታት ውይይት እንደሚያደርጉ ደጋግመው ይደውሉልኝ ስለነበር አሁን የነገሮችን ጫፍ ማገጣጠም ቻልኩ ምንም ይሁን ምንም አቶ ልደቱ ትልቅ የፖለቲካ ስሕተት ፈጽመዋል ሌላው ቢቀር የግልም ይሁን የቡድን ጥቅምን ለሕዝብ ነጻነት ዴሞክራሲ ሰብአዊ መብት ሲሉ ሊተዉና ቆይተው ያንን ለሕዝቡ ይፋ ማድረግ ይችሉ ነበር በኔ ግምት አቶ ልደቱ «ቅንጅትን ትቼ አወጣለሀ ሲሉ የምክር ቤት አባላት በሙሉ «አንተ ከምትወጣ የምትፈልገውን አሁን እናደርጋለን ደንቡንም መመሪያውንም እናፈርሳለን ስለእግዚአብሔር ብለህ»ብለው ጫማዬ ላይ ወድቀው ይለምኑኛል እኔም ማንነቴን አሳያቸዋለሁበዴሞክራሲያዊ ምርጫ ያጣሁትን ቦታ በአምባገነናዊ እምቢታ አገኘዋለሁ የሚል የሞኝ አሳቤ አድሮባቸው ከሆነ ተሳስተው ከሕዝብና ከፃገር ጋር ተጣልተዋል አሁን አኮ ከማንም በላይ መወደድና ታማኝነት ያለው «ቅንጅት» ነው «ቅንጅት»ን መንክት ደሞ በእሳት መጫወት ሆኗላ። ተብዬ ስለምጠየቅ የኔ የሆነውንፃዛሳቤን ያለተቃውሞ የሚቀበለኝን እንደኔ የማምነውን የጥቅም ጓደኛዬን «ሞሼን አስመድባለሁ የሚለው እምነቱ ስላልተሳካለት ችግር መፍጠርና አሉባልታ በአጨብጫቢዎቹ በኩል እንዲናፈስ በግል ጋዜጦች ኡኡታውን ቀጠለ ለዚያም ከቅንጅት ሁኔታው አንዴት እንደተወሰነ ጥያቄው ከየት እንደመጣ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ ለሕዝብ አሳወቀ ሕዝብ ደሞ ይህን ከተረዳ በኋላ «ይሄ ሰው» የሚል የጥርጣሪ ሁኔታ ፈጠረ ቅንጅት እየተጠናከረ ወደ ውህደቱ በሚዓዝበት ወቅት ለልደቱ ክፉ ፈተና ገጠመው የመጀመሪያው ፈተና አራቱም ድርጅቶች ሃብት ንብረታቸውን አሰባስበው በአንድ በቅንጅት ሥር እንዲያውሉ ያስገድዳል በሌላ በኩል ሒሳብን በተመለክተ በውጪ ኦዲተር ሂሳብ ተመርምሮ መጣራት ይጠይቃል በተለይ ይህ የሂሳብ ጉዳይ በጣም ያስፈራል ቼክ ያውም ባዶ ቼክ እንዲፈረም የሚያስገድድ ግለሰብ ያንን ገንዘብ ለምን አንዳዋለው በይፋ ያስጠይቀዋልና ይህ ደሞ ለአቶ ልደቱና ለአጫፋሪዎቹ በጣም የሚያሳፍር ስም የሚያሰጥ አውነታ አለበት ይህ አሁንም ቢሆን የማይቀር ነው ሂሳቡ ሲጣራና አውነቱ ፈጦ ሲወጣ ለድርጅቱና ለግል የወጣውን ለይቶ ስለሚያሳይ ያ ተለይቶ መልስ አምጡ ይላል መልሱ ደሞ ችግር የሚፈጥር ነው በተለይ ለግል ተግባር የዋለው ሂሳብ መመለስ ስላለበት አሁን ደሞ ውህደቱ ተግባራዊ ሲሆን አቶ ልደቱ ከ በላይ ተሳታፊ አባላት በተገኙበት በተካፄደው ቅድመ የላእላይ ምክር ቤት የቅንጅቱ አዲስ ሥራ አስፈጻሚ አባላት ስብሰባ ላይ እያንዳንዱ ፓርቲ ላሉት ሃላፊነቶች ተመራጮቻቸውን አቅርበው በሳአላይ ምክር ቤቱ አባላት ድምጽ ተሰጥቶባቸው የሚያልፉበት ነበር በዚህ ሂደት ላይ ሶስቱ ፓርቲዎች ለያንዳንዱ ፃላፊነት የተለያዩ አባሎቻቸውን ሲያቀርቡ የነአቶ ልደቱ ቡድን ግን ያቀረበው ለሁሉም ቦታዎች አቶ ልደቱን በብቸኛነት ነበር ለአንዱ ማሸነፍ ሲያቅት ደሞ ሌላውን በዚያም ሳይሳካ ቀጥሎ ያለውን አሁን ድምጽ ሲጠፋ ደሞ ሌላውን ሲወዳደሩ ቆይተው በምሊቀ መንበሩ ቦታ ላይ ድምጽ አግኝተው ተመረጡ ፍላጎታቸው የሊቀመንበሩን ወይም የጸፃፊውን ቦታ መያዝ ስለነበርና ያ ደግሞ ስላልተሳካ ደስተኛ አልነበሩም ይህን ሳይ እፒህ ሰው ሰዉ ሁሉ እንዳይወዳደር በማድረግ በሁሉም ቦታ እሳቸው ብቻ የቀረቡበት ምክንያት ምንድን ነው። አቶ ልደቱም ያደረገው እንደዚሁ ነውና ለዚህ ምላሽ መስጠት ያለበት እራሱ አቶ ልደቱ ነው በማለት መልስ ተሰጥቶት ተሰብሳቢው በሙሉ ጉዳዩ አንዲህ ከሆነ ይህ አጀንዳ ይብቃና ወደ ተሰበሰብንበት ዋና ጉዳይ እንግባ በሚል ተዘጋ ይህ መልስ ያልጣማቸው ሌላዋ የአቶ ልደቱ ደጋፊና የፃሳቡ ተጋሪ ነኝ ባይ ዶር ሙሉ ዓለም ጉዳዩ መዘጋት የለበትም በሚል ሃሳብ ቢያቀርቡም ተሳታፊው በተቃውሞ አጣጣለው ከቀረቡች ተቃውሞችም በመቶው ከቀድሞው የኢዴፓ መድህን አባላት ነበር ይህ በዚህ ተዘጋና ስብሰባው ቀጠለ ውህደትም ተፈጸመ ሰነዱ ተፈረመ ለኢትዮጵያ ሞቷ ልደቱ እየሆነ ጥያቄው ቅጥ አጣ ስሙ እንዳልገነነ ምነው ቅጥ አሳጣህ ለምን ተቅበጠበጥክ ገና ከጅምሩ የሕዝብ እንዳልተባልክ በማለት ነበር ተሰብሳቢው ወዲያው መግጠም የጀደመረው ይህ በእንዲህ አለፈና ቀጣዩ ስብሰባ ፓርላማ እንግባ ወይስ አንግባ የሚለውን ለመወሰን የተጠራው ስብሰባ ነበር ተሰብሳቢዎቹ የላእላይ ምክር ቤት አባላት ናቸው ስብሰባው የሚካሄደው በቅሎ ቤት በሚገኘው የኢዴፓመድሕን ጸቤት ነበር ሂደቱን በተመለከተ ዝርዝር ሁኔታውን ማቅረብ ጊዜ ማጥፋት ስለሚሆንና ቀደም ተብሉም የቀረበ ስለሆነ ወደ ድምጽ አሰጣጡና ወደ ነበረው ሁኔታ ማለፉ ይሻላል በተደጋጋሚ ለሚተላለፉች ውሳኔዎች ሁሉ ድምጽ እየተቆጠረ ነበር ውሳኔው የሚጸድቀው አቶ ልደቱ ጥያቄም ሲጠይቁ በቀጥታ በሳቸው አንደበት ሳይሆን በወኪል ጥያቄ ያስጠይቁና እሳቸው ግን ተጨማሪ ተቃውሞ ማሳሰቢያ በሚል ፃሳብ ያቀርባሉ እንጂ በድምጽ ቆጠራ ወቅት አቶ ልደቱ አቶ ሞሼ አቶ አብዱራህማን ዶር ሙለዓለም ሁሉንም ውሳኔ ያለፉት በድምጸ ተአቅቦ ነበር አራቱ ብቻ ፓርላማ እንግባ ወይስ አንግባ የሚለውን ደሞ ተቃዋሚ ሲጠየቅ አልተገኘምና ድምጸ ተአቅቦ የሚል ጥያቄ ሲቀርብ አቶ ልደቱ በጭራሽ መጠየቅ የለበትም ተቃውሞ ስለሌለ በዚሁ ማለፍ አለበት ብለው ሲሞግቱ ለምን ብዬ ስመራመር ተአቅቦ ከተጠቀሰ አሳቸው ብቻ ስለሚሆኑ ያንን ለመሸፈን ነበር