Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ኪዳን ዘሠርክ ሀለከ ለአብ ዘኢይማሰነ መድኃኔ ነፍስነ ለንዌድሰከ እግዚኦ ሒሐለከ ዘአምልብነ ናቸው ለ መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ መጽሐፈ ስለሐሳዊ መሲሕና ተከታዮች በይበልጥ በስፋት ይናግራል መጽሐፈ ዲድስቅልያ ዲድስቅልያ የመጽሐፉ ስም ሲሆን ትርጉሙም ትምህርት ማለት ነውይህም የኢኦተቤክ የሐዲስ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር ውስጥ አንዱና ጥንታዊው ነው ዲድስቅልያ ዘቅዱሳን ሐዋርያት ይባላል መጽሐፉ ቀድሞ ሲል ወደ ግዕዝ ቋንቋ ተተርጉሞና ተጠብቆ ኖሯራልአንዲያውም ከፍተኛ ዋጋው ቀደም ብሎ ስለታወቀ ከእንግሊዘኛ ትርጓሜው ጋር በአውሮፓ ታትሞልይህ መጽሐፍ የቅዱሳን ሐዋርያት አስተምህሮ የሥርዓት ክፍል ሲሆን አንቀጾችን የያዘ መጽበለ ትምህርት ወተግሣጽ ነውእነዚህም ስለሰው ልጅ ሕይወትና ሞት ስለ ፍቅረስብ እና ፍቅረእግዚአብሔር ስለ ምሥጢረ ጥምቀት ስለጾምና ጸሎት ሰለ ምሥጢረ ቁርባን ሰለ ካህናት ክብርና አገልግሎት ሰለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሰለሚፈፀሙ የተለያየ ምስጢራት ይናገራል መጽሐፈ ዲድስቁልያ አበይትና ንዑሳን አንቀጾች አሉትበእያንዳንዱ አብይ አንቀጽ ውስጥ ብዙ የተለያዩ ንዑሳን ክፍሎች ይገኛሉ መጽሐፈ ቀሌሞንጦስ መጽሐፉ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ኤጥሮስ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውና ቅዱስ ቀሌሞንጦስ ከእርሱ አግኝቶ የጻፈው ነው።
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ክፍል አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ መጽሐፍ ቅዱስ ማለት ምን ማለት ነው። አብዛኛዎቹ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የተፃፉት በፅብራይስጥ ሲሆን ትንቢተ ዳንኤል የተፃፈው ግን በአረማይክ ቋንቋ ነውየሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በዕብራይስጥ ከተፃፈው ከማቴዎስ ወንጌልና በሮማይስጥ ከተጻፈው ከማርቆስ ወንጌል ውጪ የተቀሩት የተፃፉት በዘመኑ በአብዛኛው ሕዝብ መነጋገሪያ በነበረው በፅርዕግሪክ ቋንቋ ነበር የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ አካባቢ ወደ ግዕዝ ተተርጉሟልምንም እንኳን ቅዱሳት መጻሕፍት በመጀመሪያ የተተረጎሙት ወደ ፅርዕግሪክ ቋንቋ ነው የሚሉ ቢኖሩም ሰባው ሊቃውንት ቅዱሳት መጻሕፍቱን የተረጎሙት ከክልበፊት ዓመት ዓለም በበጥሊሞስ ዘመነ መንግስት ነውበዚህም መሠረት ወደ ግአዝ ከተመለሰበት ጋር ሲነፃፀር በመካከላቸው የ ዓመት ልዩነት ይታያልስለዚህ የግሪኩ ትርጉም ሁለተኛ መሆኑ ግልፅ ነውየግሪኩ ትርጉም ሴኙቱ አጊንትየሰባው ሊቃውንት ትርጉም በመባል ይታወቃል ኑክለስ እና ዮናታን የአይሁድ ሊቃውንት ብሉይ ኪዳንን ወደ አረማይክ ቋንቋ በተኛው መክዘ በፄሮዲመስ ዘመነ መንግስት አባ ጄሮም ወደ ኢየሩሳሌም በመጓዝ ለ ዓመታት የዕብራይስጥና የግሪክ ቋንቋዎችን ካጠና በኃላ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ሹልጌት ተርጉሞታል ትርጉሙም ሹልጌት በመባል ይታወቃልሹልጌት በሮም ይኖሩ የነበሩ ሹልገስ እየተባለ የሚጠሩ ሕዝቦች ቋንቋ ነውአባጄሮምፄሮኒመስ መጽሐፍ ቅዱስን ከሹልገስ ወደ ላቲን እየተረጎመው ሳለ ዐረፈይህን የእሱን ጅምር ከእርሥሠ በኃላ የተነሥ ሰዎች እንዳጠናቀቁት ይነገራል የመጽሐፍ ቅዱስ ዓላማ ሀትምህርተ ፃይማኖት ማስተማር የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ዓላማቸው ስለ አግዚአብሔር ሕልውና መግለጽና ነገረ ሄዛሃይማኖት ማስተማር ነውዮሐመዝ አቤቱ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማያትም የእጅህ ስራዎች ናቸው ሊየእግዚአብሔርን ቸርነት ድንቅ ስራውን ተዓምራቱን መግለጽ ኛ ነገ መዝ አቤቱ እንደቸርነትህ መጠን ማረኝ መዝ ማቴ ይሁዳ በ ብር ለመሸጥ መስማማቱን ማቴ ለምጻሙን እንዳነጻ ሉቃ ሒየእምነትን ታላቅነት መግለጥ ለምሳሌ ሠለስቱ ደቂቅ በእምነት የእሳቱን ኃይል ማጥፋታቸውን አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሁ ዳንኤል በእምነት የአናብስቱ አፍ መዝጋቱ ሁ ጌዴዎን ያለ ጦር መሳርያ በእምነት የአሕዛብ ሰራዊትን ድል ማድረጉን መበእግዚአብሔር ያመኑ ቅዱሳንን ተጋድሎ መግለጥ ምሳሌየነህምያ የኢየሩሳሌምን ቅጥር መስራት የአስቴር በጾም በጸሎት ሕዝበ እስራኤልን መታደግ ሠለሰው ሕሊና የሚከብዱ በእምነት ብቻ የምንረዳቸው ድርጊቶች መግለጥ የኢያሱንፀሐይንገዝቶማቆምኢያሱሉቃማቴፀ ረየዘለዓለም ሕይወትን መስጠት ሰዎችን ወደ ድህነት ንስሐመጥራት ነው «የመማራችን ዓላማው የሕይወት ለውጥ ለማምጣት መሆን አለበት» አቡነ አስጢፋኖስ ሐዋልስራ « አውነተኛ አምላክ የሆንህ አንተን ብቻ የላኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት» መዝ ሕዝ ማቴ የመጽሐፍ ቅዱስ ባሕልና ቋንቋ መጽሐፍ ቅዱስ የራሱ የሆነ ባሕልና ዘይቤ አለው ይህም ለተጻፈለት ሰው የጸሐፊውን ሁኔታና በተጻፈበት ቦታ ይወሰናል ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ባህሎችን ጠንቅቆ ሳያውቁ በራስ መተርጎም ለስህተት ይዳርጋል አንደ ራስ ባህልም ማሰብ አይገባም ለምሳሌ ወንድም የሚለው ቃል በመካከለኛ ምስራቅና በኢትዮጵያ ያለው ትርጉም አንድ ሲሆን በምዕራባዊያን ግን ትርጉሙ ሌላ ነው በምዕራባዊያኑ ወንድም የሚባሉት በአንድ ነገድ ልጅነት ኛ ሳሙ በዝምድና ዘጸ በባልንጀርነት ኛሳሙ በሃይማኖት ሕብረት ሮሜ ፊል ዕብራዊያን ቃልን ደጋግመው መናገር ባህላቸውና ቃል ማጽኛ ነው አብርሃም አብርሃም ክፍ ሙሴ ሙሴ ዘጸ ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ማቴ ማርታ ማርታ ሉቃ ዣ ዴፍዴዒዴዒዥኞሜዒፌዒሏዒኳ «አውነት እውነት እልፃለሁ ሰው ዳግመኛ ከመንፈስ ቅዱስና ከውዛፃ ካልተወለደ » ዮሐ የዕብራዊያን የሰዓት አቆጣጠር ከ ሰዓት ጀምሮ እንደ ንጋት ይቆጠራል የእረኛ ጠባይ በኢትዮጵያ ልማድ ከሚጠብቋቸው በጎች ከኋላ እየነዳ የሚፄድ ሲሆን በእስራኤል ከፊት ከፊት እየመራ ይሄዳል የስም አወጣጥ የአነጋገር ዘይቤ ማኅበራዊ ኑሮ እንዲሁም የአጻጻፍ ስልት እንደ ሕዝቡ ባህል ስለሚለያይ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ስለዚህም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚንጸባረቀውን ባህል ለይቶ ለማወቅ ያስፈልጋል የመጽሐፍ ቅዱስ መልክዓ ምድር አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በመጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ ድርጊቶች የተፈጸሙባቸው ህዝቦች ሀገሮች ባህሎች ተራሮች ወንዞች ወዘተ ይገኛሉ እነዚህ ሁሉ ግን በየራሳቸው ታሪክ ምሳሌና ትርጉም አላቸውነገር ግን ይህን ሁሉ ለመረዳት በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም የእስራኤልን ባህል ማወቅ አስፈላጊ ነው ሀገረ እስራኤል የተመረጠችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ባይቻልም የሀገሪቱ መልክዐ ምድር ከሚያስደስቱ የዓለም ገጽታዎች መመደቡ ወብ በሆነ ፀጋ ላይ ሄይማኖታዊ ፀጋ ታክሎ ልዩ ስፍራ ስለሰጣት የመጀመሪያ ሰው አዳም መኖሪያና መቀበሪያ ስትሆን ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው ያደገው ዞሮ ያስተማረው ተአምራቱን የፈጸመው የሞተው የተነሳውና ያረገው በዚህ ቦታ ነው በዘመነ ብሉይም ሆነ ሐዲስ በሺህ ለሚቆጠሩ አመታት የአፍሪካ የአውሮፓና የእስያ የንግድ አገናኝ መስመር በመሆኗ ማዕከለ ምድር በመሆኗ አጽመ አዳም ያለበትበመሆኗ ክፍል ሁለት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብሉይ ኪዳን የቆየየጥንት ውል ወይም ስምምነት ማለት ነው የአንድ አምላክ አማኞች የዕብራዊያንን ታሪክ ይተርካል ስለ መሲኽ ክርስቶስ መምጣት የተነገሩት ትንቢቶች በብዛት አሉበት ብሉይ ሲባል ህጉ ወይም ቃል ኪዳኑ ሁሉ ያረጀ ነው ማለት አይደለምግን ዘመኑ አርጅቷል ብዙ ጊዜም አልፋል ስለዚህም በዚህ ዘመን የነበረ መሆኑን ለማስረዳት ሲል ብሉይ ኪዳን ይለዋል የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከተፃፉበት ጊዜበያዙት ሀሳብና ከአፃፃፋቸው ሁኔት አንፃር በአራት ምድቦች ይከፈላሉ እነርሥም » የሕግየኦሪትመጽሐፍት ሩ የታሪክ መጽሐፍት ሩ የመዝሙርና የጥበብ መጽሐፍት » የትንቢት መጽሐፍት ናቸው የሕግ መጻሕፍት የኦሪት መጻሕፍትም በመባል ይታወቃሉኦሪት ቃሉ የሱርስት ሲሆን ብርፃን ማለት ነው በዕብራይስጥ ቶራ በግሪክዕርዕ ኖምስ ይባላል ትርጉሙም ሕግ ማለት ነው በቁጥር አምስት ሲሆኑ ፀሐፊውም ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነውአነዚህም መጻሕፍት እንደየይዘታቸው የተለያየ ስያሜ ተሰጥቷቸዋል ኦሪት ዘፍጥረትዘልደት የሰነ ፍጥረትን ልደትአጀማመርና አመጣጥ የሚያስረዳ በመሆኑ ይህን ስያሜ አግኝቷልከህግ መጻሕፍትም ሲፃፍ የመጀመሪያው ነው ምዕራፎች ያሉት ሲሆን የመጽሐፉን ይዘት በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፍለዋል ከምዕራፍ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ስለዓለም አፈጣጠርየሰው ልጅ በኃጥያት ስለመውደቁና ስለመጀመሪያዎቹ አባቶች በዝርዝር ቀርባቧል እንዲሁም ለሰው ልጅ የተሰጠውን የፈቃድና የፍላጎት ነፃነትንም ያመለክታል « ከምዕራፍፀ የሰው ልጅ ኃጥያት መብዛት በንፍር ውሃ እንዲጠፉ መሆንየባቢሎን ግንብ በመስራታቸው ቋንቋቸውን እግዚአብሔር አንደ ደባለቀባቸው ተመልክቷል ከምዕራፍ የአብርሃምን መጠራትየይስሐቅ ልጆችን ያዕቆብንና ዔሳውን ያነሳል ከምዕራፍ በሰፊው የያዕቆብን ታሪክ ይይዛል ብኩርናን እንዳገኘ በህልሙ ስለተገለጠለት ሰማያዊ ምስጢር ጋብቻን ስለመመስረቱ ተብራርቶ ይገኛል እግዚአብሔርም ቃል ኪዳን እንደገባለት ኦሪት ዘጸአት ጸአት የግአዝ ቀል ሲሆን ትርጉሙም መውጣት ማለት ነው ምእራፎች ሲኖሩት በአራት ዋና ዋና ክፍሎች መክፈል ይቻላል ከምዕራፍ ግብፃውያን በአስራኤላውያን ላይ ስለፈፀሙት የግፍ አገዛዝ ስለ ሙሴ ልደትናበሚነደው ቁጥቋጥ ውስጥ የሙሴ መጠራትና ወደ ግብፅ ተመልሶ ወገኖቹን ከባርነት ነፃ አንዲያወጣ ከአግዚአብሔር ስለመታዘዙ የሚያወሳ ነው ከምዕራፍ ሙሴና አሮን በፈርዖን ፊት ስለመቆማቸው በእስራኤላውያን ላይ የባርነት ቀንበር ስለመጥበቁ በግብፆች እምቢተኝነት ምክኒያት በግብፅ ህዝብ ላይ ስለደረሱት ዐስር ተከታታይ መቅሰፍቶች ቃላ ከምዕራፍ ስለ አስራኤል ከግብፅ መውጣትና አግዚአብሔር ያደረገላቸውን ድንቅ ስራ በማየታቸው ለአምላካቸው የምስጋና መዝሙር ማቅረባቸውን የመሶለክታል ከምዕራፍ በሲና ተራራ ላይ እግዚአብሔር ለሙሴ ዐሥሩጽን ትአዛዛት የተፃፉበትን ፅላት መስጠቱ አስራኤል የወርቅ ጥጃ ሰርተው ስለማምለካቸውና አንደገና የቃል ቂዳኑ ሕግ ስለ መምጣቱ ኦሪት ዘሌዋውያን ሌዋውያን ከቱ የእስራኤል ነገድ የአንዱ የሌዊ ዘር ናቸውየብሉይ ኪዳን ካህናት ሌዋውያን ስለነበሩ ስለ ኦሪት ካህናትየክህነት ሥርዓትና አገልግሎት በሰፊው የሚገልፅ ነው ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በ ዋና ዋና ክፍሎች ይከፋፈላል ከምዕራፍ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ስለሚቀርቡት የመስዋዕት ዓይኖች ማለትም ስለ አንስሳት አዕዋፍ ዱቄት ዘይትና ፅጣን አቀራረብ መስዋዕቶቹ የሚቀርብባቸው ምክንያቶች ከእግዚአብሔር ድኃነትን ለመለመን እግዚአብሔርን ለማመስገንና ለካህናት ወይም ስለ ህዝቡ የበደል ዕዳ ማስተሰሪያ መሆናቸውን የሚገልፅ ነው « ከምዕራፍ ለእግዚአብሔር አገልጋይነት አሮንና ልጆቹ እንዴት የክህነት ሹመትን እንደተሾሙ የዘይት መቀባቱ ሥነ ስርዓት ከዚያም ለ ቀናት ከድንኳኑ እንዳይወጡ መደረጉ ናዳብና አብድዩ ሥርዓት በማፍረሳቸው የተፈፀመባቸው ቅጣት ተዘርዝራል ከምዕራፍ የእግዚአብሔር ሕዝብ በመብሉበሰውነቱ በልብሱበቤቱ ንፁህ ቅዱስ መሆን አንደሚገባው እንረዳለን ከምዕራፍ ከወንድም ሆነ ከሴት ሰውነት በሚፈስ ፈሳሽ ምክንያት ከሚመጣው ርኩሰት የሚቀደሱበትን የመንፃት ሥነ ሥርዓት ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ቀን የራሱንና የህዝቡን ኃጢአት ለማስተሥረይ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ስለሚገባበት ስለ ኃጢአት ሥርየት ቀን ይገልፃል ከምዕራፍ ደም መብላትና ደሙ ሳይፈሰው ታንቆ የሞተውን አንስሳ መብላት መከልከሉ የተከለከሉ ጋብቻዎችና ልዩ ልዩ ሕግጋት ይገኙበታል ከምዕራፍ ከአረማውያን አሞልኮና የተለያዩ ጥንቆለ ሥራዎች መከልከልና ወደነዚህ ቦታዎች መፄድ የሚያመጣውን ቅጣትና ካህናት የተቀደሱ መሆን እንደሚገባቸው ተዘርዝራል ምዕራፍ ስለ ልዩ ልዩ ሕጎች በዓላት መደንገግ በኪዳነ ታቦት ፊት ለፊት ባለው ቦታ በየቀኑ የወይራ ዘይት መብራት ያለበት ስለመሆኑ ለአግዚአብሔር ስለሚቀርብ መሥዎዕተ ኅብስት የድፍረት ኃጢአት በሚያደርጉ ሰዎች ላይ መፈፀም ያለበት ቅጣት ተዘርዝራል ከምዕራፍ በሰባተኛው ዓመት ምድሪቱን ከእርሻ ስለ ማሳረፍ ኢዮቤልዮ በዓል ሕግጋትና ሥነ ሥርዓት ለአግዚአብሔር ህግጋት መታዘዝስለሚያስገኘው በረከት አለመታዘዝስለሚያመጣው ቅጣት ስለ ስእለት የተደነገጉ ህጎች ኦሪት ዘጉልቁ ትልቁ በግዕዝ ቁጥር ማለት ነው የአስራኤልን ልጆች ሙሴ እንዲቆጠር አግዚአብሔር ያዘዘው በመሆኑና ስለ አቆጣጠሩም ታሪክ የሚዘረዘር በመሆኑ ይኸን ስያሜውን አግኝቷል አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በዐራት ዋና ዋና ክፍሎች ተክፍሷል « ከምዕራፍ በሲና ሰፍረው ሳሉ የሕዝብ ቆጠራ መጀመሩንና ከሲና ተነስተው ወደ ዮርዳኖስ ያደረጉት የጉዞ ታሪክ ይገኛል ከምዕራፍ እስራኤላዊያን ከሲና ተራራ እስከ ቃዴስ በረሣ ያደረጉትን ጉዞ ይተርካል « ከምዕራፍ ስለ ዐሥራ ሁለቱ ሰላዮች እስራኤላዊያን በእግዚአብሔር ላይ በማጉረምረማቸው የእግዚአብሔር ቁጣና በሙሴ አማላጅነት ስለ መዳናቸውና እንዲሁም የአግዚአብሔርን ሥራ በመዘንጋታቸው በምድረ በዳ ዓመት እንደተንከራተቱ እና የሞዓብ ንጉስ ባላቅ በበለዓም አማካኝነት እስራኤልን ለማስረገም ቢሞክርም አግዚአብሔር ግን ከመርገም ይልቅ እንዲባርካቸው እንዳደረገ ተገልፃል « ከምዕራፍ እስራኤላዊያን ወደ ከነዓን ለመግባት ስለመዘጋጀታቸው ስለ አስራኤላዊያን ርስትና የመሬቱሞ ክፍፍል ድንጋጌዎች ተዘርዝረዋል ኦሪት ዘዳግም ሸዳግም በቁሙ የተደገመ ማለት ነውይኽም በኦሪት ዘጸአትበኦሪት ዘሌዋውያን በኦሪት ዘጉልቁ የቀረቡትን ሕግጋትና ትእዛዛት በስብከት መልክ ስለሚደግማቸው ነው ለዚህም ሙሴ በናብውበዔባሪ ተራራ በሞዓብ አገር ኦሪት በመድገም ቃልኪዳኑ መታደሱን አሳወቀ ምዓራፎች ሲኖሩት በዐራት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላልአእነሱም « ከምዕራፍ አግዚአብሔር ለሕዝቡ ያደረገላቸውን ያሳያል ከምዕራፍ እግዚአብሔር ለሕዝቡ የሰጣቸውን ሕጎችና ደንቦችን በድጋሚ ይተረጎማል ከምዕራፍ ግብረገባዊ ሕጎችን ማረጋገጥና የሕግ ፈጻሚነት ምክሮች ይገኛሉ ከምዕራፍ ኢያሱ የሙሴ ተተኪ ሆኖ ስለመሾሙ የሙሴ የመጨረሻ ምክርና ለሕዝቡ ያቀረበው ቡራኬ ስለክርስቶስ የተነበየው ግልፅ ትንቢት ይገኝበታል የታሪክ መጻሕፍት ብዛታቸው ነውእነዚህም መጻሕፍት በአብዛኛው የእስራኤልን ሕዝብና የነገስታትን ታሪክ በሰፊው ይተርካሉ ቱ ነገደ እስራኤል ከሙሴ በላ የእስራኤል ሕዝብ መሪ ሆኖ በተመረጠው በኢያሱ ወልደነዌ አማካኝነት መከፋፈላቸውከኢያሱ ሞት በኃላ እስራኤላዊያን ያለምድራዊ መሪ በእግዚአብሔር መንግስት ብቻ መተዳደራቸው እግዚአብሔር ለእስራኤላዊያን መሳፍንቶችን ማስነሳቱ ከሳኦልሰለሞን ድረስ እስራኤላውን ለ ዓመታት ሳይከፋፈሉ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በአንድ መንግስት ሰር እንደነበሩና በሮብአም ጊዜ ለሁለት እንደተከፈሉ በበደላቸውም ምክንያት አስራኤላውያን ዐስሩ ነገድ በአሶር ሁለቱ ነገድ በባሊሎን እንደተማረኩ ከ ዓመት የባቢሎን ምርኮ በኃላ አስራኤላውያን ወደ ሀገራቸው እንደተመለሥ የመሲኹ የትውልድ ዘር ከዳዊት ቤት መሆኑንም ጭምር እነዚህ መጻሕፍት ያስረዳሉ መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ ፀሐፊው ኢያሱ ሲሆን ትርጉሙም እግዚአብሔር አዳኝ ማለት ነው ይዘቱየአስራኤል ሕዝብ በእግዚአብሔር ኃይልና በኢያሱ መሪነት ከነዓንን እንደወረሱ ይተርካል ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ መሳፍንት መስፍን ፈራጅ አስተዳዳሪ ማለት ነው ይህን ስያሜውን ያገኘው ከኢያሱ ሞት በላ እስከ መጀመሪያው የእስራኤል ንጉስ ሳአል ድረስ እስራኤልን ለ ዓመታት ገደማ ያስተዳድሩ ስለነበሩ መሳፍንት ስለሚገልፅ ነው በመጽሐፈ መሳፍንት የተገለፁት ቱ መሳፍንት ጎቶንያል መሳ ኢያዐር መሳ ናዖድ ዮፍታሔ ሰሜጋር ኢብፃን ባርቅ ኤሎም ጌዴዎን ዓብደን አለሜሎክ ሳምሶን ቶላ መጽሐፈ መሳፍንት ምዕራፎች ሲኖሩት ፀሐፊውነብዩ ሳሙኤልነው መጽሐፈ ሩት ሩት በዘመነ መሳፍንት የነበረች ሞዓባዊት ሴት ናትበአስራኤል ሀገር ረሀብ ተከስቶ በነበረ ጊዜ ከይሁዳ ነገድ አቤሜሌክ የተባለ ሰው ኑኃሚን ከተባለች ሚስቱ መሐሎንና ኬሎዎን ከተባሉት ሁሉት ወንዶች ልጆቹ ጋር ወደ ሞዓብ አገር ተሰድዶ ነበር አቤሜሌክ ከሞተ በኃላ ከሁለቱ ልጆች መሐሎን ሩትን አግብቶ ነበር አርሱም ልጅ ሳይወልድ ሞተ ኑኃሚን ወደ ሀገራ ለመመለስ በፈለገች ጊዜ ሩትም ተከትላ ፄደች ከዚያም ቦዔዝ የተባለውን የአቤሜሌክ ዘመድ አግብታ ኢዩቤድ የተባለውን የዳዊትን አያት ወልዳለች መጽሐፈ ሩት ከአሕዛብ ወገን የነበረችውን ሩት በእምነቷ ምክንያት እንደተቀበላት እና የዳዊት አያትም እንደሆነች ያሳያል መጽሐፈ ሩት ምዕራፎች አሉትፀሐፊውም ነቢዩ ሳሙኤል ነው መጽሐፈ ሳሙኤል አንደኛ ሳሙኤል ማለት የእግዚአብሔር ስም አምላካዊ ስም እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው ሳሙኤል ከዘመነ መሳፍንት መጨረሻ የተገኘ ነቢየ እግዚአብሔር ነው ፀሐፊው ነቢዩ ሳሙኤል ነው አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በዚሁ መጽሐፍ ምዕራፍ ላይ ሳሙኤል መሞቱ ስለተገለፀ ከመጽሐፍ የተወሰነው ክፍል በናታን ወይም በጋድ እንደተፃፈ ይገመታል ኛ ይዘቱ ስለ ካህኑ ኤሊ ልጆች ስለ ሳሙኤል ስለሳዖል መውደቅና ስለ ዳዊት መነሳት ይገልፃል ምፅራፎች አሉት መጽሐፈ ሳሙኤል ሁለተኛ ይህ ሁለተኛ የሚገልፀው ታሪክ ሳሙኤል ከሞተ በኃላ ያለውን ነው ይዘቱ ቅዱስ ዳዊት በይሁዳ ዓመት በኢየሩሳሌም ዓመት በአጠቃላይ ዓመት በንጉስነት አንደመራ ስለታቦተ ጽዮን የቅዱስ ዳዊት በደልና ንስሐ ያደረጋቸውን ጦርነቶች ይገልፅልናል ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ነገስት አንደኛ አንደኛና ሁለተኛ ነገስት መጻሕፍት ከዳዊት ልጅ ከሰለሞን አንስቶ አስከ ይሁዳ መንግስት ማለቂያ ድረስ ያለውን የ ዓመት የእስራኤልንና የይሁዳን መንግስትና ነገስታት ታሪክ ይተርካሉ ፀሐፊው በአርግጠኝነት አይታወቅም በታልሙድ ሰዎች እምነት ፀሐፊው ነቢዩ ኤርሚያስ ነው ሌሎች ደግሞ ንጉስ ስሉሞንና ንጉስ ሕዝቅያስ የንግስና ዘመናቸውን ታሪክ ሲፅፉ ነቢዩ ኢሳይያስና ኤርሚያስ የነበሩበትን ዘመን ታሪክ ጽፈዋል ይላሉ ይዘት ስለ ንጉስ ሰለሞንስለ ቤተመቅደስ መታነፅና አስራኤል ለሁለት መከፈላቸው ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ነገሰት ሁለተኛ የሁለቱን ነገስታት ታሪክ ከመጽሐፈ ነገስት ቀዳማዊ ተቀብሎ በመቀጠል ሁለቱን ነገስታት በጠላት ተከበው እስከ ተያዙበትና ሕዝቦቻቸውም ወደ ዴዋዌ እስከ ፄዱበት ያለውን ጊዜ ይገልፃል ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ዜና መዋዕል አንደኛ ዜና መዋዕል ማለት የአለት ጫና ማለት ነው የተፃፈበት ዘመን ከክል በፊት ዓመት አካባቢ በካህነ ዕዝራ ነው ምፅራፎች አሉትይዘቱ ከምዕራፍ የትውልድ ሀረግ ከአዳም እስከ አብርሃምከይስሐቅና ከያዕቆብ እስከ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ዘርዝራል ከምእራፍ የሳኦል መንግስት መውደቅና የቅዱስ ዳዊትን ንግስና ይገልፃል መጽሐፈ ዜና መዋዕል ሁለተኛ ምእራፎች አሉት የቤተመቅደሱ መሰራትና የነገስተ እስራኤልን ታሪክን ይገልፃል ፀሎተ ምናሴ ምናሴ ማለት ማስረሻ ማለት ነውምናሴ ከይሁዳ ነገስታት ቁጥር ያለ የንጉስ ሕዝቅያስ ልጅ ነውኛ ነገስት ይህም የፀሎት መጽሐፍ ምናሴ ባዕድ አምልኮን አየተከታተለ ከአሞራውያን ይልቅ ክፋትን ባደረገ ጊዜ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በአግዚአብሔር ቁጣ የአሶር ንጉስ ማርኮ ወደ ባቢሎን በወሰደው ጊዜ ምህረት አደረገለትና ምናሴም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰሕዝቡም እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ አዘዛቸው አንድ ምእራፍና አስራ ሦስት ቁጥሮች አሉት መጽሐፈ ዕዝራ ፅዝራ ማለት ረድኤት ማለት ነዉ ይዘቱ ከባቢሎን ምርኮ ስለመመለሳቸው ከ ዓመት በኃላስለመቅደስ መታነጽወደ አውነተኛ አምልኮ መመለሳቸውን ከአህዛብ ጋር በጋብቻ ስለተቀላቀሉና በዕዝራ ልመናና ልቅሶ ሚስቶቻቸውን እንደሚለዩ ቃል መግባታቸውን ይገልፃል ምእራፎች አሉት መጽሐፈ ነህምያ ነህምያ ማለት እግዚአብሔር አፅናኝአዳኝነማለት ነውነህምያ የፋርስ ንጉስ ለነበረው አርጤክስ ጠጅ አሳላፊ የነበረ አይሁዳዊ ልጅ ነውፀሐፊው ራሱ ነህምያ ነው ይዘቱም በ ቀናት ውስጥ ቅጽር በድጋሚ ማሳነጽን የጸሎትን ኃይልንና ነህምያ በማስተዳደር ዕዝራ በካህንነት ሕዝቡን በማህበራዊ ኑሮና በሃይማኖት ማገልገላቸውን ይገልጻል አስራሦስት ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ሱቱኤል ሰላትያልየፀሐፊውና የካህኑ ዕዝራ ድርብ ስም ነው ይዘቱም ካህኑ ዕዝራ በተማረበት ሀገር ስላያቸው ራዕዮችና ለጠየቀው ጥያቄ የተሰጠው መልስ አንዲሁም ካህኑ አዝራ አግዚአብሔርን በፀሎት ጠይቆ ልዩ መንፈሳዊ ፀጋና ዕውቀት ተሰጥቶታል ቀን ፆሞ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንደፃፈ ይገለፃልአስራ ሦስት ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ በኛ ዜና መዋዕል ከምዕራፍ በመጽሐፈ ዕዝራ ከምዕራፍ በመጽሐፈ ነህምያ ከምዕራፍ የተገለጸውን ታሪክ በድጋሚ በስፋት የሚገልጽ መጽሐፍ ነው ዘጠኝ ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ ጦቢት ጦቢት ስለተባለው ቅዱስ በንጉሱ ሰልምናሶር ዘመን ወደ አሶር ከተማረከ በኋላ አሱና ልጁ ጦብያ ተቸግረው ሳለ አግዚአብሔር በመልአኩ ሩፋኡል አማካኝነት ረድቶአቸው ከችግር ሁሉ እንደወጡ የሚተርክ መጽሐፍ ነው አስራ አራት ምአራፎች አሉት መጽሐፈ ዮዲት ዮዲት ማለት ሀያልተጋዳይ አሸናፊ ማለት ነው አስራ ስድስት ምዕራፎች አሉትጹንጉስ ናቡከደነጾር አስራኤላውያንን ለመውጋት የላከው ሆሉፎርኒስ የተባለው የጦር መሪ በአስራኤላዊቷ ዮዲት እጅ አንዴት እንደተገደለ የሚተርክ ነው መጽሐፈ አስቴር አስቴር በፋርስ ቋንቋ ኮከብ ማለት ነውመጽሐፉም በአርጤክስ ዘመነ መንግስት በምርኮኝነት ይኖሩ የነበሩ እስራኤላውያን ላይ የደረሰውን ስደትና ሞት ከአደጋ መዳናቸውን ይገልፃልበወቅቱ የእግዚአብሔርን ስም መጥራት ወይም ስለ ሃይማኖት አንስቶ መነጋገር ችግር ስለሚያስከትል በመጽሐፉ ውስጥ በአንድም ቦታ የእግዚአብሔር ስም አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት አልተጠቀሰምነገር ግን እግዚአብሔር ለሕዝብ ያደረገውን ጥበቃና ተራዳኢነት በሰፊው ይናገራልጸሐፊው የአስቴር አጎት መርዶክዮስ ነው አስር ምዕራፎች አሉት መጽሐፈ መቃብያን አንደኛ መጽሐፈ መቃብያን መቃብያን ማለት ጀግኖች ማለት ነው ምዕራፎች አሉት አሉት ሩፍ የመቃቢስ ዘብንያም ልጆች አብያሲላስናፈንቶ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ሃሦ ጽሩጻይደን የተባለው አመፀኛ ንጉሥ ስለሃይማኖታቸው ምክንያት እንዳሰቃያቸው የተቀበሉትን ሰማዕትነት ሃሦ ከብሊይ ኪዳን ታሪኮችንና ምሳሌዎችን እየጠቀሱ ሰለ ትንሳኤ ሙታን መናገራቸውን የሰው ልጅ የነፍስና የስጋ በረከትና ሕይወት ስለሚያገኝበት መንገድ የመከሩትን ይገልፃል መጽሐፈ መቃብያን ሁለተኛ ምዕራፎች አሉትአስራኤል በበደሉ ጊዜ የሞዓብ ሰዉ የሆነ መቃቢስን እንዳስነሳባቸውና አስራኤልን በሰይፍ ገድሎ ሲደነፉ አግዚአብሔር በመቃቢስ ስራ ተቆጥቶ ራይን የሚባል ነብይ ልቡን በንስሐ እንዲመለስ ቢነግረው ልብሱን አውልቆ በእግዚአብሔር ፊት ራሱን ቢያዋርድ እግዚአብሔር ስለልጆቹ ብሎ እንደማረው መጽሐፈ መቃብያን ሦስተኛ አስር ምእራፎች አሉት ይዘቱም የብሉይ ኪዳንን ታሪኮች እየጠቀሰ የዕድቅና የኩነኔን የትንሳኤ ሙታንንና ዲያብሎስ የሰው ልጆችን የሚያሰናክልባቸው መረቦች በዝርዝር የቀረቡበት ነው መጽሐፈ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ምዕራፎች ከአዳም ጀምሮ በ ዓም እስከተፈፀመው የኢየሩሳሌም ቤተመቅደስ መቃጠል ድረስ የአ ይሁድን ታሪክ የሚተርክ መጽሐፈ ኩፋሌ ኩፋሌ ማለት መክፈል ወይም መግመስ ማለት ነው ይህ መጽሐፍ ከመጀመሪያ የስነፍጥረት ቀን ጀምሮ አስራኤል ከግብፅ እስከወጡበት ያለው ጊዜና ታሪክ አስፋፍቶ የሚተርክ መጽሐፍ ነው ምፅራፎች ሲኖሩት ፀሐፊውም ነብዩ ሙሴ ነው መጽሐፈ ሄኖክ ከአዳም ጀምሮ ሲቆጠር ሰባተኛ ትውልድ በሆነው በፄኖክ የተጸፈ ባለ ምዕራፎ መጽሐፍ ነው ይዘት ስለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን መላዕክት ስለ ፀሀይና ጨረቃ ዑደት ስለ ዕፅዋት ስለ ጻድቃንና ኀጥአን በኖህ ዘመን ስለተፈፀመው ኀጢያትና ቅጣት የመዝሙርና የጥበብ መጻሕፍት መዝሙር ማለት ምስጋና ማለት ነው ። ስለ ወንጌል ክብር በአጠቃላይ ወንጌል በአርድእት ብቻ ተጽፎ ቢሆን ኖሮ ይህችማ ተርታ ሕግ ናት ደጊቱማ ሕግ ምሥጢረ ታምራትን በቤተ ኢያኢሮስ ምሥጢረ መንግስትን በደብረ ታቦር ምሥጢረ ምጽአትን በደብረዘይት ምሥጢረ ፀሎትን አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል መ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በጌቴ ሰማኒ ባዩ አዕማደ ምድር በተባሉ በልበ ሐዋርያት ቀርታለች በማለት አይሁዳ ደገኛይቱን ሕገ ወንጌል ከመቀበል በተከላከሉ ነበር የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል በኢኦተቤክ ትውፊት መሠረት የቅዱስ ማቴዎስ አባቱ ዲቁ እናቱ ክሩትያስ ይባላሉበማርቆስ ወንጌል ላይ የአባቱ ስም አልፍዮስ ተብሎ ተጠርቷልይህም የዲቁ ሌላ ስሙ ነውማር የመጀመሪያ ስሙ ሌዊ ስሆን ማቴዎስ የሚለውን ስም ያወጣላት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነውትርጉሙም የተመረጠ ማለት ነው ማቴዎስ የቀድሞ ሥራው ቀራጭነትግብር ሰብሳቢ ሲሆን ይሠራበት የነበረው ቦታ በገሊላ ባሕር አጠገብ በምትገኘው ደማቋ ቅፍረናሆም ከተማ ነበርከቅፍረናሆም ገብያ ወደ ገሊላ ባሕር ወደብ በሚወስደው ዐብይ መንገድ ዳር ሱቅ ከፍቶ ነጋዴዎችን ቀረጥ ያስከፍል ነበርጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ሲያስተምር ወደ ሚቀርጥበት ቦታ ጠጋ ብሎተከተለኝአለውቅዱስ ማቴዎስ አርሱ የሚሠራውን አስቦ ድሆችን በነዳ የሚያበላ ድውያንን በነዳ የሚፈውስ ሲያገኝ ተገርሞ ሥራውን እርግፍ አድርጎ ትቶ ተከተለውአባቶቻችን ቅዱስ ማቴዎስን የቁም ተስካሩን አውጥቶ ጌታን የተከተለ ሐዋርያ ይሉታልለሐዋርያነት በተመረጠ ጊዜ በቤቱ ደግሶ ጌታን ጋብዞ ድሆችን መጽውቶ ተከትሎታልናሃማቴ ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በፍልስጤምበፋርስበባቢሎንበኢትዮጵያ ወዘተ እንደሰበከ ይናገራልዩሐንስ አፈወርቅ በበዓለ ሃምሳ ድርሳኑ እንደገለጠው በቤተክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ መጀመሪያ ወንጌልን የሰበኩት በዓል ለማክበር ወደ ኢየሩሳሌም ሄድው በነበሩበት ወቅት በሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ስብከት ካመኑት ሺ ምመናን መካከል የነበሩት ኢትዮሏጴያውያን ሲሆኑም ቀጥሎም ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ነውየቅዱስ ማቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ከእነዚህ በኃላ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በኢትዮጵያ ወንጌልን እንዳስተማረ የቤተክርስትያን ታሪክ ፀሐፊ ሩፊኖስ አረጋግጧል የአገራችን ሊቃውንትም ያስተማረው በትግራይ በስተ ምእራብ በአድዋ አውራጃ ልዩ ስሙ ናዕዴር በተባለ ቦታ መሆኑን ይናገራሉአንድ በአረበኛ የተፃፈ ስንክሳር ደግሞ በ ገፅ ላይ ወንጌላዊው ማቴዎስ በትግራይ እንደሰበከ ይገልፃልሊቃውንተ ቤክ ለዚህ የሚያቀርቡት ማስረጋጃ የራሱን ወንጌል ነውቅዱስ ማቴዎስ ከሌሎች ወንጌላውያን ተለይቶ የሰብዓ ሰገልን የጥበብ ሰዎችንታሪክ የፃፈው በነዚህ አገሮች በማስተማሩ ነው ይላሉ «የተርሴስና የደሴቶች ነገስታት ስጦታን ያመጣሉዩየዓረብና የሳባ ነገስታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ» መዝሃ ባለው የቅዱስ ዳዊት መዝሙር የተርሴስና የደሴቶች የተባሉት ፋርስና ባቢሎን ሲሆን የዓረብና የሳባ የተባሉት ደግሞ የመንና ኢትዮጵያ ናቸው ከጥንት ዘመን ጀምሮ ከኢትዮጵያ በስተምሰራቅ ያለው ሀገር እስከ ሕንድ ድረስ ያለው ምስራቅ እየተባለ ይጠራል ማቴዎስ በወንጌሉ ከምስራቅ የመጡ ያለው በዚህ መሰረት ነውገድለ ሐዋርያት ቅዱስ ማቴዎስ በግሪክአጵሎን የተባለ ጣዖት ይመለክበት በነበረ ቦታአንዳስተማረ ይናገራልበመጨረሻ ግን በፍልስጥኤም ሲያስተምር የአይሁድና የአረማውያንንም ትምህርት በመቃወሙ ድውያንን ሲፈወስ አጋንንት ሲያወጣ በማየታቸው የሀገሩ ሰዎች ወደ እስር ቤት ጣሉት በአስር ላለ ያጋጠመውን እስረኛ ተአምር ነግሮ ከጌታው ቁጣ በማዳኑ ወሬው በሀገሩ ሁላ በማቴዎስ ላይ በመዳረሱ ይህንን የሠሙት መኳንንትም ማቴዎስን ለንጉሠ ከስሱትንጉሥጮሥም በመኳንንቱ ተመርቶ በማቴዎስ ላይ ሞትን ፈረደበትጥቅምት ቀን አንገቱን ተሰይፎ አረፈ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል በምራፎች ብዛት የመጀመሪያውን ወንጌል በመሆን ምዕራፎች ይዛልየተፃፈው ከቅዱስ ማርቆስ ወንጌል ቀጥሎ በ ዓም አካባቢ ነውየጌታችን ትምህርት በሰፊው በማቅረብ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛል በዚህም አቀራረቡ ከዮሐንስ ወንጌል ጋር ሲዛመድ ከሉቃስና ከማርቆስ ወንጌል ይለያልወንጌሉን የዛፈው ለአይሁድ በመሆኑ ከ በላይ የብሉይ ኪዳን ጥቅሶችን አቅርቧልበነዚህም የተናሳ ብሉይ ኪዳንን አብዝቶ በመጥቀስ ከሌሎች ወንጌሎች ይበልጣል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀድሞ በነብያት የተነገረለት መሲሕ መሆኑን ለማስረገጥ ሲል አንድን ታሪክ ከዳፈ በኋላ በነብይ የተጻፈው ብሎ ይመሰክራልሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ ትውፊትን በብዛት የተጠቀመ ሐዋርያ ነውማቴዎስ ወንጌልን ስላፃፈበት ቋንቋ ሦስት ዓይነት ሐሳብ ቀርቧል በዕብራይስጥየቤተክርስቲኒያችንን ሊቃውንት ጨምሮ ብዙ ምሁራን የተስማሙት ቅዱስ ማቴዮስ ወንጌሉን በዕብራይስጥ ቋንቋ ጻፈው በሚለው ሐሳብ ነው ነገር ግን እስካሁን ድረስ የዕብራይስጡ ዋና ቅጂ አልተገኘም በአረማይክፓፒየስ የተባለው አባት በ ኛው ከዘመን እንደገለጠው ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ አስቀድሞ የጌታችንን ትምህርቶች በአረማይክ ቋንቋ ሎጂያ በተባለ መጽሐፍ ሰብስቦት ነበርበሏእላም ወንጌሉን ሲጽፍ የጌታችንን ትምህርቶች የገለበጠው ከዚህ መጽሐፍ ነው በግሪክ አብዛኞቹ ጥንታውያን ቅጂዎች የሚገኙት በግሪክ ቋንቋ በመሆኑ በግሪክ ቋንቋ ተጻፈ የሚል ሀሳብ አለ የማቴዎስ ወንጌል ከማርቆስ ወንጌል ቀጥሎ በሁለተኛነት ተጽፎ አያለ የመጀመሪያውን ተርታ ያገኘበት ዋናው ምክንያት አቀራረቡ ለብሉይና ሐዲስ ኪዳን ድልድይ ስለሆነ ብሉይ ኪዳን ትንቢትና ምሳሌ በሐዲስ ኪዳን መፈጸሙን ስለሚያሳይ ነውወንጌሉን የጻፈው በምድረ ይሁዳ ተቀምጦ ሳለ በሶሪያ ውስጥ የሚገኝ በአንጾኪያ ከተማ ነው ሩሩ የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል የተጻፈበት ምክንያት ሀ አይሁድ ጌታን በድንግልና አልተወለደም ብለው ስለነበር አመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለአባት መወለዱን ለመመስከር ለ ኦሪትን ሊሽር መጣ ብለውት ስለነበር ኦሪትን ሊፈጽም አንጂ ሊሽር አለመምጣቱ ለማስረዳት ሐ ቡበሉይ ኪዳን ስለመሲሕ መምጣት የተነገሩ ትንቢቶች በኢየሱስ ክርስቶስ አንደተፈፀመ ለመግለፅ የቅዱስ ማርቆስ ወንጌል እናቱ ማርያም አባቱ አርስጦቡሎስ ይባላሉየማርቆስ እናት ማርያም ባውፍልያ ቤቷን ለክርስቲያኖች መሰብሰቢያነት የሰጠች ደግ ሴት ነበረችጌታም የመጀመሪያውን የሐዲስ ኪዳን ቁርባን ለሐዋርያት ያቆረባቸው በአርሷ ቤት ነውበበዓለ ዛምሳም መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረዳላቸው በእርሷ ቤት ተሰብስበው ሲጸልዩ ነው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ከታናጂ እስያ እስከ ሮም ድረስ ሰብከዋልበጫማ ሠፊው በአንያኖስ አማካኝነት የመጀመሪያው የግብፅ ቤተክርስቲያን በአናንያኖስ ቤት ተመሠረተችበግብዕ ቤተክርስትያን የትንሳኤን በዓል ሲያከብር ጣዖት አምላኪዎች ተነስተውበት በማሰርና በማንገላታት ከተሰቃየ በኋላ ሚያዚያ ቀን ዐረፈ የቅዱስ ማርቆስ ወንጌል ከወንጌላት ሁሉ አጭሩ ወንጌል ነው ምዕራፎችም ይዚልወንጌሉን የፃፈው ለሮማውያን በመሆኑ ከሌሎች ወንጌላውያን ቅዱስ ማቴዎስና ዩሐንስ የተለየ አገላለጥና አፃፃፍ ተጠቅሟልየተፃፈት ቋንቋ ሮማይስጥ ነውቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን የፃፈው ለአረማውያን በመሆኑ የአረማይክን ቃላትና የፅብራውያንን ባህል ሊያውቁት ስለማይችሉ ተርጉሞ አስቀምጦላቸዋልለምሳሌ ቦአኔርንጌስ የነጎድጓድ ልጆች አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ጣቢታ ቁሚ አንቺ ብላቴና ተነሽ ኤሎሄ ኤሉፄ ላማ ሰበቅታኒፁ አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ የማርቆስ ወንጌል የተጻፈበት ምክንያት ከሮማውያንከአሕዘብ ወገን ወደ ክርስትና ሃይማኖት ተመልሰው ላሉ በሃይማኖት በምግባር እንዲጸኑ ሮማውያንአሕዛብ አማልክቶቻቸውን የሚያውቋቸው በኃይላቸው ስለነበር በወንጌሉ የኢየሱስ ክርስቶስን ኃያልነት የአለም ሁሉ ንጉሥና ፈጣሪ መሆኑን አንዲሁም የማዳን ሥራውን በመግለጽ ያላመኑትን ለማሳመን ጽፏልአንዳንዴ የላቲንየአረማይክና ሌሎችንም ቃላት ትርጉማቸውን ለማስረዳት ጽፎላቸዋል » የቅዱስ ሉቃስ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሀገሩ አንጾኪያ ሲሆን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከተነሱት ቅዱሳን አንዱ ነው ቅዱስ ሉቃስ የሕክምና ሙያውን ዋላ ያጠናው ከአቴናና ከእስክንድሪያ ነውየሥነ ስዕል ችሎታም ነበረው ቅዱስ ሉቃስ በሰማዕትነት እአስካረፈበት ሰዓት ድረስ የቅዱስ ጳውሎስ ደቀመዝሙር በመሆን አገልግሉታል ሪኛጢሞ ቅዱስ ሉቃስ በድልማጥያ ወንጌልን በመስበክ ላይ እያለ አይሁድና ካህናተ ጣዖት ተባብረው ትምህርቱን በመቃወም ተነሱበት መስከረም ቀን ዓም አይሁዳና አረማውያን ጉባኤ አድርገው ነገር በመሥራት ለንጉስ ከሰሱት አሱን ለመያዝ ወታደሮች በተላኩበት ወቅት በመንፈስ ቅዱስ በመረዳቱ ያስተማራቸው የነበሩትን ምፅመናን ወደ የቤታቸው ላከና ወደ ባሕር ተጠግቶ አንድ ዓሣ አስጋሪ ጋር ቀርቦ ወንጌልን ካስተማረው በኃላ በመጨረሻ እንካ እነዚህ የሕያወትን መንገድ ይምሩፃልበማለት የያዛቸውን መጻሕፍት ሁሉ ሰጠውያም ዓሳ አስጋሪ አጅግ ተደስቶ አቃ በማያስቀምጥበት ቦታ በክብር አኑራቸው ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈበት ሀገር አካይያ ሲሆን የጻፈው በግሪክፅርዕ ቋንቋ ነውወንጌሉ የተጻፈው ከዓም ባለው ጊዜ ውስጥ ቅዱስ ጳውሎስ በእስር ላይ እያለ ባገኘው አረፍት ነውሉቃስ ወንጌል ምዕራፎች የያዘ መጽሐፍ ነው የሉቃስ ወንጌል የአሕዛብ ወንጌልስባኬ መንፈስ ቅዱስ ስባኬ ጸሎትወንጌለ አንስትእየተባለ ይጠራል የአሕዛብ ወንጌልእየተባለ የሚጠራው ወንጌሉ የተጸፈው ለአሕዛብ በመሆኑ ነው ሁ ስባኬ መንፈስ ቅዱስምክንያቱም ስለ መንፈስ ቅዱስ ደጋ ደጋግሞ ይናገራልና ስባኬ ጸሎትከሌሎች ወንጌላት በበለጠ ሁኔታ ደጋግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስና የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ጸሉትን ጽፏልና ወንጌለ አንሰትስለ አመቤታችን ድንግል ማርያም ስለ ቅድስት ኤልሳቤጥስለ ማርያም አንተ አእፍረ ወዘተ በስፋት ይናገራልና » የቅዱስ ሉቃስ ወንጌል የተጻፈበት ምክንያት ሃሦ በሮም ግዛት ውስጥ የሚኖሩትን ወደ ክርስትና የተመለሱትን ለማጽናት ያልተመለሱትን ደግሞ ለመመለስ ጽፎላቸዋል ለሮም ባለስልጣን ለቴዋፍሎስ ለጥያቄው መልስ ለመስጠት ጽፏል ከሁሉም መጻሕፍት በበለጠ ሁኔታ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ፍቅርና እናትነት ለመግለጥ ጽፏል የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቅዱስ ዮሐንስ ሀገሩ የገሊላ አውራጃ ሲሆን ከወንድሙ ከያዕቆብና ከ ሐዋርያት አንዱ የሆነ ከአባቱ ከዘብዴዋስ ጋር ዓሳ እያጠመደ ይኖር ነበርአናቱም ከ ቅዱሳት አንሰት አንዲ እንደሆነችና ማርያም እንደምትባል የቤተክርስትያን ትውፊት ይመሰክራልማቴ የዮሐንስ የተለያዩ ስሞችና ምክንያታቸው ፍቁረ እግዚእ በኑሮው ጌታን በመምሰል ጌታን ይወደው ስለነበር ነባቤ መለኮትታዖሎጎስ ነገረ መለኮትን ከሌሎች ወንጌላውያን በበለጠ አምልቶና አስፍቶ በጥልቀት በማስተማሩ ቦአጌርጌስወልደ ነጎድጓድ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት በመግለጡና ለጌታችን ባለው ቅንአት ባሳየው የሀይል ስራ ባለ ራእይአቡቀለምሲስበግሪክ ኃላፍያንንና መፃእያንን በራእይ በመግለፁ ቁጽረገጽፊቱ በሀዘን የጠቆረ በአለተ አርብ በእግረ መስቀል ተገኝቶ የጌታችንን መከራ መስቀል በማየቱ ከዚያች አለት ጀምሮ ፊቱ በሀዘን ጠቁሯል የዮሐንስ ወንጌል ከትረካ ይልቅ ነገረ መለኮታዊ ይዘት ስላለው ከሌሎቹ ወንጌላት ይለያልቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ከጳራቅሊጦስ በኃላ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በኢየሩሳሌም በአንጾኪያ በመቅዶንያ በእስያ ከተሞች በተለይም በኤፌሶን አስተምሯልቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ቱን መልእክታትና ራእዩን የፃፈ ሐዋርያ ነውቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው ከፍጥሞ ደሴት ሲመለስ በኤጅያን ባሕር ወደብ በ ዓም አካባቢ ነው የቅዱስ ዩሐንስ ወንጌል የተጻፈበት ምክንያት ከሶስቱ ወንጌላት የጎደለውን ለመሙላት ቅድመ ዓለም የነበረውን ሥጋን የተዋሐደውን ትንቢት የተነገረለት ሱባኤ የተቆጠረለት መሲሕ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ለመግለጥ ጽፏል የሰው ልጆች ሁሉ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ መሆኑን አምነው የዘለዓለም ሕይወት የሚያገኙ መሆኑን ጽፈፏል የሕይወት አወንጀራ የዓለም ብርዛን የበጎች በር መልካም አረኛ ትንሣኤና ሕይወት መንገድ አውነትና ሕይወት እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ የሚለው የኢየሱስ ክርስቶስ ማንነትና አምላክነት የሚገልጽ መሆኑን ለማስረዳት ጽፏል የታሪክ ክፍል የሐዋርያት ሥራ ሐዋርያት የሚለው ቃል የሐዋርያ ብዙ ቃል ሲሆን ሐዋርያ ሖረ ከሚለው የግአዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተጓዥ ማለት ነውሐዋርያት በአይሁዳውያን ዘንድ አላዋቂ ከሚባሉት የተመረጡ ናቸውበተልኳቸውም ድውይ ሲፈውሱ ሙት ሲያስነሱ ጋኔን ሲያወጡና የወንጌል ብርፃንነትን ሲመሰክሩ በህዝቡ ዘንድ ሞገስ አግኝተው ነበርየሐዋርያት ሥራ የሚለውን መጽሐፍ የፃፈው ቅዱስ ሉቃስ ነውበዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ሉቃስ ሐዋርያት ያደረጉትን ሥራ በሰፊው ፅፏልሥራውንም የሚሰራው መንፈስ ቅዱስ እንደሆነም ያስረዳል የቅዱስ ሉቃስ ዓይነተኛ ሐሳብ ሐዋርያት የኢየሱስ ክርስቶስን ትአዛዝ አየፈፀሙ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ወንጌል ለአለም አንዳዳረሱ ለማስረዳት ነውይህ መጽሐፍ እውነተኛ የክርስትና ጠባይን ስለሚገልፅ የተለየ የክርስትና መጽሐፍ ይባላልይኸውም ከመጀመሪያው አንስቶ እስከ ዕርገቱ ከፃፈ በኃላ ከጸራቅሊጦስ ጀምሮ የመጀመሪያውን የቤክ መሰረትና ህብረትየቤክንን ታምራት የመጀመሪያውን ጥምቀት የመጀመሪያውን የቤክ ስደት የመጀመሪያዎቹን ሰማዕታት የመጀመሪያውን ሐዋሪያዊ ጉዞ ከአይሁድ አለም ወጥቶ ወደ አሕዛብ መሄዱን አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የመጀመሪያዎቹን የዲያቆናት ምርጫና ሹመት የሚያስረዳ ከመሆኑም በላይ ቤክ ከምን ተነስታ ከምን እንደደረሰች የሚያሳይ ከፍተኛ ጠቃሚነት ያለው መጽሐፍ ነው ሩ የሐዋርያት ሥራ የተጻፈበት ምክንያት ሁ የቅድስት ቤክን አመሰራረትና ዕድገት ለመግለፅ ው የርደተ መንፈስቅዱስን ሁኔታ ለማስረዳት ሁ ቅዱሳን ሐዋርያት የኢየሱስ ክርስቶስን ትእዛዝ በመፈፀም ወንጌልን በአራቱም አቅጣጫ አንዳዳረሱ በመግለጥ የቅዱሳን ሐዋርያትን ሃይማኖትና ተግባርሥራ እንድንከተል እውነተኛ የክርስትና ጠባይን ለማሳወቅ ፅፏልየሐዋርያት ሥራ ምዕራፎች አሉት የሥርዓት ክፍል ሥርዓት የሚለው ቃል ሠርዓ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጓሜውም አሰራር ደንብ መርሐ ግብር ማለት ነውይህም ሥርዓት በክርስቶስ ደም የተመሰረተች ቤክ አምልኮቷን የምትፈፅምበት ሕዝበ እግዚአብሔርን የምትጠብቅበት ጸጋ የሚያሰጥ ቅዱስ ሥርዓት ነውየቤክ እምነቷ ብቻ ሳይሆን ሥርዓቷም እግዚአብሔር በቅዱሳት መጻሕፍት የገለጠው ቅዱስ ሥርአተ አምልኮ ነውየኢኦተቤክ የእለት ተእለት መንፈሳዊ አገልግሎት የምትፈፅምበት የሥርዓተ ቤክ መጻሕፍት አሏትአነዚህም መጻሕፍት ሐዋርያትና ሊቃውንት በየጊዜው ለቤክ መተዳደሪያ የወሰኑትና የደነገጉት ነው ሩ የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጮች « የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የሊቃውንት መጻሕፍት ቀኖናወ አበውየአበው ቀኖና የሥርዓት መጻሕፍት ወዘተ ናቸው ሥርዓትን መጠበቅና በሥርዓት መኖር አስፈላጊ እንደሆነና መንፈሳዊ ግዴታም እንዳለብን ዋነኛው የሥርዓት ምንጭ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናልለምሳሌ ምድርም ከሚቀመጡባት በታች ረክሳለች ሕጉን ተላልፈዋልና ሥርዓቱንም ለውጠዋልና ትኢሳ ከሥርዓትህ የሚርቁትን አጎሳቆልካቸው መዝ ያለሥርዓት የሚሔዱትን ገስዷቸው ኛተሰ ያለሥርዓት ከሚሔድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርክቶስ እንለምናችኃለን ኛተሰፅ በማለት የሥርዓትን አስፈላጊነትና ለሥርዓት ሊሰጥ የሚገባውን ክብር ገልጸውልናል የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መጻሕፍትን በሐዋርያት ቅዱስ ሲኖዶስ የተደነገጉ ናቸውሲኖዶስ ማለትም ስብሰባ ወይም ጉባኤ ማለት ነውይህም ሐዋርያት ከክርስቶስ ዕርገትና ርደተ መንፈስ ቅዱስ በኋላ ተሰብስበው የሰራቸውንና የደነገዓቸው ቀኖናዋች ናቸው መጻሕፍቱ የተጸፉበት ቋንቋ ስምንቱ የሥርዓት መጻሕፍት በመጀመሪያ የተፃፉበት እናት ቋንቋ ሱርስት የሶርያ ቋንቋ ነውአንዳንድ ሊቃውንት ደግሞ በለኛ ዘመን እነዚህ የሕግና የሥርዓት መጻሕፍት በየቋንቋው ለመተርጎም መነሻ ሆነው ያገለገሉት ሰነዶች በሙሉም ሆነ በከፊል ተቀርጸው የተገኙት በግሪኩ ቋንቋ ስለሆነ መጻሕፍቱ በመጀመሪያ የተጻፉት በግሪክ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ልሳነ ጽርዕ ነው ይላሉ ሱርስቱንና ግሪኩን መሠረት በማድረግ ወደ ላቲንሮማይስጥ ቅብጥሳደቅና ማምፊቲቅ ዐረብኛና ግዕዝ ቋንቋዎች በተለያዩ ተርጓሚያን ተተርጉማልፍትሐ ነገሥት መቅድም ቀ የሥርዓት ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት አከፋፈል ሐዋርያት የሠራቸው የሐዲስ ኪዳን የሥርዓት መጻሕፍት ስምንት ሲሆኑ እነርሱም በአጠቃላይ በሦስት ይከፈላሉክከፋፈላቸውም እንደሚከተለው ነው መጽሐፈ ዲዲስቅልያና አራቱ መጽሐፍተ ሲኖዶሳትትዕዛዝግፅውአብጥሊስና ሥርዓተ ጽዮንሐዋርያት በየጊዜው እየተሰበሰቡ ያዘጋጂቸው መጽሐፍት ናቸው ሁለቱ ኪዳናትመጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊና ካልእ ጌታችን ከትንሳኤው በኃላ የተናገራቸው ናቸው ሦ መጽሐፈ ቀለሜጦስ በሮም በኤኢስ ቆጸስነት ተሹሞ የነበረው የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀመዝሙር ቀሌሜንጦስ የዛፈው መጽሐፍ ነው ፊሊ በፍትሐ ነገሥት መጽሐፍ እንደተገለጠው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ቁጥር ሲሆኑ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ደግሞ ስምንቱን የትምህርትና የሥርዓት መጻሕፍትን ጨምሮ ናቸው መጽሐፈ ትእዛዝ ትአዛዝ ማለት በቁሙ ከስራ አስቀድሞ የሚሰጥ የሚጻፍ የሚነገር ሕግ ሥርዓት ወይም አድርግ አታድርግ የሚል ፈቃድና ደንብ ነውየመጽሐፈ ትአዛዝ ምልክቱ ወይም በአዕፅሮተ ቃል ልዩ መጠሪያው ረስጠብ በመባል ይታወቃልትአእዛዘ ሲኖዶስ ከ በላይ አንቀጾች ሲኖሩት እነዚህም ሁ ሊቃነ ጳጳሳት ሥርዓተ ሲመት አተገባበር ሁ ስለ መስዋአት አቀራረብ ሁ ስለ ንዋየ ቅድሳት ክብር ው ሰለ ሥርዓተ ጥምቀት ሁ ሰለ ሥጋ ወደሙ ክብር ወዘተየሚናገር መጽሐፍ ነው መጽሐፈ ግጽው ግጽው ማለት በቁሙ የታየ የተለጠ ጉልህ ማለት ነውሐዋርያት ለቀሌምንጦስ የሰጡት ሁለተኛ መጽሐፍ ነውየዚህ መጽሐፍ መሪ ምልክት ረስጠጅ በመባል እንደሚታወቅ ፍትሐ ነገስት ይናገራል መጽሐፉ የእግዚአብሔርን ሕልውና በማስረዳት ጀምሮ ሰለምሥጢረ ሥጋዌ ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም ሰለማስተማሩና ስለሠራቸው ሥራዎች ይናገራልመጽሐፉ ያህል አንቀጾች ያሉት ነው መጽሐፈ አብጥሊስ አብጥሊስ የመጽሐፍ ስም ሲሆን ትርጉሙ ቀኖና ማለት ነው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትንና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በአጠቃላይ መጻሕፍትን ሙሉ ዝርዝር ይዞ ይገኛል የአብጥሊስ መለያ መጠሪያው ወይም መሪ ምልክቱ ረስጠአረስጣ በመባል ይታወቃልመጽሐፉ የሚናገረው ስለ ኤሏስ ቆልሳት ሰለካህናት ሰለ ዲያቆናትና ምእመናን አጠቃላይ የስራ ድርሻና መንፈሳዊ ህይወትበስፋትም ሰለ ምስጢረ ንስሐ አሰጣጥና አተገባበር የሚያስረዳና የትምህርተ ሃይማኖትን የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነትና ምንነት የሚያትት ነው አንቀፆች አሉት አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መጽሐፈ ሥርዓተ ጽዮን ሥርዓተ ዮን ቀኖናተ ሐዋርያት ወይም ትምህርተ ሐዋርያት ከሚባሉት የሐዋርያት ሲኖዶስ መካከል አንዱ ነውሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ከመላካቸው በፊት በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው የሠሩትና የደነገጉት የቤተክርስትያን ሥርዓት ሕግና ትምህርት ነው የሥርዓተ ጽዮን መጽሐፍ መጀመሪያ የተጻፈበት ቋንቋ ጽርሕ ሲሆን በኋላ ግን ወደ አርበኞችና ወደ ግሪክ ቋንቋዎች ተተርጉሟልየሥርዓተ ጽዮን መሪ ምልክቱ «ዓይን ነውየሥርዓተ ጽዮን ቀኖና መጽሐፍ የሚገልጸው ስለ በዓለ አስተርአዮኤሏፋንያ ስለ እሁደ ሰንበት በዓል አከባበር ስለ ገሐድ ጾም ወዘተ ያትታልየቀኖናቱ ብዛትም የሚደርሱ ናቸው መጽሐፈ ኪዳን ኪዳን ማለት ውል ስምምነት የፍቅርና የአንድነት መሀላ ሰላማዊ ህግ ትምህርት ምስጋና ሁለቱን ወገን አግዚአብሔርንና ሰውንሰውንና ሰውን አንድ የሚያደርግ ነው። በዚህም ዘማዊና በኃጥያተኛ ትውልድ መካከል በእኔ በቃሌ የሚያፍር ሁሉ የሰው ልጅ ደግሞ በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ ያፍርበታልማር እያለ የተማረውን የወንጌሉን ቃል መሰረት በማድረግ ይህን መልእክት ከዝሙት ጠንቅ አንዲጠበቁ ጻፈላቸው ሃ የቆሮንቶስ ሰዎች ችግር በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አርስ በርስ መቀናናታቸው ነበር አኔስ ከማን አንሳለሁ አያሉ ሁሉም ትንቢት ተናጋሪ ሁሉም ተርጓሚዎች ሁሉም ሰባክያን ሁሉም በልሳን ተናጋሪዎች ስለሆኑ ሁሉም ራሳቸውን ከፍ በማድረጋቸው ጭቅጭቅ ነበርለዚህም ሁሉ ችግሮች ክርስቲያናዊ መልሶችን ጽፎ አዘጋጅቶ በጢሞቲዎስ በአስጢፋኖስ በፈርዶናጥስና በአካያቆስ አጅ ይህችን መልእክት በዓም ገደማ ላከላቸው ኛቆሮኛቆሮ ሃሦ በመጨረሻም ቅዱስ ጳውሎስ ጥያቄ አዘል ደብዳቤዎችን ጽፈውለት ነበርና የተለያዩ ችግሮቻቸውን በመጠየቅና መልስ በማዘጋጀት በሃይማኖት ይጸኑ በምግባርም ያድጉ ዘንድ ይህን መልእክት ጻፈላቸው ሁለተኛይቱ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን በሃይማኖት ልጁ በጢሞቴዎስ አጅ የመጀመሪያይቱን መልእክት ጽፎ ቢልክላቸውም ከኃጥያት ርቀው ንጽህና ጠብቀው መኖር አልተቻላቸውምክፉ ምግባራቸውንም ቀጠሉ ይህን በልጁ የላከውን መልእክት እንዳልተቀበሉትና ተግባራዊ አእንደማያደርጉትም በሰማ ጊዜ ከእንግዲህስ እኔ ብፄድ ይሻላል በማለት ወደ ቆሮንቶስ በፄደ ጊዜ አንዳልተቀበሉትና እአንዳሳዘኑት በዚህ መልእክት ገልዷልኛ ቆሮ የመጀመሪያ መልእክት ምን ያህል ተግባራዊ እንዳደረጉት ለመርዳት ቲቶን ላከኛ ቆሮ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋርም በመቄዶንያ ተገኝተው ሲጠይቀው የላካቸው መልእክት ብዙዎችን በክፉ ሥራቸው እንዲጸጸቱ ንስሐም አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እንዲገቡ አንዲያውም የአባቱን ሚስት ያገባ አንዲለይ አድርገዋል በማለት ደስ የሚያሰኝ ወሬ ነገረው ኛ ቆሮሃውፎ የቲቶን መልእክት ሲሰማ ቅዱስ ጳውሎስ አዚያው በመቄዶንያ እያለ ይህችን ሁለተይቱየተባለችውን መልእክት ባፈላቸው ቅዱስ ጳውሎስ ሁለተኛይቱን መልእክት የጻፈበት ምክንያት ሃሦ ንስሐ ገብተው በመመለሳቸው ለማመስገንና ለማጽናት ሃሦ ከአይሁድ ወገን የሆኑ ሓሳውያን መምህራን ወደ ወጋቸውና ልምዳቸው ለመለወጥ በመሞከራቸው ብዙዎች ተታለው በትምህርታቸውም ተስበው ስለነበር የሐሰተኞች መምህራን ትምህርት ወግና ስርዓት አንዳይከተሉ ለመምከር ፃፈላቸው ሃ ቀድሞ በፃፋቸው መልእክት ተደናግጠውበተግሣጻጽናበምክሩ ሐዘናቸውም ከልክ ያለፈ ነበርከልክ ያለፈ ሐዘናቸውንም ለማስታገስ የመልእክቱን የተገሳጹንና የምክሩን ጠቃሚነት አብራርቶ ጻፈላቸው ሦ ይህች በ ዓም አካባቢ በቲቶና ሉቃስ እጅ የተላከችበት ምክንያትም ስለ መልእክቷ እውነተኛነትና ስለቅዱስ ጳውሎስ ህይወት መመስከር የሚችሉ በመሆኑ ሲሆን በመጀመሪያዋ መልእክቱ ተግሳፅ ጠልተውት እንዳይቀሩ የመጀመሪያዋን መልእክትም እንዳያቃልሉ ሁለተኛይቱን የምስጋና ምክር አዘል አድርጎ ዕፎላቸዋል ሃሦ የእርሱም ሥልጣን ከእግዚአብሔር እንደሆነ ለማስረዳት አብራርቶ ጽፏል ወደ ገላትያ ሰዎች ይህች ገላትያ የተባለች ሀገር በታናጂ እስያ አጋርዮስና አሊያስ በተባሉ ሁለት ወንዞች መካከል የምትገኝ አውራጃ ስትሆን ዛሬ የቱርክ መናገሻ ከተማ ናትኔይህች የገላትያ ሰዎች መልእክት የተጻፈላቸው በ ዓም ሲሆን የተላከላቸውም በቲቶ እጅ ነውመልክቲቱም ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሁሉ የመጀመሪያዋ እንደሆነች ይነገራል ክርስትያኖች በአግዚአብሔር የባህርይ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ያገኘነውን ጸጋና ክብር ከኃጢያት ባርነት ነጻ እንዴት እንደወጣን የምትናገር የምታስረዳ በመሆኗ የነጻነት መልእክት በመባል ትጠራለች ይህን መልእክት የጻፈበት ምክንያት ሃ የአይሁድ መምህራን የሐሰት ትምህርት ወጋቸውን ሥርዓታቸውን የገላትያ ሰዎች አንዳይቀበሉ የተማሩትን የሐዋርያት ትምህርት እንዲጠብቁ እንዲጸኑ ሃሦ የአይሁድ መምህራን እንደ ሌሎች ሐዋርያት ጌታን አላየም ከቅዱሳን ሐዋርያትም አኩል አይቀጠርም ይሉት ስለነበር ይህንን የአርሱን ሐዋርያነትና ሥልጣኑን ያውቁ ዘንድ ሃሦ ከሐዋርያት እንጂ ከጌታ ስላልተማረ ክብሩ ያነሰ ሰው እያሉ አይሁድ ካህናት የገላትያን ሰዎች ያወናብዱ ያስጨንቁ ስለነበር ይህን ለማስረዳት ሃሦ መገረዝ ጽድቅን ያስገኛል ጳውሎስ ራሱ ተገርዚል እናንተን ግን ጽድቅ እንዳታገኙ መገረዝ አይጠቅምምይለችቷል እያሉ በዚህ ምክንያት ከአውነተኛዋ ፃዛይማኖት ሕግና ሥርዓት ያስወጧቸው ስለነበር ይህን ለማስረዳት ሃሦ ሐዋርያት ከአይሁድ ተፉቅረው ሕገ ኦሪትን ጠብቀው ሥርዓተ አይሁድን አክብረው በኢየሩሳሌም እየኖሩ እርሱ ግን እናንተን አላዋቂ አድርጎ የሐሰት ትምህርትን ያስተምራችኋል በማለት የሚናገሩትን ለማስተማር ጽፎላቸዋል ወደ ኤፌሶን ሰዎች ኤፌሶን በሮሜ መንግስት ሥር በታናሺ እስያ በምዕራብ በኩል በከይስተር ወንዝ አጠገብ ወይም በኤጅያን ባሕር ዳር የምትገኝ የልድያ የወደብ ከተማ ነበረችዛሬ በቱርክ ውስጥ የምትገኝ ሀገር ናትቅዱስ ጳውሎስ በ ዓም አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በኢየሩሳሌም ተይዞ ወደ ሮም በመሄድ በቁም አሥር በነበረ ጊዜ የኤፌሶን ሰዎች በእምነት በምግባር መጽናታቸውን በመስማቱ ይህችን መልእክት በደቀመዝሙሩ በቲኪቆስ እጅ ላካቸውቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ታስሮ ሳለ ከጻፋቸው አራት መልእክታት የመጀመሪያይቱ ናት አራቱም መልእክታት ወደ ኤፌሶን ወደ ፊልጵስዮስ ወደ ቆላስይና ወደ ፊልሞና ናቸው ን ሦ ሦ ርብ ርብ ርብ ርብ ወደ ኤፌሶን ሰዎች የጻፈበት ምክንያት በልዩ ልዩ የዓለም ሰዎች ምቀኝነትና ተንኮል ኤፌሶንን ከለቀቀ በኃላ በክርስትያኖች ላይ የተለያየ ስም ሲያወጡባቸው ይሰማ ነበርይህን በክርስቶስ የተሰጣቸውን አዲስ ስም አርሱም ክርስቲያን መባልን ታላቅ እንደሆነ ለማስረዳት ከተማዋ ታላቅ እንደመሆኗ መጠን የዝሙት ኃጥያት በጣም ተስፋፍቶ ነበርና የዝሙትን አስከፊነት ገለጸላቸው ባልና ሚስት የማይከባበሩ የጋብቻውንም ምስጢር ያልተረዱ ስለነበር ስለ ቅዱስ ጋብቻ ታላቅነት በክርስቶስና በቤተክርስቲያን አየመሰለ ጻፈላቸውኤፌ አይሁድና አሕዛብ መለያየትን ያበዙ ስለነበር በክርስቶስ አንድ ስለመሆናቸው በግልጽ ጽፎላቸዋል እንዲሁም የዲያብሎስን ተንኮል ባለማወቅ ተመልሰው ወደ ቀደም ግብራቸው እንዳይመለሱ የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ በመልበስ ዲያብሎስን ለመቃወም እንዲችሉ ጻፈላቸው ኤፌ ወደ ፊልጵስዮስ ሰዎች ፊልጵስዮስ በቀድሞ ዘመን አሊኒደስ ትባል ነበርየታላቁ እስክንድር አባት የመቄዶንያው ንጉስ ፊልጾስ ሁለተኛ ግዛቷን አስፋፍቶ በስሙ ፊልጵስዮስ ብሎ ሰይሟታልበ ዓም በሮም ታስሮ የጻፉት መልእክት ስለ ክርስቶስ አምላክነትና ሰው መሆን የምታስረዳ የሃይማኖት ትት ናትበተጨማሪም ክርስቶስ ከአብ ትክክል እንሆነበመስቀልም መሞቱን ትንሳኤውን ዕርገቱን መጥቶም ይህም ዓለም እንዲያሳልፍ ያለውን የዳግም ምድአቱን ነገር ትናገራለች ን ሦ ሦ መልእክቷ የተጻፈችበት ምክንያት ቅዱስ ጳውሎስ በሮም እስር ቤት በመሰቃይት ላይ መሆኑን የተረዱ የፊልጵስዮስ ምዕመናን ኦፍሮዲጡ በተባለ ወኪላቸው ያወጡትን አስትዋጽኦ አስይዘው ላኩትአርሱም በመከራው የማይዘነጉት በዛዘይማኖታቸው ጽኑ መሆናቸውን የሚያበረታታ ምስጋናና ምክርና ትምህርት ጻፈላቸው ፊልጵ ራሳቸውን ከፍ ከፍ ያደርጉ ይመኩም ስለነበር ለዚህ መልስ ጽፎላቸዋል እርሱ መታሰሩን የስሙ ቢጽ ሐሳውያን አኛም መምህራን ነን እያሉ በፊልጵስዮስ ክርስትያኖች ላይ ችግር ፈጥረውባቸው ስለነበር ለዚህ መልስ ጽፎላቸዋል በተጨማሪም በከተማዋ የነበሩት አይሁድ እኛ የአብርፃም ዘር ነን እያሉ በአህዛብ ላይ ስለተመኩባቸው ከንቱ የሆነ ትምክህታቸውን እኔም እኮ የቢንያም ዘር ነኝ በማለት ለሁሉም መልስ በመስጥት ጽፎላቸዋል ወደ ቆላስይስ ሰዎች የቆላስይስ መልእክት በ ዓም አካባቢ ተጽፎ በቲኪቆስና አጥሲሞስ እጅ ተላከች ን ሦ ሦ ሦ የተፃፈችብት ምክንያት ቢጽ ሐሳውያን የፍልስፍና መርዛቸውን እየረጩ መሆኑን ስለነገሩት ከዓለማውያን የቢጽ ሐሳውያን ፍልስፍና እንዲጠበቁ የአግዚአብሔር ማንነትና የጌታችን አዳኝነት በመግለጥ ጻፈላቸው የፊልሞና አገልጋይ አንሲሞስ የቆላስይስን የኑሮ ሁኔት ሰለነገረው ስለክርስቲያናዊ ኑሮ ሁኔታ አብራርቶ ጽፎላቸዋል የመጀመሪያይቱ ወደ ተስሎንቄ ሰዎች አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ተስሎንቄ ቀድሞ የመቄዶንያ ዋና ከተማ ስትሆን ዛሬ የግሪክ ሁለተኛ ከተማ ናትየቀድሞ ስሟ ቴረማ ይባል ነበር ትጉሙም «ፍል ውነ ማለት ነውአጠገባዋ ከነበረው ከፍል ውዛሃ የተወሰደ ይመስላል ቅዱስ ጳውሎስ ይህችን የመጀመሪያይቱን መልእክት የፃፋት በአቴና ውስጥ ነው ይህችንም መልእክት በ ዓም አካባቢ ጽፎ በስልዋኖስ በዕብራይስጥ ሲላስ በተባለው እና በጢሞቴዎስ በደቀመዝሙሩ እጅ ተላከላቸው ሩ መልእክቲቱ የተጻፈችበት ዐበይት ምክንያቶች ሃሦ ቀድሞ በብጥብጥ ምክንያት በድንገት ስለወጣ የተሰሎንቄ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት ጠላት ሰይጣን እንዳይቃወማቸው የእርሱም ድካማ ከንቱ እንዳይሆን የመንፈስ ቅዱስ ልጁን ጢሞቴዎስን አስይዞ ላከላቸው ሃሦ ምንም እንኳን መከራና ስደት ቢበዛባቸውም ከሃይማኖት ያለ መናወጣቸው እርስ በርስም በፍቅር መኖራቸንነ ቅዱስ ጳውሎስንም ያልረሱ መሆኑን ሌሎችም አስደሳች ዜናዎች ነግሮት ስለነበር በዚህ ምክንያት ጻፈላቸው ሃሦ የተሰሎንቄ ምዕመናን ክርክርን ያበዙ ስለነበር የተማሩትን ትምህርትና ሃይማኖት መጠበቅ አንጂ መከራከር እንዳይዙ ጻፈላቸው ሦ ሰው ሲሞትባቸው የቀቢጸ ተስፋን ነገር እያነሱ ከመጠን በላይ ያለቅሱ ያዝኑ ተስፋ ይቆርጡም ነበርና ይህን የአሕዛብ ሥራ ክርስትያን ሊሠራቸው እንዳማይገባ ጽፎላቸዋል ሃሦ እርስ በአርሳቸው የተፈቃቀሩ እየመሰላቸው አንዱ ሚስቱን ለሌላው በመስጠት የማይገባ ሥራ ይስሩ ስለነበር ጽፎላቸዋል በአጠቃላይ ፍፁማኑን የበለጠ ለማበረታት ተከፍሎ ልብ ያላቸውን ለማጽናት አንዳንዶችንም ለመገሰጽ ጽፎላቸዋል ሁለተኛይቱ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች በተሰሎንቄ የሚገኝ አይሁድ ራሱን ቅዱስ ጳውሎስን ሲያስጨንቁት እንደነበር የተሰሎንቄ ክርስቲያኖችም ያስጨንቋቸው ነበርና የሚያጽናና መልእክቱን በ ዓም በጢሞቴዎስና በሲላስ እጅ ልኮላቸዋል መልእክቲቱ የተጻፈችበት ምክንያት ሃሦ በነገረ ምጽአት ዙሪያ ብዙዎች መናፍቃን ያስቸገሯቸው ስለነበር በሰማ ጊዜ ይህችን መልእክት ጻፈላቸው ሃሦ የእርሱ መልእክት መሆኗን ስሙን በመጥቀስ እንዲቀበሉት አረጋግጦ ጽፎላቸዋል የመጀመሪያቱ ወደ ጢሞቴዎስ ጢሞቴዎስ የቅዱስ ጳውሎስ በሃይማኖትና በትምህርት የወለደው የበኩር ልጁ ነው ኛ ጢሞ ቅዱስ ጢሞቴዎስ በዕድሜ ወጣት ሲሆን በሃይማኖትና ምግባር የጸና መንፈሳዊ ቅናት ያለው ስለሆነ ቅዱስ ጳውሎስ ዲቁና ሰጠው ለቅዱስ ጳውሎስ የሥራ ረዳት የመከራ አጋር ሆኖት በሄደበት ሀገር አብሮ እየዞረ ሲቆይ በልዩ ልዩ ሀገሮችም ብዙ መልእክታትን ሳይደክም እየተላከ መንፈሳዊ ግዳጁን ፈጽሟልበመጨረሻም ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ቤተ ክርስትያን ጳጳስ አድርጎ ሹሞታልአንድ ጊዜ መታሰሩም ይናገራል ሐዋርያው ተልእኮውን እየፈጸመ እያለ በ ዓም አካባቢ በሰማዕታትነት አርፏል መልእክቲቱ የተጻፈችበት ምክንያት ሃሦ ከዚህ ቀድሞ ስለሥርዓተ ኖሉት ያልጻፈ ስለነበር በዚህ ምክንያት ጻፈለት ሃሦ በኤፌሶን ከተማና በአካባቢዋ ባሉት ሀገሮች የተስፋፋውን የግኖስቲኮችን ፍልስፍና አጠቃላይ ሁኔታ ክርስቲያናዊ ምላሽ በመሰጠት ጻፈለት ሃሦ ጢሞቴዎስን ለማበረታት ጽፎታል ሁለተኛይቱ ወደ ጢሞቴዎስ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ይህች መልእክት ለሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሁለተኛው አሥራቱ በሮም ወኃኒ ቤት እያለ የጻፋት የመሰናበቻ መልእክቱ ናትበዕድሜ የ አመት አዛውንት ሲሆን በጨለማ እስር ቤት ከአንድ ዓመት በላይ በመኖሩ ዓይኖቹ ደክመው ጊዜ ሞቱም ደርሶ አንደነበር ታውቋል መልእክቲቱን በ ዓም ጽፎ በአንክሮሎስ አጅ ልኮታልቅዱስ ጳውሎስ መልእክቱን ከጻፈ ከ ዓመት ከ ወር በኃላ በሰማዕትነት አርፏል መልእክቷ የተጻፈበት ምክንያት ሃሦ ለጢሞቴዎስ መሰነባበቻ መልእክት ጽፎለታል ሃ የመከረውን ምክር በድጋሚ ለማጽናት ጽፎለታል ሃሦ ከሐሰተኞች መምህራን ሕዝቡን እንዲጠብቅ ለማሳሰብና ለመሞከር ወደ ቲቶ ቲቶ በቅዱስ ጳውሎስ ስብከት ስላመነ በሃይማኖት የወለደው ልጁ ነውሐዋርያዊ ተልአኮውንና መንፈሳዊ ትጋቱን ተረድቶ ቅዱስ ጳውሎስ በሜድትራንያን ባሕር አጠገብ በምትገኝ ደሴት የቀርጤክስ ቤተ ክርስትያንን እንዲያስተዳድር በውስጧ አይሁድ ለሚኖሩባት ሀገር ሊቀጳጳስ አድርጎ ዲያቆናትንና ቀሳውስትን አንዲሾም እንዲያስተማር ሾሞታልቅዱስ ጳውሎስ መልእክቱን በ ዓም አካባቢ አርጣ በተባለው ደቀመዝሙር ጽፎታል ሩ መልእክቷ የተጻፈችበት ምክንያት ሃሦ የቀርጤክስ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ ቦታዎች ተቋቁመው በቁጥር በዝተው ቢገኙም በጣም ያልተደራጁ የወንጌል አገልግሎትም በአንዳንድ ቦታዎች ያልተዳረሰ መሆኑን ተረድቶ ነበር ወንጌል እንዲያስፋፉባቸው በአስተዳደርም በኩል መመሪያ በመስጠት ይህችን መልእክት ጻፈለት ሃሦ የቀርጤክስ ሰዎች ጠባያቸው የከፋ ስማቸው የጠፋ ነበርና መከራ እንዳይበዛበት መከራ ቢመጣበትም አንዲታገስ አስቀድሞ የሰዎቹን ጠባይ በማስገንዘብ አገልግሎቱም እንዳይጎዳ ጽፎታል ሃሦ በሀገሪቱ ብዙ ዓለማውያን ሰዎችና መናፍቃን ስለነበሩ ከእነርሱ እንዲርቅ ምእመናኑም ግንኙነት እንዳይኖራቸው በክፉ ትምህርታቸው አንዳይሳቡ ክህደታቸውን እየገለጠ ጽፎለታል ሃሦ በመጨረሻም በትምህርትና በግብረ ገብነት የታወቁትን በመምረጥ የቤተ ክርስትያን ጠባቂ የሚሆኑትን እንዲሾም አርሱም በትጋት እንዲያገለግልና እንዲጸና ይህችን መልእክት ጽፎለታል ወደ ፊልሞና ሀገሩ ቆላስዮስ የሆነው ፊልሞና ደግ ባለጸጋ ሲሆን ወደ ኤፌሶን ለሥራ በሄደ ጊዜ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ስብከት ሰምቶ ከእነቤተሰቡ አምኖ ተጠምቋልይህ ሰው አብርፃማዊ ሕይወት የነበረው ክርስትያኖችን በቤቱ እየተቀበለ ያበላ ያጠጣና ያሳድርም ነበር ቅዱስ ጳውሎስንም ይንከባከበው ለአገልግሎቱም የሚያስፈልገውን ያደርግ ነበር ከኤፌሶን ወደ ቆላስይስ ተመልሶ አናሲሞስ የተባለ አገልጋይ ነበረው ይህ አገልጋይ የሚጠብቃቸው የፊልሞና ከብቶች ሲጠፉበት አገሩን ቆላስይስን ትቶ ወደ ሮሜ ሲገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያ እስራቱ ላይ ሳለ አናሲሞስ የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርት ሰምቶ አምኖ ተጠመቀወደ ሮሜ ለምን እንደመጣም የደረሰበትን ሁኔታ ሲነግረው ይህች የማስታረቂያ መልእክት ለፊልሞናና ለሚስቱ ለአፋብያ እንዲሁም ለልጁ ለአክርጳስ ጽፎ በአናሲሞስ አጅ በ ዓም አካባቢ ላከላቸው መልእክቷን የጻፈበት ምክንያት አናሲሞስ ከፊልሞና ተጣልቶ በስደት ወደ ሮሜ እንዳይቀር ይህችን መልእክት አሲዞ ላከው አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄም ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፊልሞናና አፋብያ በአናሲሞስ መጥፋት እንዳያዝኑ መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን ከመወጣት ወደ ጊላ እናዳይሉ ከብቶችን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን የተጠመቁ ክርስትያን ወገኖችን ሁሉ እያስተማረ ከእነርሱ ጋር ሆኖ ያበረታቸው ዘንድ መልእክቱን በእጁ አስይዞ ልኮላቸዋል ስለጠፋው የፊልሞና ንብረትና በዚህ ምክንያት በክርስቲያኖች መካከል ልዩነት እንዳይኖር አጠቃላይ ሁኔታ ጽፎለታል ወደ ዕብራውያን ሰዎች ፅብራውያንከአብርፃም ቅድመ አያት በአባታቸው በዔቦር ዕብራውያን የተባሉ በኢየሩሳሌም ያሉ ምዕመናን እና አይሁድ ናቸውይህ ስም በሐዲስ ኪዳን ዘርን ወይም ዜግነትን ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ሕግ በመጠበቅ ስለሚገኝ ጽድቅ የሚያስረዳ ነው ይህች መልእክት የተጻፈችው ሮማውያን የኢየሩሳሌም ቤተመቅደስ ካፈረሱበት ከ ዓመት በፊት ነው መልእክቷም የሙሴን ሕግየቤተመቅደሱን አገልግሎት የነገስታቱንና የመሳፍንቱን ታሪክ ትውፊትና ሥርዓት ጠንቅቀው የሚያውቁ አይሁዶች በሚበዙባቸው ሀገሮች በኢየሩስአሌም በኢጣሊያና በእስክንድሪያ ለሚኖሩ ክርስቲያኖች ከአይሁድነት ወደ ክርስትና ለተመለሱ የተጻፈች ናት የዚህች መልእክት ፀሐፊ ማነው። የሚለው ጥያቄ ለሔሬኔዎስ ለዚፖሊተስ ለጠርጡለስና የማርቲን ሉተርን ሀሳብ መሰረት ላደረጉ ለብዙዎች ነገረ መለኮት ምሁራን አጠጠያያቂ ሆኖ ቆይቷል ብዙዎች ይህ መልእክት የቅዱስ ጳውሎስ አይደለም ለማለት የሚገልዷቸው ምክንያቶች ሃ አጻጻፉ ከቅዱስ ጳውሎስ የአጻጻፍና ባሕርይ የተለየ ነው ሃሦ መልእክቱ የተላከው ለዕብራውያን አንደመሆኑ መዘጋጀት የነበረበት በዕብራይስጥ ቋንቋ ነበር ነገር ግን መልእክቱ የተዘጋጀው በግሪክ ቋንቋ ነው ሦ በመልእክቱ መጀመሪያ ላይ በሌሎች መልእክቶች የተለመደውን የሰላምታ አሰጣጥ አልተጠቀመም ሃ የእርሱ ቢሆን ስሙን ሊገልጽ ይችል ነበርየሚሉ ናቸው ከ ዓም የነበረው አርጌንስ ከ ዓም የነበረው ቀሌምንጦስ ዘእስክንድሪያ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ አትናቲዮስና ሌሎችም የቤተ ክርስትያንን ትውፊት መሠረት በማድረግ ቅዱስ ጳውሎስ አንደጸፈው ተናግረዋል ታላቁ የቤተ ክርስትያን ታሪክ ፀሐፊ ቅዱስ አውሳብዮስም በ ዓም የዕብራውያን መልእክትን ከቅዱስ ጳውሎስ መጽሐፍ ዝርዝር ውስጥ አካቶታልበዓም በቅርጠግናከ ላይ የተደረገ የቤተ ክርስትያን ጉባኤም የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት በቀኖና ደንግጎ አስቀምጦታል እነዚህ የቤተ ክርስትያን ሊቃውንት መልእክቱ የቅዱስ ጳውሎስ ነው ሲሉ በመረጃና ከላይ ያልቀበሉትን ሰዎች ጥያቄ መልስ አንደሚከተለው በመስጠት ነው ሃ የአጻጻፉ ባሕሪ የተለየው ቅዱስ ጳውሎስ ጥልቅ የኦሪት አውቀት ስላለው መልእክቱ ተቀባይነት እንዲኖረው ከሌሎቹ መልእክታት ለየት አድርጎታል ሦ ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ከጻፈው በፃላ ወደ ግሪክ ቋንቋ የተረጎመው ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ነው ሃ ቅዱስ ጳውሎስ ከሌሎቹ መልእክቶቹ ሁሉ በእርሱ እንደተጻፈ ማረጋገጫ አድርጎ የተናገረው የሰላምታ ቃል በዚሁ መልእክትም ተገላጽዋልዕብ ሃሦ ጥልቅ ዕውቀት ያለው ለአጻጻፍና ለአቀራረቡ ምንም አይነት ችግር የሌለበት ቅዱስ ጳውሎስ የፅብራውያን ሰዎች ከእግዚአብሔር ተለይተው እንዳይቀሩ ሕጉን ሥርዓቱንና ትውፊቱን እንዲጠብቁ በሚገባቸው ኦሪታዊ አገላለጽ እንዲመልሱ ለማድረግ የጻፈላቸው በመሆኑ ነው አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሦ ስሙን በመልእክቱ ውስጥ ያልገለጸበት ምክንያት አስቀድሞ የእርሱ ተማሪና ለወጋቸው ቀናተኛ ስለነበር ስሙን ቢያዩ ኖሮ ለበቀል ስሜት መልእክቱን ስለማይቀበሉት ነው ዘመኑ አይሁድ በሮማውያን ላይ ለማመጽ የተዘጋጁበት ጊዜ ስለነበር በሮም መንግስት የቁም እስረኛ ላይ በመሆኑ በግዞትና በጦርነት ጊዜ መተማመን ስለማይኖር ሮማውያን ካወቁ ወገኖቹን ያነሳሳብናል ብለው እንዳይቃወሙትና ምክንያት አግኝተው እስራቱን ወደ ፖለቲካ እንዳያዞሩበት ቀድሞውንም ያሳሰሩት እነርሱ ናቸውና ገና ስሙን ሲያዩ ኦሪት አለፈች ሊለን ይሆናል ብለው ከማንበብ አእንዳይከለከሉነጻ ሆነው መልእክቱን አንብበው ወደ ክርስትና ያለመጡትን ለማምጣት የመጡትን ደግሞ ለማጽናት ጽፎላቸዋል በመጨረሻም ወንድማችን ጢሞቴዎስ እንዲፈታ ዕወቁ ከኢጣልያ የሆኑት ሰላምታ ያቀርቡላቸዋል ፅብ የሚሉት መረጃዎች ፀሐፊው ከጢሞቴዎስ ጋር ያለውን ቅርብ ግንኙነትና በኢጣልያ በአገልግሎት እያለ የጻፈው መሆኑን ያስረዳል በማለት መሠረታውያን የቤተ ክርስትያን አባቶች በእነዚህና በመሳሰሉት መረጃዎች መስክረዋል ይህች መልእክት በመጀመሪያዋ እስራቱ በሮሜ እያለ በዓም አካባቢ ጽፎ በጢሞቴዎስ እጅ ልኮላቸዋል መልእክቲቱ የተጻፈችበት ምክንያት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መምጣት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውፃ ፈሳሽ አለመሆኑን ለማስረዳት ኢየሱስ ክርስቶስ ከነቢያት ከመላአክት አንዲሁም በክህነቱ በመሥዋዕቱ በሕጉ በኪዳኑ በሚያወርሰን መካነ ዕረፍት ወዘተየሚበልጥ መሆኑን ለማስረዳት በወቅቱ ክርስትና በተቀበሉ ግሪክኛ ተናጋሪ በነበሩ አይሁድ ላይ ስደትና መከራ ስለጸናባቸው በእምነታቸው ጸንተው መከራውን ታግሰው የጽድቅ አክሊል ተካፋዮች አንዲሆኑ ለመምከርና ለማጽናት በኦሪት ሕግ ብቻ ይኖሩ የነበሩ ወደ ክርስትና ሄሃይማኖት ያልተመለሱ ብዙ አይሁዳውያን መልእክቱን አንብበው ይመልሱ ዘንድ ጽፎላቸዋል ሰባቱ መልእክታት የቅዱስ ጴጥሮስ ኛ እና ኛ የያዕቆብ የዮሐንስ እና የይሁዳ እነዚህ ሰባቱ መልእክታት በመባል ይታወቃሉአነዚህም ሰባቱ መልእክታት የተባሉበትም ምክንያት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተ ክርስትያን ብቻ ስላልተጻፉ ማለትም ለአብያተ ክርስትያናት ስብስቦች የተላኩ መልእክታት መሆናቸው ነው መልእክታቱም ሲላኩ ከአንድ ቤተ ክርስትያን ይደርስና ለምእመናኑ ከተነበበና ከተረዱ በኋላ ሀብት ያላቸው አጽፈው ቅጅ ያስቀሩና ዋናውን ላዋሳቸው ወይም ለሌላ ቤተ ክርስትያን እንዲደርስ በማሰብ ያስተላልፉና ይጠቀሙበት ነበር የቅዱስ ጴጥሮስ መልእክታት የመጀመሪያይቱ የቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያይቱን መልእክት የጻፈው በመከራና በስደት ጊዜ ነውመልእክቷ የተጻፈችው በቅዱስ ጴጥሮስ ነጋሪነት በስልዋኖስ እጅ ሮም ባቢሎን ውስጥ በ ዓም አካባቢ እንደሆነ ይነገራል ዒ መልእክቷ የተጻፈችበት ምክንያት መልእክቱ ያለምንም ምክንያት ሊደርስ ከሚችል ፈተናና ችግር ጌታችን እንደታገሰ እንዲታገሱ ለመምከር በንጹህ ደም የተዋጁ ስለሆኑ በንጽህና አንዲኖሩ በክርስቶስ ላይ እንደተመሰረቱ ካህናትና ቤተመቅደስ እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሃ የዘለአለም ህይወት እንዳላቸው ያውቁ ዘንድ ሦ ከሥጋ ምኛት አንዲጠበቁ ሃሦ ከምእመናን ሁሉ ጋር ባላቸው የሚገባ ግንኙነት ትሁታን እንዲሆኑ ጽፎላቸዋል ሁለተኛይቱ የቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ይህች መልእክት በቅዱስ ጴጥሮስ ተጽፋለችየጻፈላቸውም በኒሮን አዋጅ ተይዞ በአሥራት እያለ በ ዓም አካባቢ ነው መልእክቲቱ የተጻፈችበት ምክንያት ሃሦ ሐሰተኞች ነቢያትና ሐሰተኞች መምህራን ለዚህ ዓለም ሠራኢ መጋቢ የለውም ትንሣኤ ሙታን የለውም ኅልፈተ ሰማይ ወምድር የሌም አንድ ጊዜ ካመኑ ምግባር አይጠቅምም አያሉ በክህደት ትምህርታቸው ያላመኑትን ምግባር ያላቸውን ክርስትያኖች ያውኳቸው ስለነበር ለእነዚህ ሰዎችና ለጥያቄዎቻቸው መልስ በመስጣት ይህን መልእክት ጽፎላቸዋል ሃ የሚገባውን የክርስትያን አኗኗር ሕይወትና መሠረቱ የቤተ ክርስትያን መሥራች የቅዱሳን ሁሉ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ያወቁና በክርስትና እምነት ይጸኑ ዘንድ ጽፎላቸዋል ሃሦ ያመኑት ሰዎች ይህን መልእክት ተረድተው በሃይማኖት በምግባር አንዲኖሩ ሌሎች ምግባር ሃይማኖት የሌላቸው አንብበው ተረድተው ይመለሱ ዘንድ ይህን መልእክት ጽፏል የመጀመሪያው የቅዱስ ዮሐንስ መልእክት ቅዱስ ዮሐንስ በኤፌሶን ሳለ በ ዓም አካባቢ እንደጻፈው ይገራል መልእክቷ የተጻፈችበት ምክንያት ሦ መናፍቃን ትንሳኤ ሙታን የለም ከጥምቀት በጊላ የምንሰራው ኃጢአት አይደለም ከዚህ የተለየ ምግባርም አያስፈልግም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ አልተገለጠም » ግኖስቲኮች አዋቂዎች ነን በማለት ያለ አነርሱ አውነተኛ ክርስትያን እንደሌለ በማሰብ ለእኛ የመጨረሻ እውቀት ተገልጦልናልስለዚህ ያለ ሕግ መኖር እንችላለን የሚሉትን የተለያዩ ጥያቄዎቻቸውን አንድ በአንድ በመመለስና በማስረዳት ጽፎላቸዋል ይኸውም ስለትንሣኤ ሙታን መኖርና የጌታችንን መለኮታዊ ክብርና ምሥጢረ ስጋዌውን በማረጋገጥ ማንኛውም ክርስትያን የእግዚአብሔርን ትአዛዛት መጠበቅ እንዳለበትና ድኅነት የሚገኘውም ለእርሱ አምልኮ በማቀረብ እንደሆነ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ስለመውደዱና እርስ በርስ መዋደድ ዓይነተኛ የክርስትና ምልክት እንደሆነ ኃጥያቱን የተናዘዘ የእግዚአብሔርን ምህረት የሚያገኝ እንደሆነ የሐዋርያት ትምህርት አጽንተው መያዝ ያለባቸው ስለመሆኑ ስለ አውቀት ምንነት አጠቃላይ ሁኖታ አስረድቶ ከፍጥሞ ደሴት ግዞቱ ሲወጣ ለመናፍቃን የክህደት ትምህርት መልስ ይሆን ዘንድ ጽፎላቸዋል አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄጅ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሁለተኛይቱ የቅዱስ ዮሐንስ መልእክት ይህች መልእክት ሐዋርያው ዮሐንስን በኤፌሶን ከተማ በ ዓም አካባቢ ለአንዲት ሴትና ቤተሰቧቿ ከመናፍቃን ትምህርት እንድትጠበቅ የጻፈላት መልእክት ነው ይህች ሴት በኤጅያን ደሴቶች አንዱ ቀለብ እየተሰፈረላት የነገስታቱን ልጆች የምታሳድግ ሮምና የተባለች ሞግዚት ነበረች ዮሐንስና ደቀመዝሙሩ አብሮኮሮስ በዚህች ደሴት ለማስተማር ፈልገው የሮምና የአባቷ ባሮች ነበርን ለብዙ ዘመናት ጠፍተን ስንኖር አሁን መጣን አያሉ በደሴቷ አስወሩከንቱ ውዳሴ የሚያጠቃት ሴት ነበረችና ወደ ቤቷ ወስዳ ቅዱስ ዮሐንስን እንጨት ፈላጭ ደቀመዝሙሩ አብርኮሮስን ደግሞ ውፃ ቀጅ አደረገቻቸው አንድ ቀን ከምታሳድጋው አንዱን ይዛ ወደ ቤተ ጣዖት ስትገባ ዮሐንስና አብሮኮሮስ ተከትለዋት ገቡያን ጊዜ በቤተ ጣዖቱ ያደረው ሰይጣን እነ ቅዱስ ዮሐንስን ሲያይ የቤቱን እቃ በማተረማመስ ወጣበዚህ መካከል አስከትላው የነበረው ልጅ በድንጋጤ ሞተ ያን ጊዜ የእናንተ መምጣት ነው ለዚህ ሁሉ ያበቃኝ ብላ ደበደበቻቸው ቅዱስ ዮሐንስም አስነሱልኛ አትይምን። ከመቼ ወዲህ ነው ደግሞ የሞተ ሰው የሚነሳው ብላ የበለጠ ተቆጣች ያን ጊዜ አነ ቅዱስ ዮሐንስ ጸልየው አስነሱላትበዚህ ተአምር ምክንያት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምና ተጠምቃለችወድያውኑም በቤቷ የምእመናን ጉባኤ ተጀምሮ አርሷንም ለዚህ እመ መፄጌት አድርገው ሾመዋታልቅዱስ ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት በታሰረ ጊዜ በመናፍቃን የሐሰት ትምህርት የተነሳ በቤቷ ያለው የክርስቲያኖች ጉባኤ መከፋፈል ደረሰበት ጠብ ክርክር ተነሳ ይህን የሰማው ቅዱስ ዮሐንስም የድሮ ኑሮዋን ወይም ህይወቷን አስታውሳ የአሁኑን መከራ እንድትረሳ እመመኔትነቷም ለትእቢት እንዳይሆንባት ታላቁ ሐዋርያ በድሮ ስሟ አመቤቴ እያለ በትህትና በመጥራት አጠቃላይ ሁኔታውን ጽፎላታል መልእክቲቱ የተጻፈችበት ምክንያት ሦ በመጀመሪያቱ የዮሐንስ መልእክት ላይ የተገለጹት መናፍቃን ምእመናንን ለማስካድ ይጣደፉ ስለነበር የሐስት ትምህርታቸውን በመቃወም እውነተኛዋን የክርስትና ትምህርት እንዲያጸኑ ነው ሶስተኛይቱ የዮሐንስ መልእክት መልእክቱ የተላከችው ጋይዮስ ለተባለ ሰው ነውበሐዲስ ኪዳን ውስጥ ጋይዮስ በመባል የሚጣወቁ ሰዎች ሲኖሩ ይህችን መልእክት ለማድረስ የታደለው በሮሜ ለተጠቀሰውና በአብርሃማዊ አንግዳ አቀባበል በረከት ለደረሰው ጋይዮስ ነው መልእክቱን የጻፈበት ምክንያት ሃሦ ጉባኤው ይሰፋ ዘንድ እንግዳ እየተቀበለ የሚያገለግለውን ጋይዮስን ለማመመስገን ሃሦ በቤተክርስትያን ውስጥ መለያየት እንዳይኖር ለመምከር ሃሦ ዲዮጥራጢስን ለመገሰጽ ፅፏል የሐዋርያው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት በሐዲስ ኪዳን ያፅቆብ በመባል የሚጠሩ ቅዱሳን አባቶች አሉ ያዕቀብ ወልደ ዘብዴዎስ የዮሐንስ ወንድምና ከሚስጥር ሐዋርያ አንዱ የይሁዳሐዋርያው አባት ይህም ታዴዎስ ወይም ልብድዮስ እየተባለ የሚጠራው የኢየሩሳሌም ቤተ ክርስትያን መሪ የጌታ ወንድም የተባለውና ይህን መልእክት የጻፈው ነው መልእክቱ የተጻፈበት ምክንያት አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሃሦ መልእክቱ የተላከላቸው ሰዎች ተበትነው ይኖሩ ለነበሩና ክርስትናን ለተቀበሉ አይሁድ ተበታትነው ስለነበር በያሉበት ለማበረታታትና ለማጽናናት ሃሦ ስደትና መከራ ይበዛባቸው ስለነበር በደረሰባቸው መከራና ስደት ተስፋ አንዳይቆርጡና ዋጋ እንደሚያገኙ አንዲሁም ክብር አንዳለው ለመምከር ሃ በቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት የተጻፈውን የነገረ ሃይማኖት ትምህርት አእንዲያጸኑና በተጨማሪም ደግሞ ምግባር በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳት የሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ መልእክት በሐዲስ ኪዳን ውስጥ የይሁዳ ተብለው የሚጠሩ ብዙ ሰዎች አሉየዚህ መልእክት ጸሐፊ የጌታ ወንድሞች ከተባሉተ አንዱ ነውየያፅቆብን መልእክት የጻፈው የያዕቆብ ወንድም የተባለው የዮሱፍ ልጅ ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ ነውሁለቱም ወንድማማቾች ከጌታ ትንሣኤ በኃላ ያመኑትና የሰበኩ ናቸው መልእክቱ የተጻፈበት ምክንያት ሦ በሐሰተኞች መምህራን ትምህርት ችግር የደረሰባቸው ክርስቲያኖች ከክህደት ትምህርት ርቀው ከቅዱሳን ሐዋርያት የተረከቡትን የቀና የክርስትና እምነት አጽንተው እንዲይዙ ለማድረግ ሃሦ ተመክረው ያልሰሙ ሰዎች እንደሚቀጡ የሚመለሱት ደግሞ እንደሚድኑ ለማሳወቅ ተጽፏል የቅዱስ ዮሐንስ ራእይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልአኩ አማካኝነት በራፅይ በገለጸለት መሠረት የዚህ መጽሐፍ ፀሐፊ ወንጌላዊው ዮሐንስ ነውሮዮሐንስ ለቄሳር ድምጥያኖስ ሐውልት የሚሰግዱትን በመቃወም በንጉሱ ትእዛዝ ወደ ፍጥሞ ደሴት ተጓዘ የቅዱስ ዮሐንስ ራእይ በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ በመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ዘንድ ደግሞ የሐዲስ ኪዳን የትንቢት መጽሐፍ በመባል ይታወቃልፍዑፁምነትን ለመግለጽ በሰባቱ የእስያ አውራጃ ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ቢልም ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የተላከ መጽሐፍ መሆኑ ይታመናልየዮሐንስ ራእይ የትንቢት መጽሐፍ ሲሆን ከስነ ጽሑፍ ሁኔታ አንጻር በአጠቃላይ ሦስት አይነት አቀራረብ አለው ሦ የጽሑፉ መግቢያና መደምደሚያ በማሳሰቢያ መልክ የቀረበ ነው ሃ በተለይ ምዕራፍ ሁለትና ሦስት ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት አለቃዎች የተላኩና በደብዳቤ መልኩ የቀረቡ ናቸው ሃሦ ሌላው አብዛኛው ክፍል በራዕይ መልክ የቀረበ ሲሆን በብሉይ ኪዳን የመቅደስ ሥርዓትና ንዋየ ቅድሳት ወዘተ ምሳሌነት ለዮሐንስ የታየ ነው ቅዱስ ዮሐንስ ራዕዩን የጻፈበት ምክንያት ብዙዎች የፋርስ ነገስታት የሰሩት የአርጤምስ ጣዖት በማምለካቸው ሁሉንም ሊያስተምር መላእክትአለቃዎች ተብለው ለተጠሩ በታና እስያ ለሾማቸው ሰባት ሊቃነ ጳጳሳት በቤተ ክርስትያን መልካም አስተዳደርና ሕይወት ዙሪያ ለመምከር የክርስቲያኖችን ሰማያዊ ሕይወትና የመላእክትን የጻድቃንን የሰማዕታትን ክብር ለማሳየት ጽፏል የጥጦስን የሐሳዊ መሲህን የምጽአትንና የመንግስተ ሰማያትን ነገር የገለጸለት አግዚአብሔር ጻፍ ብሎት ለማስረዳት ጽፏል ፈሓ አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ጄጄ ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት አአሣቴዩ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል ምንጭዉሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት።