Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي
  • قائمة القراءة
  • مختصر
  • كتاب مسموع
  • بحث
  • تحميل
  • myzon
  • تسجيل الدخول
  • تسجيل
English  አማርኛ  Français  العربية
كتاب اليوم

የስርቻው መጣጥፍ @OLDBOOKSPDF.pdf


  • word cloud

የስርቻው መጣጥፍ @OLDBOOKSPDF.pdf
  • Extraction Summary

እስከ ሰማኒያ አንዳፍታ ትንፋሼን ልሰብስብ ይህን የማጫውትዎ ቢስቁልኝ ብዬ ይመስልዎት ይሆናል እንደገና ተሳስተዋል እንደሚያስቡት ቀልደኛ ሰው አይደለሁም መነባንቤ ሰላም ከነሳዎ እንደረበሸዎት አውቃለሁ ለመሆኑ አንተ ቲጠፎዐዚዐሂዞዐዮኮ ማነህ ብለው ሊጠይቁኝ ይከጅላሉ እመልስልዎታለሁ የመዝገብ ቤት ሠራተኛ ነኝ ስራ ለመያዝ ዋነኛ ምክንያቴ ሆዴን እሞላ ዘንድ ነበር ኋላ ግን ነገሮችን አገናዝቤ ስሙን ለወጥኩና ለኀትመት ይበቃ ዘንድ ፅሁፉን ለዝነኛ ጋዜጣ ላኩት ያኔ ታዲያ ከአሥራአምስት ዓመታት በኋላ እንኳን ሊዛን የማስታውሳት በነዚያ ጥቂት ሰኮንዶች እንዳየኋት ብቻ አልመሠለኝም ነበር ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ከቤቴ ያየችው ሁሉ መሆን እንደሚገባው ስለነበር ባይገርማት ይሻል ነበር ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ዋጋዋን ጥሩ አድርጌ ሳልከፍላት እንደማልቀር ዛትኩ « አጉል ሁኔታ ላይ አገኘሽኝ ሊዛ » አልኳት አፌ እየተሳሰረብኝ የዚህን አላግባብነት ወዲያው ተረዳሁት « እንደምታስቢው አይደለም ሌላ ነገር አታሰብ » አፖሎን እንደተመለሠ መነዕሩን አድርጎ እንደገና ሥራውን ቀጥሎ ነበር። » እንደገና አጓራሁባት ጠረጴዛውን እየነረትኩ አእምሮዬን መሣት ቢቃጣኝም የእብደት መሣይ ብስጭቴ አጉልነት ይታወቀኝ ነበር « ይህ ርኩስ እንዴት እንደሚያሰቃየኝ አታውቂም ሊዛ በኔ ለመጫወት ነው የሚኖረው አሁን ብስኩት ሊገዛ ሄጻዲል እሱ » ሳልጨርሰው እንባ አነቀኝና በድንገት ማልቀስ ጀመርኩ ሁኔታዬ ቢያሳፍረኝም እንባዬን መግታት አልቻልኩም « ምነው። » አለችና ፈራ ተባ እያለች ልትነሳ ስትል የረገጥኩባት የራስ ክብሯን ለመሠብሰብ መሞከሯ መሆኑ ገባኝና በቁጣ ሞገድ እንቀጠቀጥ ጀመር « እስቲ ንገሪኝ ምን ፈልገሽ ነው የመጣሽው። ያኔ በሆዴ ስስቅብሽ ነበር አሁንም እየሳቅኩብሽ እንደሆነ እወቂ ምን ያሳቅቅሻል። » ይህ ንግግሬ ግራ እንደሚያጋባትና አጥርታ ምንነቱን ለማየት እንደሚያቅታት ባስብም የሁኔታዬን አቅጣጫ በደፈናው እንደተረዳችው አውቄያለሁ በድንጋጤ ፊቷ አመድ ለበሰ ለመናገር ፈልጋ ከንፈሮቿ ቢላወሱም ካፏ ድምፅ አልወጣም ከሥሯ በመጥረቢያ የቆረጧት ይመስል ከወንበሩ ሳይ ተመልሳ ዘፍ አለች ተቀምጣ ሰውነቷ እየተብረከረከ አፏን ከፍታ ታዳምጠኝ ጀመር « ሳድንሽ። ያኔ ልምከርሽ ብዬ ስመፃደቅ ለምን ልኬን አትነግሪኝም ነበር። በፎዐበወዐዐዐሂፍዞዐዮኮ አትይኝም ነበር።ጠብፍ ዐዕዚዐይዩዕዐዕዚሂዞኮሀሾ ያቂዋ አንቺው ነሽ በመምጣትሽ እኔ ራሴ የርጉማን ርጉም መሣለቂያ ርካሽ ምድርን ከወረሯት ትላትሎች ሁሉ የከፋሁ ምቀኛ ነኝ ሌሎቹ ትሎች ከኔ እምብዛም ባይሻሉም አያፍሩበትም ታዲያ ሁልጊዜ ማንም ተባይ እየተነሳ በጥፊ ይለኛል እንዲህ ያለሁ ሰው ነኝን። አሰቃይቼ ልገድላት ካልሆነ በቀር ሌሳ ምን ልፈይድላት። ባልጀምረው ሳይሻለኝ አይቀርም ነበር ሆኖም ግን ይህን ሁሉ ስፅፍ እፍረት ተጠናውቶኝ ነበር ስለዚህም ይህ የመታረሚያ ቅጣት እንጂ ስነፅሁፍ አይደለም እንዴት ቢሌሉኝ በጠማማ ተፈጥሮዬ ከሰው ተለይቼና ሕይወትን በውል ከሚኖሯት ጋር ሳልቀላቀል በግብዝነት በክፋት ከዋሻዬ ተወትፌ እንዴት ሕይወቴን እንዳባከንኩ መመዝገብ ደስ የሚያሰኝ ነገር አይደለም ታሪክ ያለተዋናይ አኣይፃፍም ይህ ትረካ የታነፀው ግን በይሁንታ በተለቀሙ የኢተዋናይ ድርጊቶች ጥርቅም ነው ከዚያም በላይ ሁላችንም ከህይወት የተፋታን አነሰም በዛም ስንኩሎች በመሆናችን ምክንያት ከዚህ መፅሐፍ ውስጥ ያሉት ነገሮች ያስቀይሙናል በእውነቱ ለነገሮች ባይተዋር ከመሆናችን የተነሳ በእርግጥ የሚኖር ሕያው ሕይወትን እየተጠየፍን ስለሱ ባያነሱልን እንመርጣለን የእውን ሕይወትን ከባርነት ስለምንቆጥረው ነገሩ ሁሉ እንደልቦለድ መፅሐፍ ትረካ ቢሆን በልባችን እንፈቅዳለን ታዲያ ምን ያቁነጠንጠናል።

  • Cosine Similarity

ጠብፍ ዐዕዚዐይዕዐዕዚሂዞኮሀህሾ በሃፍረት አለንጋ እየገረፉ ጨርቄን ጥዬ ላብድ ጥቂት እስቲቀረኝ አሰቃዩኝ ይህን ስልዎ ምናልባት በባህሪዬ ተፀዕቼ የእርስዎን ይቅርታ መጠየቅ መሻቴ ይመስልዎ ይሆናል ይህን እንደሚያስቡ በእርግጥ አውቃለሁ ያሻዎትን ቢያስቡ እኔ መች ደንታ ሊሰጠኝ የለዬለት መናጢ መሆን አልተቻለኝም መልካም ወይም መጥፎ ወስላታ ወይም ቅን ትልቅ ሰው ወይም ተባይ አልነበርኩም ካንዱ መስፈር የተሳነኝ አሁን ታዲያ ከስርቻዬ ውስጥ ተወትፌ ብልሀ ሰው መች ለእገሌነት ይበቃል እያልኩ በከንቱ ዕድሜዬን እቆጥራለሁ እገሌነት የየዋሆች ነው አዎ የዘመናችን ብልህ ሰው ሞላጫ ይሆን ዘንድ በኀሊናው ይገደዳል ባኀሪው የሰከነ የምግባር ሰው ደግሞ አእምሮ ስንኩል ውስን ፍጡር መሆን አለበት ይህ በአርባ ዓመታት እድሜዬ የደረስኩበት እምነቴ ነው አርባ ዓመት ሞላኝ። ይህን ጥርጣሬዬን የሚያረጋግጥልኝ ነገር አለ ለምሳሌ የደህነኛውን ሰው ተፃራሪ ማለትም ከተፈጥሮ አብራክ ሳይሆን ከጀርባዋ የዘለቀ ከፍተኛ የአእምሮ ንቃት ያለውን ሰው ቢያስተውሉ ይህ የጓሮ ሰው ከተቃራኒው ተጋፍጦ መቋቋም ባቃተው ቁጥር በላቀ አስተሳሰቡ ራሱን ከአይጥ እንጂ ከሰው አይቆጥርም ምናልባት ግንዛቤው የላቀ ዓይጥ ሊሆን ይችላል ግን ያም ከአይጥነት አያድነውም ተቃራኒው ግን ሰው ነው ዋናው ነገር ግን እርሱ ራሱ ማንም ሳይፈርጀው ነው ራሱን ከአይጥ የሚቆጥረው እስቲ የዚህን አይጥ ምግባር እናስተውል ተበድሏል እንበል ለነገሩ ዘወትር እንደተበደለ ነው ስለተበደለም መበቀል ይፈልጋል በዚህ ጊዜ በውስጡ የሚታመቀው ምሬት ሰው በምሉዕ ተፈጥሮው መቋጠር ከሚቻለው በላይ ነው የገፋውን በሰፈረበት ቁና ሰፍሮ ሊመልስለት ከሌሎች ይልቅ አጥብቆ ይቋምጥ ይሆናል ምክንያቱም ምሉዕ ስብዕናውን የያዘ ሰው ከተጠናወተው ደደብነት የተነሳ የብቀላ ፍላጎቱን ከሚዛናዊ ፍትህ የመነጨ ጉዳይ አድርጎ ሲያየው አይጡ ግን በላቀ አመለካከቱ ነገር አለሙን ከፍትህ ማዶ አሻግሮ ያስቀምጠዋል ከዚያም ወደ ድርጊቱ እንደርሳለን ማለትም ከብቀላው ርጉሙ አይጥ ከመጀመሪያው ጉድ አልፎ ተርፎ በጥያቄና በዩ ዕወዐዩዐዕዕዐዚሬዞኮርዮ በጥርጣሬ መልክ በፈጠረው የጉድ አጥር ተከቦ ከበፊቱ ጥያቄው ላይ ሌሎች ብዙ መልስ አልባ ጥያቄዎች ደራርቦ መውጫ ከሌለው በራሱ ጥርጣሬና ሽብር በከረፋው መቀመቅ ውስጥ ወርዶ ይቀበራል ዙሪያውን ሆነው ዳኝነት ተቀምጠው የሚወቅሱት የምግባር ሰዎች ሲስቁና ሲሳለቁበት ከአፋቸው በሚዘንበው ለሃጭ ታጥቦ ሳለ አንድ ሊያደርግ የሚችለው ነገር ነፍሱ በምሬት ተመርዛ ውርደቱን ተከናንቦ ራሱ እንኳ በማያምንበት የንቀት መሣይ ፈገግታ ከናፍሩን ጠምዝዞ ወደ ጉድባው ማዝገም ብቻ ነው የኛው አይጥ ከአፀያፊው የጉድባው ክርፋት ውስጥ ተወትፎ ወዲያው ከውርደቱ ከመዘለፉና ከመረገጡ የተነሳ በእድሜ ልክ የክፉትና የቂመኛነት ቆፈን ይመረዛል ለዓርባ ዓመታት ሳያሰልስ ከልቡ የቀበረውን ብሶትና ቂም ቆፍሮ እያወጣ በየጊዜው ውርደትና ጉዱን በትጋት እየተረተረና በራሱ እየተሳለቀ ነፍሱን ይቀጣታል ብሶቱን አልሞ ፀንሶ የወለደው እሱ ራሱ መሆኑ ሲያሳፍረውም የዚህ የሃሳብ ውላጅ ጥቃቱን ሥራስር በመፈልፈል ደጋግሞ እያሰላሰለ ከመቆጨት አይታቀብም ያልነበረ በደል ቢኖርስ እያለ በምህረት አልባ ኀሊናው ያውጠነጥናልፁ ከዚህም አልፎ ብቀላውን ለመሠንዘር እንደነገሩ ከተረሳበት የምድጃ ዳር ሲውተፈተፍ ሳለ እንኳ በመበቀል መብቱም ሆነ ችሎታው እምነት የለውም የብቀላ ጥረቱም ከበዳዩ ይልቅ እርሱ ራሱን መቶ እጥፍ እንደሚያሰቃየው ጠ ንቀቆ ያውቀዋል በዳዩ የእንዲህ አይነቱን ሰው የብቀላ ሙከራ መች ከቁንጫ ንክሻ ሲቆጥረውፁ ከጊዜ በኋላ አይጡ በሞት ጥላ ስር ተኝቶ እያጣጣረ በደሉን በዓመታት ከተጠራቀመ ወለዱ ጋር ሰብስቦ እያስታወሰ ያለመደምደሚያ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ግን በዚህ በቀዝቃዛ የሰቀቀን ጓዳ የከፊል ተስፋቢስነትና የከፊል እምነት ቀየከሥቃይ ብዛት ራስዎን ለአርባ ዓመታት ከተቀበሩበት ዋሻ በዚህ በትጋት ከተገነባ ድንግዝግዝ መድረሻቢስነትና ከፍሬ ለመብቃት ያልታደሉ ፍላጎቶች የፈጠሩት መርዝ ከሚፈልቅበት የመዋዥቅ ሕመም ለዘላለም የተተከሉ ውሳኔዎች ከሚገዙበትና የፀፀት ጥርስ ከሚፋጭበት መንደር ነው ቅድም የነገርኩዎ ሃሴተ እርግማን የሚፈልቀው ይህ ዓይነቱ ደስታ እጅግ በመርቀቁና በቀላሉ ሊጨበጥ በጅ ባለማለቱ ጥቂት አእምሯቸው የደበዘዘና ልባቸው የደነደነ ሰዎች ቅንጣቱን እንኳን ሊረዱት አይችሉም ታዲያ እርስዎ ጥፊ ያልቀመሰው ሰው በየት በኩል እንዲህ አይነቱ ደስታ ይገባዋል። ስንት ጊዜ ነበር ሳላጠፋ አውቄ ራሴን ችግርና ጣጣ ውስጥ የከተትኩት የሚገርመው ታዲያ ባልፈፀምኩት ጥፋት ራሴን ደልዬ እያዘንኩና እያለቀስኩ ነፍሴን አሸማቅቃት ነበር ሳስበው ከእንዲህ አይነቱ በሽታ የጣለኝ ልቤ ይመስለኛል ይህ ታዲያ የተፈጥሮ ሕግ ውጤት አልነበረም ምንም እንኳን የተፈጥሮ ሕግጋት ዘወትር ቢበድሉኝም ቅሉ ይህን ታዲያ አሁን እንኳን ሳስታውሰው ያቅለሸልሸኛል ያኔም ሳደርገው እጅግ ያስጠላኝ ነበር ምክንያቱም ካደረግኩት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ቅጥፈቴ ሃፍረተቢስ አስመሳይነቴ ይታየኝና በራስ ጥላቻ እላሽቃለሁ ሁሉም መወሻከት ነበር ፀፀቴ በሃዘን የሚቀልጥ ልቤ የመሻሻል መሃላዬ ሁሉም ለምን በዚህ ሁኔታ ራሴን እቀጣ እንደነበር ይጠይቁኝ ይሆናል መልሱምራ ምንም ሳልሰራ እጆቼን አጣጥፌ መቀመጥ እጅጉን ይሰለቸኝና አልባሌ ነገር ማድረግ ያምረኛል እውነቴን ጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬኮር ነው ራስዎን በውል ቢመለከቱ የዚህን እውነትነት ያዩታል በሌሉበት ጀብዱዎችን እየፈጠርኩና ሕይወትን ቀድጄ እየሰፋሁ እንደምንም ለመኖር ተጣጣርኩ ስንት ጊዜ ነበር ያለምክንያት ከምድር ተነስቼ ተነካሁ ያልኩት። መልስ ሰነፍ ሰው ይህን ስለራሴ መስማት ምንኛ ባስደሰተኝ በወጉ ተለይቼ ታውቄ እገሌነት አገኘሁ ማለት ነበር ሰነፍ ሰው ይህ እኮ ስም ነው ሥራና ማሪዕረግ እውነቴን ነው የምርጦች ክበብ አባል ሆቬ ዋና ዓላማዬና ምግባሬ ሳላሰልስ ራሴን ማክበር ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ይሆናል አንድ የማውቀው ሰው የውድ መጠጦች ስም አዋቂ በመሆኑ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ይኩራራ ነበር በሙያው ታላቅነት አንድም ቀን ጥርጣሬ ሳይገባው ኖሮ ኀሊናው የሰላምና የድል አክሊል ደፍታ ነበር ነፍሱ ከስጋው የተለየችው ይህ ሰው ታዲያ ግብዝ ነው ብለው ያስባሉ። እንዲህ ነው እንጂ ታላቅ ሰው ። ችግሩ ግን ይህ ዓይነቱ ጥቅም ካንዱም ሠፈር ይመደብ ዘንድ ያዳግታል ለምሣሌ አንድ ጓደኛ አለኝ ሰው ሁሉ ያውቀዋል እርስዎም ያውቁታል ጓደኛዬ አንድ ነገር ለማድረግ ሲያቅድ ነገሩ እንዴት በትክክል በደንቡ መደረግ እንዳለበት ግልፅ አድርጎ በርቱዕ አንደበት ይነግርዎታል ከዚያም አልፎ ለሰው በርግጥ የሚያዋጣውን ነገር ተንትኖ ያስረዳዎታል የሚበጃቸውን የማያውቁ ቂሎችንና የቅንነትን ምንነት ያልተገነዘቡ አርቆ ማስተዋል የተሳናቸውን ሰዎች ያንቋሽሻቸዋል ይህ ሰው ታዲያ አንድ አስራአምስት ደቂቃ ያህል ቆይቶ ምንም ነገር ሳያስገድደው ከሚበጀው ነገር ሁሉ በበለጠ ከውስጡ በመነጨ ነገር ተገፍቶ ቀደም ሲል ስለአግባብ ሲለፍፍ የነበረውን የሚፃረር ነገር ያደርጋል ጓደኛዬን የሚመስሉ ብዙ ሰዎች ስላሉ እሱን ብቻ አይፍረዱበት አዎ እንግዲህ ይኸው ነው ለሰው ከሌላ ፍላጎቱና ጥቅሙ ሁሉ የሚበልጥበት ለርሱም ሲል ሕግን ጥሶ አግባብን ረግጦ ሰላምና ብልፅግናን ወዲያ ብሎ የሙጥኝ የሚለው የጥቅሙና ቲኒ ጠዐህዚዞርዮኮ የሚበጀው ነገር ሁሉ ቁንጮ የሆነውና ሊቃውንቱ የዘነጉት የሰው ምርጫው ሌላ ነው ታዲያ እርሱስ ቢሆን የጥቅም አይነት አይደል። መልሱን ለእርስዎ እተዋለሁ የሮማዋ ክሊዎፓትራ ከገረዶቿ ጡት የወርቅ መርፌ እየተከለች ሲያለቅሱና ሲወራጩ ማየት ትወድ ነበር ይባሳል ይህ የሆነው ታዲያ ካሁኑ ጋር ሲነፃፀር በኋላ ቀርነት ዘመን ነው ይሉኝ ይሆናል ካስተዋሉ ግን አሁንም ቢሆን ከሰዎች አካል መርፌ ይሰነቀራል ምንም እንኳን ሰው ነገሮችን አጣርቶ ማየት የቻለ ቢሆንም ሳይንስና ሐቅ በሚጠቁሙበት መንገድ ከመጓዝ ርቆ ይገኛል እርስዎ ግን ሰው በትምህርት አማካይነት ካረጁ ልምዶቹ ተላቅቆ በሳይንስና በቀና አስተሳሰብ ተመርቶ ሊታረም እንደሚችል አይጠራጠሩም ሰው በገዛ እጁ ከስህተት ታቅቦ ፈቃዱን ከሚበጀው ነገር ጋር ማቃቃሩን እርግፍ አድርጎ እንደሚተው እርግጠኛ ነዎት ወይም ደግሞ ሰው የራሱ ነፃ ፈቃድ ያልነበረውና የሌለው የፒያኖ ቁልፍ ስለሆነና የሚኖረውም በተፈጥሮ ሕግጋት በሚገዛ ዓለም ውስጥ ነውና የሚያደርገው ነገር ሁሉ ከግል ፈቃዱ የመነጨ ሳይሆን በነዚህ ሕግጋት መሠረት እንዲሁ የሚከሠት ነገር ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ መሆኑን ሳይንስ ያስተምረዋል ይሉኝ ይሆናል እዬ ግን አልስማማም ምስጢሩ ይህ ከሆነ መደረግ የሚሜኖርበት ነገር ቢኖር እነጊህን የተፈጥሮ ሕግጋት ፈልጎ ማግኘት ነው ያም ሲሆን ሰው ለድርጊቱ ተጠያቂ መሆኑ ይቀርና የሕይወት ጥያቄዎች መልስ ያገኛሉ የሰው ድርጊቶች ሁሉ በእነዚህ ሕግጋት መሠረት ተሰልተው ይወሰኑና በልዩ መዝገብ ተቀምረው ይቀመጣሉሌ እንዲያውም መዝገበቃላትና ኢንሳይክሎፒዲያ የመሳሰሉ ሁሉ ነገር በቅድሚያ ታልሞና ተሰልቶ የሚሰፍርባቸው መፃህፍት ይታተሙና ከዚያ ወዲያ ምንም ግራ የሚያጋባ ያልተጠበቀ እንግዳ ነገር በሰው መታየቱ ያከትማል ከዚያም ይህን የሚሉት እርስዎ ነዎት ሁሉ ነገር ያላንዳች ስህተት ተሰልቶ የተዘጋጀበት እንከን አልባ የሆነ የኢኮኖሚ ግንኙነት ይፈጠርና ጥያቄዎች ሁሉ ከመወለዳቸው በፊት መልስ ያገኛሉ የሰው ልጅ የድል አክሊል ይቀዳጅና የብልፅግና ነጎህ ይቀዳል ታዲያ የዚህ አይነቱ ሕይወት እጆጅግ አሰልቹቺ አይሆንም። ያ ብቻ አይደለም ሰዎች ደግሞ በወርቅ መርፌ መወጋት ግ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ይከጅሉ ይሆናል ይህ የኔ ሃሳብ ነው ምክንያቱም ሰው ሲባል ደደብ ነው ከእግር እስከራሱ ድድብና የወረሰው ምናልባትም ደደብ ባይሆን እንኳን የለየለት ምሥጋና ቢስ በውለታቢስነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ፍጡር ለምሣሌ በዚያ ቅድም ባወሳነው ሁሉ በሠመረበት ምሉዕ የነገው ሥርዓት አንድ ርጉም ሰው ከመሬት ብድግ ብሎ እጆቹን ወገቡ ሳይ አድርጎ ይህን እንከን አልባ ሥርዓት በርግጫ ብለን እንኮታኩተን ላንዳፍታ እንደቅጥያጣ ፈቃዳችን ብንኖር ምናለበት። የሰው ተፈጥሮ ግን የሃሳብም ሆነ የጭፍን ሂደት ሙሉ ሕይወት ነው ቢሳሳትም እንኳን ሕያውነቱ አይካድም ያሳዘንኩዎት ይመስለኛል የተማረና የተመራመረ የወደፊት ሰው እያወቀ ከንቱውንና ጎጂውን የሚከጅልበት አንድ ሁኔታ መኖሩን ለመቶኛ ጊዜ እነግርዎታለሁ ይህን የሚያደርገውኛሦ ዩጠ ፔበዐኮዮ ዎ በአግባቡ የመሻት ግዴታው ሳይታሰር የመከጀል መብቱን ለመጠበቅ ሲል ነው ይህ ቁቂልነት ይህ የወፈፌ ፍላጎታችን አንዳንዴ ከሚበጀን ነገር በላይ ይልቅብናል ጥፋት እንደሚያመጣብንና ቀና አስተሳሰባችን ከሚመክረን ጋር እንደማይጣጣም ስናውቀው እንኳን ምክንያቱም ይህ ጋጠወጥ ክጀላ ውዱን ሐብታችንን ግለሰባዊ ባኀሪያችንን ይጠብቅልናል ግለሰባዊነት የፀጋ ሁሉ ጫፍ ነው ብለው የሚከራከሩ አሉ በርግጥ ከተፈለገ የሰው መሻት በውን ከሚበጅ ነገር ጋር ሊስማማ ይችላል አልፎ አልፎ እንዲህ ሲሆንም ሰውዬውን ጠቅሞ ያስሞግሰዋል መሻት ግን ይበልጡኑ ጊዜ እምቢ ብሎ ይጣመማል ያም ሆኖ ግን ለሚሻው ይበጀዋል አንዳንዴም ውዳሴ ይገባዋል ለምሣሌ ያህል ሰው ደደብ አይደለም እንበል በውነቱ ደደብ ነው ማለት አይቻልም ሰው ደደብ ከሆነ ብልሁ ማን ሊሆን። ሁለት ጊዜ ሁለት ደግሞ ሕይወት አይደለም የሞት መጀመሪያ እንጂ ሆኖም ግን ሁለት ጊዜ ሁለት አራት ነው የሚለውን ነገር ሰው ዘወትር እንደፈራው ነው እኔም እፈራዋለሁ የሰው ስራው ይህን ሁለት ጊዜ ሁለት አራት ነው ለማግኘት መጫር እስከሆነ ድረስ ውቅያኖስን ሰንጥቆ ይጓዛል ሕይወቱን ለዚህ ዓላማ ይሰዋል ማግኘቱን ግን ይፈራል ለምን ቢሉ ማግኘቱ ፍለጋውን እንደሚያቆምበትና የጥረትና የልፋቱን ፍፃሜ እንደሚያበስር ያውቀዋል ለፍቶአደሮች ስራቸውን ፈፅመው ደሞዛቸውን ሲቀበሉ ከመሸታ ቤት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው ያርፉታልፅ እዚያም የሳምንት ስራ አገኙ ማለት ነውሱ ሰው ግን ወዴት ይሄዳል። ሁሌ ነገር ተሳክቶለት ያቀደውን በፈፀመ ቁጥር ሰው ሃፍረት የመሰለ ነገር ጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ ይታይበታል ወደግቡ ለመድረስ መታገል እጅጉን ይወዳል ከግቡ መድረሱን ግን እምብዛም አይፈልገውም ባጭሩ የሰው ተፈጥሮ አስቂኝ ነው ሁለት ጊዜ ሁለት አራት ማለት ደግሞ አስቀያሚ ነገር ነው የድፍረት ድፍረት እጁን ወገቡ ላይ አድርጎ ጢቅ እያለ ከመንገድ የሚጋረጥ ይሉኝታ ቢስ ባለጌ ሁለት ጊዜ ሁለት አራት ነው ማለት መልካም እንኳን ቢሆንም ፍሳጎታችን ውዳሴ ማዜም ከሆነ ሁለት ጊዜ ሁለት አምስት ነው ማለትም አንዳንዴ ውብ ነገር ናት ለሰው የሚበጀው ደሀነኛውና ገንቢው ነገር ብቻ ነው ብለው አጥብቀው በአርምሞ የሚለፍፉትስ ለምንድን ነው። በውስጤ ይተራመስ የነበረውን ነገር ሁሉ በውጫዊ ስሜት አምቄ አስቀምጥ ብዬ ጧት ማታ እያነበብኩ ነበር ጊዜዬን የማሳልፈው ማንበብ በርግጥ ጠ ቅሞኛል ረበሸኝ አሰቃየኝ አስደሰተኝ አልፎ አልፎ ግን ቋቅ ይለኝ ነበር ያኔ ታዲያ ወጣ ብዬ መንቀሳቀስ ያምረኝና ከአልባሌ ርክሰች ገብቼ እዳክራለሁ በዕረፍት አልባነትና በሠላም ማጣት በሽታዬ ምክንያት ያማረኝን ነገር ካሳደረግኩት እፎይ አልልም ማልቀስ መንሰቅሰቅ በሲቃ መጠማረር ልምዴ ነበር ከማንበብ በቀር የማመልጥበት ዋሻ አልነበረኝም ከዚህ በቀር ጉዳይ የምለው ነገር በአካባቢዬ አልነበረምራ ከውስጤ የታመቀው ደስታቢስነት ገንፍሎ ሲፈስ ነፍሴ አጉል ነገር አጥብቃ ትናፍቃለችነፁ መጥፎ መንገድ ዋልጌነት ይህን የምነግርዎ ድርጊቶቼን በምክንያት ለማንተራስ ብዬ አይደለም አዩ እንደገና ዋሸሁ ይህን ሁሉ የነገርኩዎ የምክንያቴን ጭብጥነት አሳይ ብዬ ነው አልዋሸም ብዬ ቃል ስለገባሁ እስቲ ይቺ ማስታወሻ ትሁነኝ ብቻዬን በውድቅት ሌሊት ተንጂክኬ ሄጄ ቆሻሻ ነገር አደርግና ተላብሼው የምመለሠው የሃፍረት ማቅ ከገላዬ ተጣብቆ ይቀጣኛል አንዳንዴም ለጆሮ የሚቀፍ ነገር ከአንደቤቴ ልውጣ እያለ ይታገለኛል ይህን ሳደርግ ሳለሁ ነፍሴ በሥርቻ ህይወቴ ርግማን ነቅዛ ነበር መታየትና የሚያውቀኝን ሰው ማግኘት ስለምፈራ ብርሃን የናፈቃቸው ሰዋራ ቦታዎችን ነበር የማዘወትረው አንድ ቀን በጨለማ በመሸታ ቤት ደጃፍ ሳልፍ ሰዎች ከከረምቦሳ ጠረጴዛ ዙሪያ ተኮልኩለው ሲጨቃጨቁ ቆዩና ከመካከላቸው አንዱን ገፍተው በመስኮት ሲያስወጡት አየሁ ሌላ ጊዜ ቢሆን ኖሮ በድርጊታቸው እጠየፍ ነበር ያኔ ግን የተገፋውን ሰው መሆን ተመኘሁና በደረሰበት ውርደት ቀንቼ ወደ ከረምቦላው ጠፍዐህዐሂዞኮር እስከዚያ ድረስ ግን የዶሮ ቤትን ከቪላ አልቆጥረውም ይህ የመስታወት ቤት ሕንፃ የሃሳብ ውላጅ ቢሆንም እንኳን ከድንቁርናዬ የመጣ የተፈጥሮ ህግ የማይፈቅደው የህልም እንጀራነፁ ታዲያ ተፈጥሮ ባይፈቅደው እኔን ምን ሲገደኝ። ልክ አሁን በጣፍኳት አንዲት ቃል እንኳን እኔው ራሴ እምነት ቢኖረኝ ምንኛ ጥሩ ነበር የዘበዘብኩትን ባምንበትም ቅሉ በሌላ በኩል ደግሞ እንዲሁ የምቀላምድ ይመስለኛል ታዲያ ይህን ሁሉ ለምን ቀባጠርክ። ቀጥዬ የምጀምረው አይነት ጉድ ለህትመት አይገባም ለአንባቢያን አይሆንም ያን የማደርግበትም ወኔው የለኝም ዩጠብፍ ዐዐዩዐዐዚዞርዮ እንዲህ ነው ነገሩ ሰው ሁሉ ከባልንጀራው በቀር ለሌላ የማይገልጠው ነገር ሞልቷል ሌላ ደግሞ ራሱም ቢሆን በድብቅ ተንጂክኮ የሚመለከተው ድብቅ ምሥጢር አለው በመጨረሻም መልካም ሰው የምንለው ሁሉ ከራሱ እንኳን የሠወረው ብዙ ቋጠሮ ተሸክሟል እንዲያውም የሰው ጨዋነቱ በሳቀ መጠን ይህን መሣይ ከራሱ እንኳን የሰወራቸው ጉዶች በዚያው ልክ በዝተው ይርመሠመሣሉ ያም ሆነ ይህ እስካሁን በስጋት ሸፋፍኙ ያቆየኋቸውን ጀብዱዎቼን ለማስታወስ በቅርቡ ድፍረት አግኝቻለሁ ግን ልክ አሁን ገበናየን ሳስታውሰው ብቻ ሳይሆን ከትቤ ላስቀምጠው ስቆርጥ ሰው ለራሱ መዋሸቱን ትቶ ሳይፈራ ከእውነት ፊት ይችል እንደሆነ ማየት ፈለግኩ ማን ነበር እውነተኛ የግል ሕይወት ታሪክ ማግኘት አስቸጋሪ ነው ያለው። እያልኩ እገረም ነበር ለምሳሌ አንድ አብሮኝ የሚሠራ ሰውዬ ፊቱ ተዣጎርጉሮ ማጅራት መች ስላስመሠለው ለዓይኔ ያስጠላኝ ነበር የሌላው ባልደረባዬ ያረጀ ልብስ ደግሞ እድፍ ደልቦበት ይከረፋል ታዲያ እነሺህ ሰዎች በልብሳቸው በፊታቸውም ሆነ በማንነታቸው ሃፍረት ተሰምቷቸው አያውቅም ሰው ይጠሳናል ብለውም አያስቡም ለሰው አስቀየምን ብለው ቢያስቡ እንኳን ተቀያሚው አለቃቸው እስካልሆነ ድረስ ግድ አይሰጣቸውም ዛሬ ነገሩን ሳጤነው ገደብ በሌለው ትዕቢትና ግብዝነቴ ምክንያት ከራሴ ከምጠብቀው የላቀ ስብዕና የተነሳ ለነበረኝ እንከን ሁሉ መልሴ ሃዘንና ራሴን መጥላት ሆኖ ኋላም ይህንን የወደቀ የራስ ግምቴን ከሰው ያገኘሁት አድርጌ እንደቆጠርኩት አውቀዋለሁ ለምሣሌ መልኬን እጅግ እጠላው ነበር ፊቴ ላይን የሚያስከፋ ማስጠሎ ስራ በሄድኩ ቁጥር ውዳቂነቴን እደብቅ ብዬ በተቻለኝ መጠን ያልነበረኝን ግርማ ሞገስ ተላብሼ እጀነን ነበር ምንም እንኳን ፊቴ ውብ ባይሆንም ቢያንስ ሕይወት የሠፈነበት የብልህ ሰው ፊት ከመሰለ ይበቃል ብልም ይህን ሳስብ እንኳን ታዲያ ፊቴ ውበትንም ሆነ ብልህነትን እንዳላጎናፀፈው ይገባኛል ሌላው ሁሉ ቀርቶ ሰዎች ፊቴን የብልህ ፊት አድርገው ቢያዩልኝ ኖሮ ርጉም መምሠሉ ባልከፋኝ ነበር ባልደረቦቼን አንዱ እንኳን ሳይቀር እጠላቸው እንቃቸውና እፈራቸው ነበር በል ሲለኝ ደግሞ ከኔ እጅጉን የተሻሉ አድርጌ ጠፎ ዐበህይዩዐዐሂዞኮር አያቸዋለሁ። ብዬ ተፍቼበት እንዳልሄድ ደግሞ የምከፈልበት ማደሪያዬ ሆነብኝ ያሻኝን ባስብም እንኳን ጨክኙፔሼ ልተፋበት አልቻልኩም ሮማንቲክ የምንለው ሰው ሌላ ዕድል ሳይኖረው ስራው ላይ ከሚተፋ አእምሮውን ቢስት ይቀለዋል አእምሮውን ስቶም ወደ ዕብድ ሆስፒታል ካልወሰዱት በቀር ከስራው በጅ ብሎ አይፈነቀልም ይህ ስሜት የነካካቸው ብዙዎች አያብዱም እንዲያውም ጊዜ በገፋ ቁጥር በያዙት መንገድ ከሹመት ወደ ሹመት ይተላለፋሉ ሾላካነታቸውና ጥበባቸው ይገርማል ልባቸው የተቃራኒ ስሜቶች ጎጆ ናት የቱንም ያህል ቢረክሱ እንኳን የእምነት ማተባቸውን አይበጥሱም ለዚህ እምነታቸው አንዲት ድንጋይ ባይሸከሙና የምላጮችና የሌቦች ቁንጮ ቢሆኑ እንኳን በልባቸው የከበሩና ለእምነታቸው በመቆርቆር የሚያነቡ ናቸው ቀድሜ ወደ ጀመርኩት ልመለስና ከሥራ ጓደኞቼ ጋር በቅፅበት ያጦፍኩት ጓደኝነት ብዙም አልቆየም ወዲያወ ተጣላኋቸውና እርግፍ አድርጌ የተውኳቸው ይመስል ሰላምታ እንኳን ነፈግኳቸው ይህ የሆነው አንዴ ብቻ ነው ሌላውን ጊዜ ግን ብቸኛ ነበርኩ ጠፍዐይ ከቤቴ ስሆን ዋና ሥራዬ ማንበብ ነበር በውስጤ ይተራመስ የነበረውን ነገር ሁሉ በውጫዊ ስሜት አምቄ አስቀምጥ ብዬ ጧት ማታ እያነበብኩ ነበር ጊዜዬን የማሳልፈው ማንበብ በርግጥ ጠ ቅሞኛል ረበሸኝ አሰቃየኝ አስደሰተኝ አልፎ አልፎ ግን ቋቅ ይለኝ ነበር ያኳ ታዲያ ወጣ ብዬ መንቀሳቀስ ያምረኝና ከአልባሌ ርክሰት ገብቼ እዳክራለሁ በዕረፍት አልባነትና በሠላም ማጣት በሽታዬ ምክንያት ያማረኝን ነገር ካላደረግኩት እፎይ አልልም ማልቀስ መንሰቅሰቅ በሲቃ መጠማረር ልምዴ ነበር ከማንበብ በቀር የማመልጥበት ዋሻ አልነበረኝምል ከዚህ በቀር ጉዳይ የምለው ነገር በአካባቢዬ አልነበረም ከውስጤ የታመቀው ደስታቢስነት ገንፍሎ ሲፈስ ነፍሴ አጉል ነገር አጥብቃ ትናፍቃለች መጥፎ መንገድ ዋልጌነት። እያለ ይንፈራፈራል አንቶን ብድር ስጠይቀው ተገረመ ግንባሩን ቋጥሮ በዝምታ እየተመለከተኝ ቆየና ከክፍያ ቀን ሁለት ሳምንት በኋላ ያበደረኝን ከደሞዜ ቆርጦ እንደሚሰጠኝ ተስማምቼ ፈርሜ ገንዘቡን ወሰድኩ እንዲህ እንዲህ እያለ ሁሉ ነገር ዝግጁ ሆነ ውቡ የቀበሮ ፀጉር ከካፖርቴ አንገትያ ላይ ተተከለ እኔም ለቁርጡ ቀን መዘጋጀት ጀመርኩ አዩ እንዲሁ በጭፍን ዘልዬ ድርግም ማለት የለብኝም ሁሉም ነገር በዘዴና በርጋታ ቢሆን ይበጃል ያም ሆኖ እንኳን ከብዙ ሙከራ በኋላ ተስፋ መቁረጥ ያንዣብበኝ ጀምሮ ነበር ከመቶ አለቃው ጋር ደፍሬ ልላተም አቃተኝ ከዚያ ሁሉ ዝግጅትና ውሣኔ በኋላ ላልምረው ተገዝቼ ሄጄ ከፊቴ ሳየው ሐሞቴ ፈስሶ እኔ ቀድሜ መንገድ እለቅና እሱ መፈጠሬን ረስቶ መሠሥ ብሎ ያልፋል ጭራሹን ልጠጋው ስል መፀለይ ጀመርኩ እግዚአብሔር ቆራጥነቱን ሠጥቶኝ የወጠንኩትን ያስፈፅመኝ ዘንድ አልተሳካልኝም አንድ ቀን ታዲያ ሳላደርገው ላልመለስ አምርሬ ሄድኩና ያደረግኩት ነገር ቢኖር ከፊቱ ስንዝር ሲቀረኝ ወኒዬ ፈረጠጠና እግሩ ስር ተደናቅፌ እንደጎማ ኳስ መንጠር ብቻ ነበር እሱም በርጋታ ተራምዶኝ አለፈ ያኔ ሌሊት ታምሜ አደርኩ ሰውነቴ እንደእቶን ነደደ አቃዥኝ ተወራጨሁ ከዚህ በኋላ የስቃዬ ፍፃሜ በተመኘሁት መንገድ መጣልኝ ለነገሩማ ከፍፃሜው ቀን በፊት ይህን አደገኛ ዕቅዴን እርግፍ አድርጌ መተው እንዳለብኝ ወስጄ ነበር ከዚያም ይህንን ከንቱ ደባዬን እንዴት እንደምተወው ለማየት ለመጨረሻ ጊዜ ወደኔቭስኪ ጎዳና ሄጄ ሳለሁ ከሰውዬው ሦስት እርምጃ ሲቀረኝ በቅፅበት ቆረጥኩና ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ጋ ዓ አይኔን ጨፍጌ ገሠገሥኩ ትከሻ ለትከሻ ተላተምን። ከትምህርትቤት ወጥቼ ነፃነቴን እንደተቀዳጀሁ እዚያ ካወቅኋቸው ሁሉ ጋር ተቆራረጥኩ ከነሺፒያ ሁሉ ልጆች ሁለት ወይም ሦስት ብቻ ናቸው እስካሁን ሰላምታ የማልነፍጋቸው ከእነርሱም አንዱ ሲሞኖቭ ነው ሲሞኖቭ በትምህርቱ እምብዛም አልነበረም ዝምተኛና ልዝብ ነበር በአንዳንድ ነገሮች ላይ የነበረውን የግል አመለካከቱንና ግልፅነቱን ተመልክቼ በአንድ ወቅት ቀርቤው ነበር ለጥቂት ጊዜም ያህል በጓደኝነት ጡፈናል ወዲያው ግንኙነታችንን ውርጭ ወረሰው እንጂ ዛሬ ታዲያ የዚህ ትውስታ እየረበሸውና ወትሮ ያየብኝ እኩይነቴ ያልለቀቀኝ እየመሠለው የሚጠላኝና የሚርቀኝ ይመሥለኛል ቢሆንም ግን እኔ ዓይኔን ጨፍ እቤቱ መሄዴን ቀጠልኩ አንድ ሐሙስ ቀን የአንቶን ቤት ለእንግዶች በሚዘጋበት ዕለት ሲሞኖቭን አስታወስኩት ወደቤቱ እያመራሁ ሳለሁም ሲሞኖቭ የእኔ ከአጠገቡ መሆን እንደሚያውከውና መሄድ እንደሌለብኝ ተሰማኝ ነገር ግን ይህን መሣይ የሃሣብ ሹክታዎች ለክፋት ይመሥል ልሸሸው ከሚገባኝ ነገር ጎትተው ስለሚያላጉኝ ሳላመነታ ቀጥ ብዬ ወደቤቱ አመራሁ ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት ከአንድ ዓመት በፊት ነበር ሁለት የቀድሞ አብሮተማሪዎቼንም ከሱ ጋር አገኘኋቸው ስገባ ከፍ ያለ ቁም ነገር የሚወያዩ ይመስላሉ የሌኣን መኖር ከምንም አልቆጠሩት ካየኋቸው ዓመታት ስላለፉ እኔን ችላ ማለታቸው ደነቀኝ ከክፍሉ ዝንብ የገባ ያህል እንኳን ልብ አላሉኝም ትምህርት ቤት ሣለሁ ልጆች ሁሉ ቢጠሉኝም እንኳን ይህን የመሠለ የንቀት ኮሶ ተግቼ አላውቅም በስራዬ ጥሩ ደረጃ አለመድረሴ የለበስኩት ድሪቶዬና ባጠቃላይ ወድቄ መቅረቴ በእነርሱ አመለካከት የዋጋቢስነቴ ምልክት በመሆኑ እንደናቁኝ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ ገባኝ ይህን የመሠለ ውርደት ተቀብዬ ግን ይሁን ለማለት አልተዘጋጀሁም ነበር ሲሞኖቭማ ሲያየኝ ጭራሹን የተገረመ መሠለ ለነገሩ ከቤቱ ባየኝ ቁጥር ይገርመዋልር በሁኔታቸው ግራ ተጋብቼ ቅስሜ ተሰብሮ ሲከፋኝ ተቀምጩ ወሬያቸውን ማዳመጥ ጀመርኩ እንደዚያ በተመስጦ የሚወያዩት ወደሌላ ክፍለሃገር በቅርቡ ለሚሄደው እዝቬርኮቭ ለሚባል ጓደኛቸው በማግስቱ የመሸኛ ራት ስለማዘጋጀት ነበር አቶ እዝቬርኮቭም የኔው አብሮተማሪ ነበር ትምህርታችንን ልንጨርስ ስንቃረብ ነበር እሱን መጥላት የጀመርኩት የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ሳለን እዝቬርኮቭ መልከመልካም በሁሉ የተወደደ ሲፈነጥዝና ሲቦርቅ የሚመሽለት ልጅ ነበር ያኔ እንኳን ደስተኛና መልከመልካም በመሆኑ ብቻ ነበር የጠላሁት በትምህርቱ ድሮም ደካማ ነበር እየቆየ ይባሱን ተስፋቢስ ቢሆንም ግን በታዋቂ ዘመዶቹ ምክንያት ያለችግር ትምህርቱን ጨርሶ ለመመረቅ በቃ ትምህርቱን በጨረሰበት ዓመት ትልቅ ርስት ከሁለት መቶ ገባሮች ጋር ወርሶ በኛ በድሆቹ ላይ ይወጣጠርና ይበጣጠስ ጀመር ገራገር ቢሆንም እንኳን ብልግናው ልክ አልነበረውም የዚያን ጊዜ ተማሪዎች ጥራዝ ነጠቅ የኩራትና የራስ ክብር ሥሜታቸው እንኳን እዝቬርኮቭን ከመለማመጥና ጫማውን ከመሣም አላዳናቸውም ጉራው እየናረ በሄደም ልክ አጃቢውና አወዳሹ በዛ አሁን ሳስበው ያ እዝቬርኮቭን ከቦ የሚያጨበጭብ ተማሪ ሁሉ ከሱ ጥቅም ያገኝ መሥሎት ሳይሆን እንዲያው ተፈጥሮ ስላደለችውና ስለሞላለት አድናቆቱን በማጎብደድ ማሳየቱ እንደነበር ይገባኛል ከዚያም አልፎ እዝቬርኮቭ በመካከላችን የማኀበረሠ። ጥሩ አድርጌ መለስኩለት እዝቬርኮቭ ግን ደደብ ቢሆንም በቀላሉ የማይከፋ እፍረተቢስ ነውና ድንፋታዬን ስቆ አለፈው ሙከራዬ ሳይሳካልኝ የተሳቀለት እሱ ብቻ ሆኖ ቀረ ከዚያን ቀን ጀምሮ እንደቀልድ እያደረገ በነገር ይኮረኩመኝ ጀመር እኔ ግን ቂሜን በሆዴ ቋጥሬ በይምሰል ንቄት ልጓም ተሸብቤ መልስ አልሰጠሁትም ከተመረቅን በኋላ ሊቀርበኝ መሞከሩ ራሴን ስላሞካሸልኝ ፊት አልነሳሁትም ነበር ሆኖም ግን የማይቀረውን ወዲያው ተቃቅረን ተራራቅን ከዚያ ቆየት ብሎ በኮሌኔልነት መሾሙንና ጋጠወጥ አኗኗር መጀመሩን ሰምቼ ነበር ኋላም ስለደረሰበት ማዕረግ ወሬ ደርሶኛል መንገድ ላይ እያየኝ ሠላምታ ሲነፍገኝ እኔን ከመሠለ ትቢያ ጋር ሰላምታ በመለዋወጥ ደረጃውን ሲያራክስ መታየት ፈርቶ እንደሆነ ገብቶኛል አንዴ ደግሞ ከቴያትር አዳራሽ አንደኛ ደረጃ ክፍል ውስጥ ተቀምጦ የማዕረግ መለያውን ከትከሻው ኮልኩሉ የአንድ የሽማግሌ ጄኔራል ሴቶች ልጆች ፊት ሲያጎበድድና ሊነጠፍላችሁ ሲል ሳየው ትምህርቱን በጨረሰ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ራሱን መረን ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ መልቀቁን ተመለከትኩ ምክንያቱም ምንም እንኳን ያኔም መልካምነቱና ግርማ ሞገሱ ባይጠፋም አካሉ ረግቦና ከብዶ ነበር ሰላሳ ሲሞላው ሥቡ እንደ ዉንጠለጠል ጥርጥር አልነበረኝም ታዲያ የወትሮ አብሮተማሪዎቼ ሪ ት ለማዘጋጀት ደብ እንቅ የሚሉት ለዚሁ እዝቬርኮጣ ነበር ራሳቸውን የሱ እኩል አድርገው ባይመለከቱም እንኳን በእነዚያ ሦስት ዓመታት ከእዝቬርኮቭ ጋር የነበራቸውን ጓደኝነት ጠብቀዋል ሲሞኖቭ ቤት ከመጡት መሐል አንደኛው ፌርፊችኪን የተባለ በሰው መቀለድና ማሾፍ የሚወድ ድውይ ጦጣ ፊት ነው ከልጅነታችን ጀምሮ አምርሬ የምጠላው ዋነኛ ጠላቴ ነበር ፌርፊችኪን በልቡ ቦቅቧቃ ሆኖ ሳለ ጀግና መሳይ አይናውጣ ጥፍራም ነው እሱ ነበር ከእዝቬርኮቭ አጃቢዎች አንዱ እዝቬርኮቭን ማዘል የሚቃጣው ቢጠቅመኝ ብሎ ነበር አንዳንዴም ገንዘብ ይበደረዋል ሌላው ሲሞኖቭ ቤት ያገኘሁት ትሩዶሊቦቭ በምኑም እገሌ የማይሉት ተራ ወታደር ነበር ቁመቱ ዘለግ ያለና ፊቱ ቅዝቃዜ የለበሰ ለሃብትና ለሹመት የሚያደገድግ ከጣት እስከማታ ስለዕድገትና ደሞዝ ቢያወራ የማይታክተው ሰው ነው የእዝቬርኮቭ የሩቅ ዘመድ በመሆኑ በመካከላችን ለየት ያለ ቦታ ተሰጥቶት ነበር ከምንም ስላልቆጠረኝ ትህትና ቢነፍገኝም ብዙም አልተከፋሁም «መልካም» አለ ትሪዶሊቦቭ «እያንዳንዳችን ሰባት ብር ብናዋጣ በሃያ አንድ ብር ጥሩ እራት መብላት እንችላለን እዝቬርኮቭን ግን አናስከፍለውም» «ልክ ነህ እኛ ጋብዘን አናስከፍለውም» ሲል ተስማማ ሲሞኖብ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ለበ «በርግጥ እዝቬርኮቭ ዝም ብሉ ስንከፍል የሚያይ ይመስላችኋል። ለምን። « በበኩሌ የምንጎራደደው እግሬን ለማፍታታት ነው ይህን ደግሞ ማንም ሊከለክለኝ አይችልም » ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር አልፎ አልፎ ወደክፍሉ የሚገባው አስተናጋጅ ሥራውን ትቶ በመገረም ያየኝ ነበር ከመመላለስ ብዛት ጭንቅላቴ ዞረብኝ አንዳንዴ ቅዙት ውስጥ ያለሁ ይመስለኛል ላብ ያጠምቀኝና በዝ እጁ ይደርቃል አሥር ዓመታት ወይም ሃያ ወይም አርባ ዓመታት እንኳን አልፈው ነፍሴን የውርደት አተላ የጋትኩበትን ይህን ርጉም ሰዓት ሃፍረት እየወረሰኝ እንደማስታውሰው እየቆየ ሲሰማኝ ልቤን በስለት የወጉት ያህል ያመኛል ራሱን በፈቃዱ ይህን ከመሠለ ይቅርታ ከማይገባው ቅሌት ውስጥ የሚከት ሰው እንደሌለ እያወቅኩት ከምድጃው ወደ ጠረጴዛው መንቆራጠጤን ቀጠልኩ «እነዚህ እንስሶች ምን የመሣሠሉ ሃሳቦችና ስሜቶች በውስጤ መኖራቸውን ቢያውቁ ኖሮ » እያልኩ አስብ ነበር ጠላቶቼ የተቀመጡበትን ሶፋ እያስተዋልኩ እነርሱ ግን የኔን መኖር ዘንግተዋል አንዴ ብቻ እዝቬርኮብ ስለሼክስፒር ሲያወራ ሰምቼው የማንጓጠጥ ሳቅ ስስቅ ሁሉም ተመለከቱኝ አሳሳቄ ሲታወቀኝ ያደረግኩት የክፋትና የአትርሱኝ ባይነቴ ሲቃ ስለነበር ወሬያቸውን አቁመው በጥላቻ ለአንድ ደቂቃ ያህል ሲያዩኝ እኔ በቸልታ ከምድጃው ወደ ጠረጴዛው እንጎራደድ ቀጠልኩ ያም ምንም አላመጣም አንዳቸውም አልተናገሩኝም መልሰው ረሱኝ አምስት ሰዓት ሞሳላ «እሁኑኑ እዚያ መሄድ አለብን። » አለ እዝቬርኮቭ ከሶፋው ብድግ ብሎ «አዎ እንሂድ » ብለው ተስማሙ ሁሉም ያኔ ነበር በድንገት ከአዝቬርኮቭ ፊት ሄጄ ተጋረጥኩትፁ ታክቼ ሆድ ቦቱሶኝ ስለነበር ለሥቃዬ ፍፃሜ ካመጣልኝ ምንም ነገር ባደርግ አይገደንም ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ ነበር ራሴን መስቀል እንኳን ቢሆን። » « ምን ማለት ነው « ለምን። ቆሜ ጠበቅኳት ወዲያው ተመለሠች አስተያየቷ ለማላውቀው ጥፋድ ይቅርታ የምትጠይቀኝ አስመስሏታል ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ ሁለንተናዋ የቀድሞው አልነበረም መጀመሪያ ሳገኛት ለብሳው የነበረው የግዴለሽነት የጥርጣሬና የግትርነት ጥላዋ ተገፍፎ በምትኩ እምነት ገርነትና ዓይናፋርነት ሠፍኖባታል ሕፃናት የሚወዱትን ሰው አንድ ነገር ሲጠይቁ ገዕታቸው እንዲህ ይመስላል ምንም ሳትነግረኝ ያሰበችውን ሁሉ የማውቅ ልዩ ድንቅ ፍጡር የሆንኩ ይመስል በዝምታ የተጣጠፈ ወረቀት ሰጠችኝ በዚያ ወቅት ፊቷ ላይ ወገግ ብሎ የፈካው የኩራት መንፈስ ባደረገው ጥሩ ነገር የተመሠገነ አንድ ፍሬ ልጅ ላይ የሚታየውን ይመስል ነበር ወረቀቱን ዘረጋሁትኹ አንድ የሕክምና ተማሪ የፃፈሳት ደብዳቤ ነበር ደብዳቤው በጥራዝ ነጠቅ ቃላት የተሞላ አፃፃፉም መራቀቅ የሚከጅለው ቢሆንም እንኳን ትሕትና የተሞላበት የፍቅር ደብዳቤ ነበር ያነበብኩትን በትክክል ባላስታውሰውም ሊያስመስሉት ከማይቻል እውነተኛ የውስጥ ስሜት የፈለቀ እንደነበር ማወቄ ትዝ ይለኛል አንብቤ ስጨርስ በዕረፍት ማጣት የሚቁነጠነጡ ዓይኖቿ ለገለፀችልኝ ምሥጢር ምላሽ እንድሰጥ በጉጉት ሲጠብቁኝ አየሁ እንዴትና የት እንዳገኘችው አጠር አድርጋ ደስ እያላት ነገረችኝ «ከቤተሰብ ቤት ጥሩ ሰዎች ማንም ገና ምንም መጥፎ ነገር ከማያውቅበት » አለችኝ «አየህ እዚህ ገና አዲስ ነኝ ብቻ እንትኑን እዚህ እቆያለሁ ብዬ አሳስብም እሄዳለሁ ዕዳዬን ከፍዬ እንደጨረስኩ ከዚያ ለግብዣ ከሄድኩበት ቤት አንድ ተማሪ ነበርነፁ ከኔ ጋር ስንደንስና ስናወራ አመሸን ኋላ በወሬ በወሬ ሪጋ ሳለሁ እንደሚያውቀኝ ነገረኝ ሁለታችንም ልጆች ሳለን አብረን እንጫወት ነበር ድር ዩጠፎ ዐበህህይዩዐዐሂሬዞኮር ቤተሠቦቼንም ያውቃቸዋል ስለአሁኑ ኑሮዬ ግን ምንም አያውቅም እዚያ አብራኝ ሄዳ በነበረች ጓደኛዬ በኩል በማግስቱ ይህን ደብዳቤ ላከልኝ እና እንደዚህ ነው» ትረካዋን እንደጨረሰች እንደማፈር ብላ ዓይኗን ሠበረች ምሥኪን የዚያን ተማሪ ደብዳቤ ድንቅና ብርቅ ነገር የሆነ ይመስል በጥንቃቄ አስቀምጣዋለች እሷም እንደሌሎቹ በእውን ያፈቀራትና በአክብሮት የተመለከታት ሰው መኖሩን ሳላውቅ እንዳልሄድ ስትከንፍ ሄዳ ያንን ደብዳቤ አምጥታ አሳየችኝ ምናልባት ደብዳቤው ለፍሬ ሳይበቃ ከሳጥኗ ተቀምጦ ሊያረጅ ተፈርዶበት ይሆናል ያ ቢሆንም እንኳን ዕድሜ ልኳን አለኝ የምትለው የአንድ ወቅት ምንነቷን መሥካሪ ቅርሷ አድርጋ እነደምትቆጥረው እርግጠኛ ነኝ ምንም አልተናገርኩ። » እያልኩ ሳስብ የሊዛን ነገር ለጊዜው ረሳሁት መጀመሪያ ከሲሞኖቭ ትናንት ማታ የተበደርኩትን ገንዘብ ባስቸኳይ መመለስ ይገባኛል ለዚህም ሲጨንቀኝ የፈጠርኩት መላ ከአንቶን አሥራአምስት ብር መበደር ነበር ዕድሌ ሲቀና አንቶን የዚያን ቀን ጧት በቀኝ ጎኑ ተነስቶ ኖሮ ብድሩን እንደጠየቅኩት እሺ አለኝ በዚህ ባላሰብኩት መልካም አጋጣሚ ተደስቼ የውሉን ወረቀት እየፈረምኩ ሳለሁ ከጓደኞቼ ጋር ፓሪስ ሆቴል እንዳመሸሁ ነገርኩት « አንድ ጥሩ ጓደኛዬ አብሮ አደጌን ልንሸኝ ተንቀባርሮ ያደገ ብዙ የለመደ ነው ይህ ጓደኛዬ ጥሩ ቤተሰቦች አሉት የታወቁ ባለፀጎች እሱም ከፍ ያለ ሥራ ነው ያለው ብታየው እንዴት አይነት አስተዋይና ተጫዋች መሠለህ የቆነጃጅት ነገር ግን አይሆንለትም እና እሱን ልንሸኝ ተሰባስበን ከልክ በላይ ጠ ጣን » ብዬ ሳላፍር ለአንቶን ወሸከትኩለት ሳይከብደኝ በማንነቱ ያልተከፋ ሰው መስዬ ከቤቴ እንደደረስኩ ወዲያው ለሲሞኖቭ ደብዳቤ ፃፍኩ የዚያ ደብዳቤዬን ለዛና ቅንነት እስካሁን ድረስ በመደነቅ አስታውሰዋለሁ ወዲያ ወዲህ ሳልል በኩራት ጥራዝነጠ ቅ ቃላት ሳልጨምር ለተፈጠረው አጉል ነገር ሁሉ ጥፋተኛው እኔ መሆኔን አመንኩ ለጥፋቴ ምክንያትም መጠጥ ያልለመደ አንጎሌ በአልኮል ተመርዞ እንደሆነና ከአሥራአንድ ሰዓት ጀምሮ ይመጣሉ ብዬ ኪፓሪስ ሆቴል ቁጭ ብዬ ስጠብቅ የጠጣኋት የመጀመሪያዋ ዩጠፍ ዐበህህይዩዐዐሂዞሀ ብርጭቆ ፍጥር አድርጌ ራሴ ላይ ስለወጣችብኝ መሆኑን ጠ ቀስኩ የይቅርታ ጥያቄዬን በቀጥታ ለሲሞኖቭ አቅርቤ ይህንኑ እሱ ለሌሎቹ እንዲያስተላልፍልኝ አሳሰብኩት በተለይም ለሲሞኖቭ ሲሞኖቭን « ሳልዘልፈው እንዳልቀረሁ የሰነበተ ሕልም ያህል ትዝ ይለኛል » ብዬ ፃፍኩ ወደ መጨረሻውም ላይ እያንዳንዳቸውን አግኝቼ ይቅርታ ብጠይቃቸው በወደድኩ ሆኖም ግን ራሴን ስላመመኝና ከዚያም በላይ በሥራዬ ስላፈርኩበት ያን ማድረግ እንደማልችል ገለዕኩ ከሌላ መንገድና ምክንያት ከመደርደር የተሻለ በመሠለኘኝ አፃፃፌ ነፃነትና አልፎ አልፎ በሚታይበት ተገቢ ግዴለሽነት ደስ ብሎኝ ያለፈው ምሽት ምንም ሊገረሙበት የማይገባ ተራ ነገር እንደሆነ አስመሰልኩት ደብዳቤዬን ሲያነብቡ አስበውት እንደነበረው በተፈጠረው ነገር አፍሬ ጣይዋን ማየት ተስኖኝ የተቀመጥኩ እንዳይመስላቸው የትናንት ማታውን መቃቃር የምመለከተው ማንም ራሱን የሚያከብር ሰው ሊያየው እንደሚገባ አድርጌ መሆኑን እንዲረዱልኝ ስል ደብዳቤዬን ደመደምኩ «ጨዋ ሰው አልፎ አልፎ ይሳሳታል » አልኳቸው አፃፃፌ የጌትነት ለዛ ያለው መሠለኝ እያነበብኩት ሳለሁ ይህን የመሠለ ደብዳቤ መፃፍ የቻልኩት የተማርኩና የሠለጠንኩ ሰው በመሆኔ ነው ስል ራሴን አሞካሸሁትሱ ከፊቴ በተጋረጠው አጋጣሚ ሌሎች ቢወድቁ ኖሮ ራሳቸውን እንዲህ በጥበብ ማውጣት ያስቸግራቸው እንደነበር እርግጠኛ ነበርኩ ግን ለመሆኑ ትናንት እንደዚያ የሆንኩት በመጠጡ ምክንያት ሳይሆን ይቀራል። ትናንት ከልቤ ነበር የተናገርኩትፁ ከውስጤ የነበረው ነው በቃላት ተጠቅልሎ ከአፌ የወጣው ትዝ ይለኛል የፈለግኩት የሊዛን ክቡር መንፈስ ከሚያንቀላፋበት መቀስቀስ ነበር በዚያ ሳቢያ ጥቂት ብታለቅስም ይበጃታል እንጂ አይጎዳትምራ ሆኖም ግን መረጋጋት ተሣነኝ እቤቴ ከተመለስኩ በኋላ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ተኩል ሆኖ በዚያ ሰዓት ሊዛ እንደማትመጣ እያወቅኩ አእምሮዬ ሊላቀቃት አልቻለም ከሷ ጋር ካሳለፍኳቸው ሰዓታት ሁሉ ልሄድ ተነስቼ ሻማ ባበራሁበት ቅፅበት ያየሁት ሁኔታዋ በጭንቀትና በፍርሃት የተገረፈ ፊቷን እደብቅ ብላ ፈገግታ ስትከልስበት ያ ብቻ ነው ቁልጭ ብሎ ከዓይነኀሊናዬ የተቀረፀው ያኔ ታዲያ ከአሥራአምስት ዓመታት በኋላ እንኳን ሊዛን የማስታውሳት በነዚያ ጥቂት ሰኮንዶች እንዳየኋት ብቻ አልመሠለኝም ነበር ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር በማግስቱ ይህን ሁሉ ጭንቀትና ሥጋት እረፍት ያጣ አእምሮ ከልክ በላይ አጋኖ እንደፈጠረው ከንቱ ነገር ቆጥሬ ልረሳው ዝግጁ ነበርኩ ይህን ለመሣሠለ አላስፈላጊ ጭንቀት የሚዳርገኝ በሽታ እንዳለብኝ ስለማውቅ « ነገርን መካብ እወዳለሁ ያ ነው ችግሬ » እያልኩ ደጋግሜ ሳነበንብ « ቢሆንም ግን ሊዛ መምጣቷ አይቀርም » ይለኛል ሌላ ድምፅ በዚህ እጅግ ከመጨነቄ የተነሳ አልፎ አልፎ ቁጣ ከውስጤ እንደገሞራ ይነዳል « ትመጣለች። አፖሎን ነበር ከዚህ ሃሳቤ ያላቀቀኝ አፖሎን ፈጣሪ ለቅጣት የላከብኝ ርግማኔ ነው ለዓመታት ሳናሰልስ ተነታርከናል አምርሬ ነው የምጠላው እሱን የምጠላውን ያህል ሰው በህይወቴ ጠ ልቼ አላውቅም አፖሎን ጠና ያለ ሰው ነው ራሱን እርስዎ ማለት የሚቃጣው የትዕቢት ቋት በትርፍ ጊዜው ልብስ መጠቃቀም ይወዳል እኔን ታዲያ በማላውቀው ምክንያት እጅግ ይንቀኛል ልታገሠው በማልችለው ዕብሪት ቁልቁል ይመለከተኛል ለነገሩ ጠፎ ዐበህዩዐዐሂሬዞኮርዮ ማንንም ይንቃል በጥንቃቄ ተከፍሎ የተደለሰ ሉጫ ፀጉሩ የተለጠ ፈባት ራሱን በተለይ በትጋት የሚያበጥራትና በአትክልት ዘይት የሚያርሳት ከግንባሩ በላይ ያለች ቁንጮውን መጥፎ ነገር ወጥቶት አያውቅ ይመሥል ሁሉን ተጠይፎ የተገጠመ አፉን ቢመለከቱ ስለራሱ ቅንጣት ጥርጣሬ ገብቶት የማያውቅ ሰው መሆኑን ያውቁታል በምድር ላይ እሱን የመሠለ ወግ አጥባቂና ራሱን ማክበር ቸል የማይል ሰው ያለ አይመስለኝም የልብሱን አዝራሮችና የጣቶቹን ጥፍሮች የሚያደንቅ ግብዝ ሰው ነው ጌታዬ እንጂ አገልጋዬ እንዳልሆነ ሁሉ ይበጣጠስብኛል ሲናገረኝ ቃላቱን ቆጥቦ ነው ሲመለከተኝ ዕብሪትና ንቀት ከፊቱ ላይ አነብና በንዴት እቃጠላለሁ የተከፈለበት ሥራውን ሲሰራ ውለታ የሚያደርግልኝ ያስመስለዋል ለነገሩ እኮ ምንም ያህል አይሠራልኝም ሊሠራልኝም የሚገደድ አይመስለውም የቂሎች ሁሉ ቂል አድርጎ እንደሚቆጥረኝ አውቀዋለሁ ጥሎኝ ያልሄደውም በየወሩ ደሞዙን ስለምከፍለው ነበር በሱ ምክንያት አምላክ ብዙ ኃጢአቴን ይቅር ይለኛል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ አንዳንዴ ጥላቻዬ እጅግ ከመምረሩ የተነሳ አረማመዱን ብቻ አይቼ ኮሶ እንደጠጣ ሰው ያንገሸግሸኛል ከሁሉም በላይ የሚያስጠሳኝ ግን መኮላተፉ ነው ምላሱ ከልክ በላይ ረዝሞ ስለተፈጠረ ይመሥለኛል ሲናገር እንደትንሽ ልጅ ይኮላተፋል ይህ ታዲያ ያማረለትና ልዩ የሚያደርገው እየመሠለው ይኩራራበታል ሲናገር ድምፁን ዝቅ አድርጎ እጆቹን ከኋላው አጣምሮ ምድር እያስተዋለ ነው በተለይ ከወንበሩ ላይ ተቀምጦ ዳዊት ሲደግም ስሰማው እንዴት እንደሚያናድደኝ መግለፅ ያቅተኛልፁ በዚህ ምክንያት ብዙ ጊዜ ብንጣላም በጨለማ ዳዊት መድገሙን አላቆመም ድምፁን ከፍ አድርጎ ቃላቱን እየጎተተ ፍትሐተ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂዞኮር ሙታን የሚያደርስ ይመስል ማዜም እየቃጣው ዳዊት ማንበብ አጥብቆ ይወዳል የሚገርመው ታዲያ ዛሬ የተመኘው ደርሶለት ዘመድ የሞተባቸው ሰዎች ዳዊት እንዲደግምላቸው ይቀጥሩታል ከዚያም አልፎ አይጥ በማጥፋትና የጫማ ቀለም በመሥራት ተክኖ ባለብዙ ሙያ ሆኗል የኔ አገልጋይ ሆኖ ሳለ እንደዚያ እየጠሳላሳሁት ላባርረው ተስኖኝ ነበር ያለሱ መኖር የማልችል ይመስል ውጣ ብለውም ኖሮ በምንም መንገድ ሊወጣልኝ የሚስማማ አይመስለኝም እኔም ያኔ የተሟላ ቤት ውስጥ ለመኖር አቅሙ አልነበረኝም ያች ቤቴ ከሰው ሸሸቼ የምወተፍባት ዋሻዬ ነበረች ታዲያ አፖሎንም የቤቴ አካል ሆነና ለሰባት ዓመታት ተቆራኝቶኝ ኖረ ደሞዙን ለሁለት ወይም ለሦስት ቀናት ማዘግየት የማይታሰብ ነበር ሳልከፍለው አንድ ቀን ሲያልፍ ማድረግ የሚጀምረው ነገር መግቢያ ቀዳዳ እስከማጣ ድረስ ያሰቃየኝ ነበር ሊዛን ባገኘሁበት ዕለት የተፈፀመው ነገር ሁሉ መንፈሴን መርኮዞት ስለነበር የአፖሎንን ደሞዝ ለሁለት ሣምንት አዘግይቼ ልቀጣው ወስጌ ነበር ይህን ማሠብና ማድረግ ከጀመርኩ ሁለት ዓመት ሆኖኛል እኔ ላይ መጨማለቁን እርግፍ አድርጎ እንዲተው ትምህርት ልሰጠውና ከፈለግኩ ክፍያውን ማቆየት መቻሌን ላሳየው ለምን ደሞዙን እንደማልከፍለው ሳልገልፅለትና አውቄ ዝግት አድርጌው ኩራቱን ረግጨ እሱ ቀድሞ እንዲጠይቀኝ ላስገድደው ከሳጥኒ ሰባት ብር አውጥቼ ገንዘቡ እንደነበረኝ ላሳየውና ብሩ እያለኝ ሳልከፍለው የቀረሁት እንዲሁ ልከፍለው ስላልፈለግኩ ጌታው እንደመሆኒ መጠ ን ለጊዜው አለመክፈል ስለመረጥኩ ይህን ያደረግኩትም አክብሮት የራቀው ባለጌ በመሆኑና በትህትና እንድከፍለው ቢጠይቀኝ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮር ግ ምናልባት በድርጊቴ ተፀፅቼ እንደምሠጠው ካልሆነ ግን ሌላ ሁለት ሦስት ወይም አራት ሣምንታት እንደሚጠብቅ ላረጋግጥለት እንደዚያ አምርሬ ልቀጣው ስፎክር ቆይቼ ድሉ በመጨረሻ የሱ ሆነ አራት ቀን ሳይሞላኝ ተሸነፍኩኝ ሁሌ ደሞዙ ለጥቂት ቀናት ሲዘገይበት የሚያደርገው ነገር ነበረው ይህን ቀድሞ ብዙ ጊዜ ስለሞከርኩት ጠንቅቄ አውቀዋለሁ በመጀመሪያ ፊት ለፊት በተገናኘን ቁጥር ተኮሳትሮ ለረጅም ጊዜ ያስተውለኛል እንደምንም ብዬ ይህን አስተያየቱን ልብ ያላልኩ ከመሰልኩ ዘዴውን ይለውጥና ያለምክንያት ከክፍሌ ውስጥ በዝግታ እየተራመደ ገብቶ በሩ አጠገብ ይቆምና አንድ እጁን ከኋላው አድርጎ እያነበብኩ ከተቀመጥኩበት ወይም ወዲያ ወዲህ ስንቆራጠጥ በንቀት ይመለከተኛል ምን እንደፈለገ ስጠይቀው አይመልስልኝም ተለጉሞ ሲያፈጥብኝ ይቆይና ሲበቃው አፉን ጥብቅ አድርጎ ገጥሞ በርጋታ ወጥቶ ወደክፍሉ ይሄሃዳል ይህን ካደረገ ከሁለት ወይም ሦስት ሰዓት በኋላ እንደገና መጥቶ ከፊቴ ይገተራልሱ አንዳንዴ ብስጭት ሲያቃጥለኝ ለምን ከፊቴ እንደቆመ ሳልጠይቀው ጭንቅሳቴን በድንገት ወንጭፌ ቀና አደርግና መልሼ አፈጥበታለሁ በዚህ አይነት ለሁለት ደቂቃዎች ያህል እንፋጠጥና እሱ ቀድሞ እየተጀነነ ሲወጣልኝ ለጥቂት ሰዓቶች እረፍት አገኛለሁ ይህ ድርጊቱ ሃሣቤን ሳይለውጠው ቀርቶ እምቢተኝነቴን ከቀጠልኩ በማፍጠጡ መሐል በረጅሙ መተንፈስ ይጀምራል የኀሊናቢስነቴን መጠን ገምግሞ ተስፋ የመቁረጥ ዓይነት ትንፋሽ ከዚያም ፀጉሬን ነጭቼና ስሬ እስከሚገታተር ጮሄ ገንዘቡን ወርውሬለት መገላገል እመርጣለሁ ዩጠፎ ዐበህይዩዐዐሂሬዞኮርዮ አሁን ገና ያን የፍጥጫ ጨዋታውን ሊጀምር ከክፍሌ መሠስ ብሎ ሲገባ ቱግ ብዬ በቁጣ ተቀጣጠልኩ በቋፍ ነበር ያለሁት አሱ ሳይጨመርብኝም ቆይ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

تعليقات:


memezon

خيارات التنزيل | تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي | كتاب اليوم

© dirzon | شروط الخدمة | خصوصية | حول | خدمات | اتصال