የተቃወሙትና በሙሉ ድምጽ ተብሎ» አለፈ እነዚህ በተለያየ ጊዜ የተጠራቀሙ ሁኔታዎች አሁን ድርጅቶቹ ከስመው በቅንጅት ይጠቃለሉ ሲባል ተቃውሟቸው የመጣውም የቀድሞ ተልእኳቸውን ለመወጣት አመቺ ጊዜ ያገኙና የቅንጅትን ውህደት ለማራዘምና ወደ አለመግባባት መበታተን ለመውሰድ ቢሆንም ያም በሕዝብ ጥረት ቁጭትና ምሬት ሳይሳካ ቀረ ወደ መሰረቱ እንሂድ ኢህአዴግ ወደግዛት ሳይመጣ በፊት ቡግና ነጻ» ወረዳ በሚባልበት ጊዜ የአቶ ልደቱ የቅርብ አስተማሪና ተጠሪ አቶ በረክት ስምኦን ነበሩ መመሪያ የሚሰጡት ለአቶ በረከት አስፈላጊውን የስለላ ውጤት የሚያስታውቁ ደሞ አቶ ልደቱ ነበሩ አሁን የታቀደው ግብ አልመታም ሊቀጥል የሚችለው ሂደት አቶ ልደቱን አቅፎ ደግፎ ለሥልጣን ማብቃት» ሳይሆን በመቅረቱ ገዢው ፓርቲ በሳቸው ላይ የንግድ ሥራውን በመቀጠል በእሳቸው ላይ አደጋ አድርሶ ቅንጅት እንዲህ አደረገ ማለት ሊሆን ይችላል ቅንጅት አሁንም ቢሆን አኔ አስከማውቀው ድረስ አቶ ልደቱን «ለሕዝብ ይቁሙ እንጂ እንዲህ ያርግዎት» ስለማይል አቶ ልደቱ ንስሃ ገብተው እውነቱን ለሕዝብ አሳውቀው ከፃዛገርና ከሕዝብ ጋር ቢታረቁ ይበጃቸዋል አርቀ ሰላም ብቻ ነው የሚያዋጣቸው አንጂ የሕዝብን ጥቅምና ነጻነት ለራሳቸው ስልጣን ፍለጋ በመለወጥ የሚገኝ አንዳችም ትርፍ እንደሌለ ሊያውቁት የሚገባ ጉዳይ ነው። መስተዳድሩ የፈራው በፃዛላፊነት ተጠያቂ ሆኖ ሳይሆን ያን የሚጠላውን የጣት ምልክት እንደችቦ ሲዘረጋና ለቅንጅት አመራር አባላት ፍቅርና ክብር የሚሰጥ ህብረተሰብ ማየትን ነበር የፈራው ስለዚህም አዳራሹን የማግኘት ጉዳይ ያለቀለት ሆነ ይህም ማለት ከሕብረተሰቡ ጋር መገናኘት አከተመ ማለት ነውኢህአዴግ ግን አዳራሹ በጁ መስተዳድሩ በጁ ሁሉ ነገር በደጁ ስለሆነ እንዳሻው ሕዝብን እየሰበሰበ ያሻውን ፕሮፓጋንዳ ያካሂድብናል ይሁንና የራሱ ደጋፊ ከሚባሉት የቀበሌ መስተዳድርና አባላት ከሚላቸው በስተቀር የሚሰበሰብ አልነበረም እኛም ይህ አግባብ አለመሆኑንና ሕገመንግሥቱ የሚፈቅደውን መብታችንን እየተነፈግን መሆኑን ለሚመለከታቸው ሁሉ አቤት ብንልም መልሰው ወደ አዲስ አበባ መስተዳደር ሂዱ ነበር መልሳቸው እንዲህ እንዲህ እያልን ቆየንና የገዢው ፓርቲ አንዳችም ፍትፃዊ የሆነ ተግባር አልከውንም በማለቱና ስለተቀማነውም ድምጽ ፍትፃሃዊ መልስ አልሰጥም ያለውን ምርጫ ቦርድን ከማስተካከል ይልቅ አበጀህ የኛ ልጅ» እያለ ስለሚያሞካሸው ኅብረተሰቡ ደግሞ ድምጻችንን አስከብሩልን የሚለው ጥያቄው ቢሮ በመምጣትም በጋዜጦችም በተለያየ መንገድ በመጠየቁ አኛም ሰላማዊ ትግል ያልነውን መሰረት በማድረግ አሁንም ሕዝቡን ለሰላማዊ ትግል ጥሪ አደረግንለት ጥሪው ሁሉም ለሶስት ቀናት በየቤቱ እንዲቀመጥ የሚል ነበርና «መንግሥት» ገዢው ፓርቲ የሕዝቡ ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚችልና በሚያስከትለው የኤኮኖሚ ውድቀት ሊያነበረክከው እንደሚችል በመረዳት ከፍተኛው የገዢው ፓርቲ ቁንጮ ባለስልጣን « ይህን ጥሪያችሁን አንሱና ከሰማይ በታች ባለ በማንኛውም ጉዳይ ላይ መወያየት እንችላለን » በማለታቸው በሚከተለው የኤኮኖሚ ድቀት ተጎጂው የኛ የሆነው የቆምንለት ሕዝብና ፃገራችን በመሆኗ አንድ ፃገርን የሚያስተዳድር መንግሥት ቃሉን አያጥፍም በሚል እንዲሁም ትግላችን ሰላማዊ በመሆኑ ገዢው ፓርቲም ወደ ሰላም መመለስ ከፈቀደ አንድ ጊዜ አንየው ማታለልም ከሆነ በዚሁ እንተዛዘባለን በሚል ጥሪው ተነሳ ሕዝቡም ወደ ሥራው ተሰማራ ገዢው ፓርቲ ወዲያው ቃሉን አጠፈ ሁኔታው በጣም የሚያሳዝን ከአንድ ዛገርን ከሚመራ አካል የማይጠበቅ ቢሆንም አንድ ጊዜ ሆኗል ብለን ሌላ መንገድ መከተል መረጥን አሁንም ሰላማዊውን መንገድ ተከትለን በሄፄድን ቁጥር አካሄዳችን ወደ ድል አድራጊነት ሲያመራ በገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ስር ያሉት የመገናኛ ብዙፃዛን ከዳር አስከዳር ዋልታ ኢንፎርሜሽን አይጋ ዌብ ሳይት ሁሉም ቅንጅት ሕገመንግሥቱን ሊንድ ነው» የሚል ፕሮፓጋንዳ አወረዱብን ተከታትሎ በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰአቱ እየተጠቀሰ የካርዱ ቀለም አየተለየ ማስጠንቀቂያ ይሰጠናል በሕገ መንግሥቱ ላይ ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ የመቃወም መብት ተሰጥቶታል ሕዝቡ ደሞ በሕገ መንግሥቱ ላይ የሰፈረውን የዜግነት መብታችችንን ተጠቅመን እናስከብራሰን አለ ቅንጅት አዲስ አበባን ሙሉ በሙሉ በማሸነፉ አዳዲስ አዋጆች እየወጡ የመስተዳድሩ መብቶች በሙሉ ወደ ፌዴራል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ተዛወሩ መስተዳድሩ ገቢን በተመለከተ ባዶውን ቀረ በዚያ ሁኔታ እያለ አዲስ አበባን ለመረከብና የተወሰደ መብቱን ለማስመለስ ተወሰነ ወደ ምክር ቤት ላላመግባት ከወሰንን አዲስ አበባንም መረከብ የለብንም የሚል ክርክር አንደቅድመ ሁኒታ ልደቱና ሞሼ አመጡ ይህን የሚያሳየው ቪድዮ አለ በዚህ ላይ የጠነከረ ክርክር ነበር ያቀረቡትየሕዝብን ድምጽ እናክብር ነው ውሳኔያችንና አዲስ አበባን መረከብም የሕዝብን ድምጽ አለማክበር ነው ስለዚህ አዲስ አበባንም መረከብ የለብንም የሚል አቋም ያኩዙ በአንግባ አንግባ ውይይት ላይ ልደቱና ሞሼ ከኔ ኋላ ነበር የተቀመጡትና የሚያወሩት ሁሉ ይሰማኝ ነበር። » ቢልም እነሱ በተለያየ መልክ አዛው ናቸውበኔ ግምት ምንም ሳይወሰን እንድንለያይ ያሰቡ ሆነው ነበር የታዩኝና የበኩሌን ተናገርኩፁ «እባካችሁ በመግባባት ያለቀውን ጉዳይ መልሰን ወደ ነበረበት ማድረጉ ሌላ ሚስጥር ከሌለው በስተቀር ጥቅሙ አይታየኝም ምናልባት ውሳኒ ላይ እንዳንደርስ የሚፈልግ ሰው ካለ በግልጽ ይናገር በተረፈ ለኔ እንደገባኝ ሳንወስን ብናድር ነገ ተሾልኮ ወደ ፓርላማ ለመግባት የሚያመች ሰበብ ለማግኘት ነውና ወደ ውሳኔ ለመግባት እንድንችል የተወሰነ የጊዜ ገደብ ይሰጥና ወደ ድምጽ እንሂድ በኔ በኩል ደቂቃ የሚበቃን ይመስለኛል» አልኩ ሌሉችም ተመሳሳይ ዛሳብ ሰጡና ለ ደቂቃ ተወያይተን ወደ ድምጽ ገባንበመጨረሻም ውሳኔው በሙሱ ድምጽ ሆነና ተደመደመ አዲስ አበባም አለመግባት ተወሰነ ዶር ብርፃኑ ዶር ሽመልስ ዶር በፈቃዱና አኔ ተያይዘን ወደግሎባል ሆቴል ቡና ለመጠጣትም መኪናዎች አሰኪነሱ ለመጠበቅም ስናመራ ደህንነቶች ተከተሉን ይፎክራሉ ለማስፈራራት መሆኑ ነው ማንም ከቁጥር ያገባቸው የለም ግሎባል ገባን ወንበር ይዘን የሚጠጣ ስናዝ ደህንነቶችም ገብተው እንደኛው አዘው ቁጭ አሉ ምን እንደሚፈልጉ ማወቅ አልቻልንም ለደህንነታችን ይሆን እየተባባልን አንስቃለን በመጨረሻ መግለጫ መሰጠቱን ስንሰማ ወደ መኪናዎቻችን ስንፄድም አሁንም አጃቢዎች ነበሩን መኪናዎቻችንን አሰነስተን ወደየቤታችንም ስንፄድ አጃቢዎች ነበሩን አኔን እስከ ቤቴ መግቢያ ድረስ አጅበውኝ ወደ ቤቴ ሰገባ ተመለሱ ምን ማለት እንደሆነ አልተረዳሁትም ለነበፈቃዱም ስደውል እንደኔው ታጅበው መግባታቸውን ነገሩኝ ክንቱ ልፋት ከንቱ የነዳጅና የመኪና ብክነት የፀን ምርጫና ያሰከተለውን ውዝግብ የካርድ ንጥቂያና የአቤቱታ ሰሚ ማጣትን በተመለከተ አንዳርጋቸው ጽጌ ፓርላማ አለመግበት ጋር የተወሰደውን አርምጃ በተመለከተ የሚከተለውን እውነታ ፎ ነበርና እሱን እዚህ ውስጥ ማካተቱ ጥሩ ግንዛቤ ይሰጣል አንዳርጋቸው ኢህአዴግንም ቅንጅትንም በሚገባ ስለሚያውቅ ለፍረድ አሰጣጥ ስለሚያመች አቅርቤዋለሁ መስከረም ቅንጅትና የግንቦት ቱ ምርጫ መጭበርበር ከአንዳርጋቸው ጽጌ መንደርደሪያ የግንቦት ቱ ምርጫ መጭበርበሩ ከታወቀ በኋላ ወያኔ ከህዝብ የዘረፈውን ድምጽ ለማስመለስ ቅንጅት ቃል ገብቶ የተለያዩ እንቅስቃሴችዎን አድርጓል ቅንጅት ሰላማዊና ህጋዊ የትግል አቅጣጫ በመከተል ወደ ፍርድ ቤት በመፄድ በራሱ በምርጫ ቦርድ መድረክ ላይና በዲፕሎማሲያዊው ዘርፍ ትግል በማድረግ በወያኔ የተዘረፈውን የህዝብ ድምጽ ለማስከበር ብዙ ጥሯል የተሰረቀውን የህዝብ ድምጽ ለማስመለስ መደረግ የነበረበትን ጥረት ሁሉም የምደግፈው ቢሆንም ወደ ፍርድ ቤትና ወደ ምርጫ ቦርዱ እየተመላለሱ የመሄዱ የትግል አቅጣጫ የህዝብን ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ያገኘ ነበር ማለት ግን አይቻልም ይህ አመለካከት የፃገር ቤቱንም ሆነ በውጭ ዛገር ቅንጅትን የሚደግፈውን አብዛኛውን ህዝብ ያካተተ ነበር ወያኔ አምባገነን ስለሆነ ከዚህ የበለጠ ጠንካራ የሆነ የሰላማዊ ተቃውሞ እንጂራሱ በፈጠራቸው ፍርድ ቤት ዳኞችና የምርጫ አስፈጻሚ አካላትእንዲሁም የራሳቸውን ብሄራዊ ጥቅም አስቀድመው በሚያሰሉና በወያኔ ኪስ ውስጥ ቀድሞውኑ በተያዙ የውጭ መንግስታት አማካይነት የህዝብን ድምጽ ማስከበር እንደማይቻል የተሟገቱ በርካቶች ነበሩ ያም ሆነ ይህ ፍርድ ቤትን ምርጫ ቦርድንና አለምአቀፍ ህብረተሰቡን በመጠቀም የህዝብ መብት ማሰከበር ባይቻልም ጥረቶቹ ሁለት መሰረታዊ ቁምነገሮች ማስረገጥ ችለዋል የመጀመሪያው ሰላማዊና ህጋዊ ጎዳናዎች ከመርፌ ቀዳዳ ጠብበው በሚታዩበት ወቅትም እንኳን ችግሮችን ሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት ቅንጅት ያለውን የእምነት ጽናት ማረጋገጥ የተቻለበት ነውፁ በቪህም ወያኔ እራሱን ብቻ ለሰላም አሳቢና ተጨናቂ እያደረገ የሚያቀርበውን ጩኸት ባዶነት አረጋግጧል የወያኔን የግድያ የአፈናና የወከባ ትንኮሳዎች በትአግስት በማሳለፍ ለሰላምና መረጋጋት ከወያኔ በላይ ቅንጅት እንደሚጨነቅ አስመስክሯል ሁለተኛው በፃገሪቱ ውስጥ ከወያኔ በጎ ፈቃድ ውጭ የሚንቀሳቀሱ የፍትህም ሆነ የምርጫ አስፈጻሚ አካላት እንደሌሉ አረጋግጧል ወያኔም ከባዶ ጩኸት ያለፈ የዴሞክራሲ የፍትህና የሰላም አምነት ያልዘራበት እንደሆነ ለሁሉም ማሳየት ችሏል ይህ በተለይ ወያኔ ስለራሱ ዴሞክራሲያዊነትና ሰላማዊነት በሚያሰራጨው የፕሮፓጋንዳ አስማት ደንዝዘው የነበሩትን በርካታ የውጭ መንግስታት ዲፕሎማቶችን ነጻ ለማውጣት ችጳል ከዚህ በኋላ የውጭ መንግስታት ለወያኔ የሚሰጡት ድጋፍ ካለ ወያኔ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አዎንታዊ ሚና ስለሚጫወት አንዳልሆነ የፃገራችን ህዝብም እንዲረዳው ማድረግ ሏል በተለይ ከምርጫው በፊት የነበረው አንጻራዊ ዴሞክራሲያዊ አውነታ ተጋኖ መታየት አንደሌለበት ለውጭ መንግስታት ለማሳየት ማጭበርበር በተደረገባቸው ቦታዎች ላይ በተወሰደው የማጣራት ሂደት ውስጥ መሳተፉ ጠቀሜታ አስገኝቷል ይህም ለቅንጅትና ለህብረት ከፍተኛ ዴፕሎማሲያዊ ድል።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact