Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convertir en PDF
  • Liste de lecture
  • Abrégé
  • Livre audio
  • Chercher
  • Télécharger
  • myzon
  • S'identifier
  • registre
English  አማርኛ  Français  العربية
Livre du jour

የሀሰተኛ ሰነድ.pdf


  • word cloud

የሀሰተኛ ሰነድ.pdf
  • Extraction Summary

ከዚህ ተልእኮ መሳካት አንጻር በየበጀት አመቱ የሚሰሩ የንቃተ ህግ ትምህርት እንዲሰጥባቸው ከተለዩ የህግ አርስተ ጉዳዮች መካከልም ይሄው ሀሰተኛ ሰነድ መፍጠርም ሆነ መገልገል የሚያስከትለውን ተጠያቂነት ተብራርቷል።

  • Cosine Similarity

በዚሁም መሰረት ይህ የስልጠና ሰነድ ማህበረሰቡን ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልገል የሚያስከትለውን የህግ ተጠያቂነት በመዳሰስ ማህበረሰቡን በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ለማሰልጠን ታስቦ የተዘጋጀ ሰነድ ነው የስልጠና ሰነዱ በዋናነት በሁለት ክፍል የተዋቀረ ነው በክፍል አንድ ስለ ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልገል የሚስከትለው የህግ ተጠያቂነት ጠቅላላ ግንዛቤን ለመፍጠር በማሰብ ስለ ሀሰተኛ ሰነድ ምንነት የምንዳስስ ይሆናል። ይህ አጭር የስልጠና ሰነድ የተዘጋጀው ይሄንኑ ዋና አለማ ለማሳካት በማሰብ ነው በዚህም መሰረት የህ የስልጠና ሰነድ የሚከተሉት ዝር ዝር አላማዎች አሉት ሁ የማህበረሰቡን ንቃተ ህግ በማሳደግ ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልገል ወንጀልን መከላከል ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልገል ወንጀልን ተፈጽሞ ሲገኝ ማህበረሰቡ ለፍትህ አካላት ተገቢውን ድጋፍ አድርጎ ወንጀለኞች አንዲጠየቁ የበኩሉን ድርሻ አንዲወጣ ማስቻል እና ሁ ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልገል ወንጀልን የሚከላከሉ ባለድርሻ አካላት በጉዳዩ ላይ የጋራ ግንዛቤ ኖሯቸው በትብብር እና በቅንጅት እንዲሰሩ ማድረግ ናቸው ክፍል አንድ ሀሰተኛ ሰነድና ማስረጃ በጠቅላላው በፍትህ ስርአት ወስጥ ማስረጃ የጀርባ አጥንት ነው በዚህም ፍትሀብሄራዊ ክርክር ውስጥ አከራካሪ የሆኑ ፍሬ ነገሮችን እውነትነት ለማረጋገጥ ወይም በወንጀል ምርምራ እና ክርክር ውስጥ የተባለው ወንጀል መፈጸም አለመፈጸሙን ለማረጋገጥ የሚቻለው ማስረጃ ሲኖር ብቻ ነው በፍትህ ስርአት ውስጥ ማስረጃ የማይተካ ሚና አለው ሲባልም ይሄንኑ እውነት ታሳቢ በማድረግ ነው በስፋት ስራ ላይ የሚውሉ ማስረጃ አይነቶችን ስናይ የሰው ምስክርነትየሰነድ ማስረጃዎች የባለሞያ ማስረጃዎች እና ገላጭ ማስረጃዎች ይገኙበታል በዚህ የስልጠና ጽሁፍ በዋናነት ትኩረት የምናደርግበት በሰነድ ማስረጃ ላይ የሚፈጸም የሀሰት ተግባር እና በሀሰት የተዘጋጀውን የሰነድ ማስረጃ መጠቀም የሚያስከትለውን ጉዳት እና የህግ ተጠያቂነት ነው በሰነድ ማስረጃ ላይ የሚፈጸሙ ጥፋቶችን ከማየታችን በፊት ሰልጣኞች በጉዳየ ላይ ግልጽ አረዳድ እንዲኖራቸው በማሰብ በቅድሚያ በዚህ ክፍል የሀሰተኛ ሰነድ ምንነት እና በጥቅሉ የሀሰት ማስረጃ ምን እንደሆነ አንዳንድ ነጥቦችን በማንሳት የምናይ ይሆናል። የሀሰተኛ ሰነድ ምንነት ስለ ሀሰተኛ ሰነድ ምንነት ከማንሳታችን በፊት የቃሉን አፈጣጠር ማንሳቱ ተገቢ ነው በዚሁ መሰረት ሀሰተኛ ሰነድ ከሚለው ንባብ መረዳት እንደሚቻለው ሀሰተኛ ሰነድ የሚለው ሀረግ ከሁት አማርኛ ቃላት የተመሰረተ ሲሆን እነሱም ሀሰት እና ሰነድ የሚሉ ናቸው። ሀሰተኛ የሰነድ ማስረጃ ሀሰተኛ ሰነድ ከአራቱ የማስረጃ አይነቶቹ አንዱ የሆነው የሰነድ ማስረጃ ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው። የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ እና አንቀጽ መሰረት ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ በመንግስታዊና ህዝባዊ ድርጅቶች ሰነዶች ላይ የሚፈፀም ከሆነ በሙስና ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው መንግስታዊ ሰነድ ሲባል የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ወይም የክልል ቢሮዎችና በየደረጃው ያሉ አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የወጡ በማስመሰል የሚዘጋጅ ሲሆን ለምሳሌ የንግድ ወይም ኢንቨስትመንት ፈቃድ ወረቀቶች የይለፍ ወረቀቶች የብቃት ማረጋገጫዎች የስራ ፈቃድ ወረቀቶች የስራ ልምድ የክፍያ ማዘዣዎች የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ሊብሬዎች ወዘተ የሚያካትት ነው የህዝባዊ ድርጅቶች ሰነድ ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወይም ተቋማት ሰነዶች ለምሳሌ የመጋዘን ደረሰኝ የእቃ ማውጫ ፈቃድ የትምህርት ማስረጃ የባንክ ክፍያ ሰነዶች እና መሰል በእነዚህ ተቋማት የሚሰጡ ሰነዶችን የሚመለከት ነው እነዚህ ሰነዶች በአግልግሎት ሰጪዎች ወይም በተገልጋዮች በሀሰት ሊዘጋጁ ይችላሉ ሰነዶችን ማዘጋጀትና መገልገል የሚያስከትለውን የህግ ተጠያቂነት በክፍል ሁለት በዝርዝር ይቀርባል። በተጨማሪም በወንጀል ህጉ አንቀጽ መሰረት በዚህ ህግ ያልተሸፈኑ ወንጀሎች ላይ ልየ ልዩ አዋጆች አማካይነት የወጡ የወንጀል ድንጋጌዎች ይሄንኑ ህጋዊነት መርህ በመከተል ዝርዝር ወንጀሎችን ደንግገው ይገኛለ ከሀሰተኛ ሰነድ ጋር በተገናኘም በወንጀል ህጉ አንቀጽ እና ቀጥሎ ባሉ ድንጋጌዎች በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት በመንግስታዊ እና ህዝባዊ በሰነዶች ላይ የሚደረግ የወንጀል ድርጊት እንደሚያስጠይቅ ደንግገው ይገኛሉሌ የሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መገልግል የወንጀል ተጠያቂነትን በቀጣይ ክፍል በስፋት የምናየው ይሆናል። የሀሰተኛ የሰነድ ማስረጃ ማዘጋጀት እና መገልገል የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት በአገራችን የወንጀል ፍትህ ስርአት ሀሰተኛ ማስረጃን በተመለከተ የሚያስጠይቁ በሁለት የሚከፈሉ ድርጊቶች አሌ እነሱም የመጀመሪያው ሀሰተኛ ሰነድን ማዘጋጀት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሌላ ሰው ወይም ድርጅት ባዘጋጀው ሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ነው ሀሰተኛ ሰነድ መፍጠርበእውነት የተዘጋጁትን ሰነዶች ወደ ሀሰትነት መለወጥ እና በዚሁ በሀሰት በተለወጠ ወይም በተዘጋጀ ሰነድ መገልገል የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነት ስናይ በመጀመሪያ በወንጀል ህጉ ስለጉዳዩ የተካተቱትን ድንጋጌዎች የምናይ ሲሆን ቀጥሎም የወንጀል ድንጋጌ የያዙ የተለያዩ አዋጆች ስለ ሀሰተኛ ሰነድ መፍጠር እና መገልገል የደነገጉትን የምናይ ይሆናል። ሌላው ትኩረት የሚሻው የህጉ አንቀጽ ላይ የተደነገገው በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል ነው በዚሁ ድንጋጌ መሰረት ማንም ሰው በሀሰት በተዘጋጀ ወይም ወደ ሀሰት በተለወጠ ሰነድ እያወቀ የተገለገለበት እንደሆነ በአንቀጽ መሰረት ከ ወር በማያንስ ቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከ አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል መሆኑን ነው በተጨማሪም ጥቅም ወይም መሻሻልን ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ተገቢ መብት ለማስገኘት የሚችሉ ፅሁፎችን ግላዊ ሁኔታን የሚገልፁ ማስረጃዎችን ወይም ምስክርነትን ማስረጃዎችን ወይም ማናቸውንም አይነት ጉዳይ የሚመለከቱ የምስክርነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም አስመስሎ የሰራ ወይም እያወቀ ይህን የመሰለውን ሰነድ እንዲገለገልበት ለሌላ ሰው መስጠት በወንጀል ህጉ አንቀፅ መሰረት በቀላል እስራት ወይም መቀሥ ያስቀጣል። በወንጀል ህጉ በሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ እና መገልገሉ በተጨማሪነት በወንጀል ህጉ አንቀጽ መሰረት የሚፈጸም የአታላይነት ወንጀል ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ወይም በሀሰት የተዘጋጅን ሰነድ በመጠቀም የራሱን ማንነት በመደበቅ የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት እና ግምት በመጠቀም በማድረግ ባለማድረግ ሌላውን ሰው አታሎ ተጎጂው የራሱን ወይም የሌላ ሰው ጥቅም የሚጎዳ ድርጊት እንዲፈጽም ካደረገ በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከ አመት በማይነልጥ ጽኑ አስራት እና መቀጮ የሚስቀጣ ወንጀል ነው በተመሳሳይ ሁኔታ በወንጀል ህጉ አንቀጽ መሰረት ተጠርታሪው ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ የተጣለብትን እመነት ወደጎን በመተው ለአንድ ለተወሰነ አለማ የተሰጠውመን ዋጋ ያለውን ንብረት የራሱ ወይም የሌላ ሶስተኛ ወገን ለማድረግ ሀሰተኛ ነሰድ ካዘጋጀ ወይም በሌላ ሰው የተዘጋጀውን ሀሰተኛ ሰነድ አገልግሎት ላይ ካዋለ እንደነገሩ ሁኔታ በቀላል እስራት ወይም ከ አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል። በሰነዶች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ከላይ የዘረዘርናቸው ብቻ አይደሌም በሌሎች አዋጆች የተደነገጉትን ወንጀሎች በሚከተለው ከፍል እናያለን ሀሰተኛ የሰነድ ማስረጃ ማዘጋጀት እና መገልገል በልዩ ልዩ አዋጆች በወንጀል ህጉ ላይ ሀሰተኛ ሰነድን ማዘጋጀት እና መገልገልን የተመለከቱት ወንጀሎች ተፈጻሚነታቸው በመንግስታዊና ህዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች ሳይሆን ከዚህ ውጪ ባሉት እና በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴ የምንጠቀምባቸውን ግላዊ ሰነዶችን በሀሰተኛ መንገድ ማዘጋጀትና መገልገል በወንጀል የሚያስጠይቅበት ሁኔታ ነው ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ እና መጠቀሙ በመንግስት ድርጅቶችበመንግስት የልማት ድርጅቶች እና በህዝባዊ ድርጅት ሰነዶች ላይ በሚፈጸምበት ጊዜ ወንጀሉ የሙስና ወንጀል ሲሆን ተፈጻሚነት የሚኖረውም የወንጀል ህጉ ሳይሆን የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር ይሆናል። በዚሁም መሰረት ማንኛውም ሰው የሌላውን ሰው መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ተገቢ ያልሆነ ማናቸውንም መብት ወይም ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ አንድ ፅሁፍ መዝገብ ወይም ማንኛውም ሰነድ የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት በማስመሰል ያዘጋጀ ወይም የፈጠረ በመንግስት ወይም በህዝባዊ ድርጅት መዝገብ ፅሁፍ ወይም ሰነድ የሰፈረን እውነተኛውን ፅሁፍ በመለወጥ ወይም በመደለዝ በሀሰተኛ ፊርማ በእጅ በተደረገ ምልክት ወይም በጣት ፊርማ በማህተም ወይም የሌለውን ስልጣን ወይም ችሎታ እንዳለው አስመስሎ በመፈረም ሀሰተኛ ሰነድ የፈጠረ እንደሆነ « አንድን የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰነድ በተለይ የፈራሚውን ስም ወይም ፊርማ ወይም የሰነዱን ይዘት አሃዝ ፍሬ ነገር ወይም ዝርዝር መግለጫ በሙሉ ወይም በከፊል በመለወጥ በማሻሻል በመቀነስ ወይም በመጨመር ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም ማናቸውንም ሀሰተኛ ፍሬ ነገር ያስገባ ወይም እንዲገባ ያደረገ እንደሆነ በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር አንቀፅ መሰረት ከሶስት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ያስቀጣል። ሌላው መገንዘብ የሚገባን ጉዳይ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር አንቀፅ መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቀው ሀሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ይዞ መገኘትና መገልገል ጭምር ሲሆን በዚህም መሰረት ወደ ሀሰት የተለወጠ ወይም በሀሰት የተዘጋጀ ሰነድ በቤቱ በተሽከርካሪው በኪሱ ወይም በማንኛውም አግባብ በቁጥጥሩ ስር የተገኘ እንደሆነ በአንቀጽ መሰረት ከሶስት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ ዕኑ እስራት። ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱም ሆነ መገልገሉ እላይ በተገለጸው አግባብ ከ አመት ጽኑ አስራት በላይ ሊያስቀጣ የሚችልበት ሁኔታ ካለ ዋስትናው በዚሁ ልዩ የስነስርአት እና የማስረጃ አዋጅ መሰረት የተከለከል ነው በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር ላይ የተደነገገው አንደተጠበቀ ሆኖ ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ ወይም መገልገሉ ወንጀል የሳን ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ በሚሰጣቸው በብሄራዊ መታወቂያዎችየልደት የጋብቻ እና መሰል ሰነዶች ላይ ከተፈጸመ በወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ብሄራዊ መታወቂያ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት እንደ ወንጀሉ አፈጻጸም እና የደረሰው ጉዳት መጠን እስከ አመት በሚደርስ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል ነውወ በሌላ በኩል ከግብር አከፋፈል ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሰው ሆን ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ለገቢዎች ሚኒስቴር የተጭበረበሩ ሰነዶችን ያቀረበ እንደሆነ በፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ አንቀፅ መሰረት ከሶስት እስከ አስራ አምስት አመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል። በዚሁ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት ህግን አለማወቅ ይቅርታ አያሰጥም ሀሰተኛ ሰነድ መፍጠር ወይም መገልገል የሚያስከትለው የፍትሐብሔር ተጠያቂነት ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት እና በመጠቀም ወንጀል የሚያስከትለውን የፍትሐብሔር ሀላፊነትም ስናየው እላይ ካነሳናቸው ሀሳቦች ጋር የሚጣጣም ሲሆን ወንጀለኛው ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀቱ ወይም ሌላ ሰው ባዘጋጀው ሀሰተኛ ሰነድ በመገልገሉ ከወንጀል ተጠያቂነት ባሻገር የመንግስት የህዝባዊ ተቋማት ወይም ሌላ ግለሰብ የገንዘብ ጥቅም ወይም ሞራል የተጎዳ ከሆነ ለደረሰው ጉዳት ተጠያቂ ነው በፍትሀብሔር ህጉ አንቀጽ መሰረትም የሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትም ሆነ መገልገሉ ግልጽ የሆነ ህግ የጣሰ ከሆነ በወንጀል አድራጊዎች ላይ ከወንጀል ቅጣት ባለፈ በድርጊቱ ምክንያት በግለሰቦችድርጅቶችእና መንግሰት ላይ ለደረሰ ጉዳት ተጠያቂ ይሆናል። ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትም ሆነ በሀሰት የተፈጠረን ሰነድ መገልገል የዜጎችን መሰረታዊ እና ሰብአዊ መብቶች ያለ አግባብ በመንጠቅ መብቱ ለማይገባቸው ሰዎች እንዲተላለፍ በማድረግ የሰብአዊ መብት ጥሰት እዲስፋፋ የሚያደርግ ሲሆን ከመንግስት እና ህዝብ ጥቅም አንጻርም በሀሰት በሚፈበረኩ ሰነዶች ምክንያት የህዝብ እና የሀገር ንብረት አለአግባብ እንዲመዘበር በማድረግ ለሙስና እና ሌላች የኢኮኖሚ ወንጀሎች መበራከት ዋነና መሳሪያ ሆኖ የሚያገለግል የወንጀል ተግባር ነው በጥቅሉ ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት እና መግልገል ህብረተሰቡ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ሲሆን ከህግ ተጠያቂነት አንጻርም ፈጻሚዎቹን ወንጀሉ ወጥ በሆነ ሁኔታ የሚያስጠይቅ ነው የፍትሀብሔር እና አስተዳደራዊ ሃላፊነትን በተመለከተ የሀሰት ትግባር እንደተፈጸመበት ሰነድ ባህሪ እና ወንጀሉ እንድተፈጸመበት ድርጅት ማለትም የመንግስት የመንግስት የልማት ድርጅት ህዝባዊ ድርጅት ወይም የግል ድርጅት አይነት በፍትሐብሔር ህጉ በመንገስት ሰራተች አስተዳደር አዋጅ ወይም በአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ መሰረት የሚያስጠይቅ ነው በዚህም ጉዳት ለደረሰበት ወግን ካሳን መክፈሉ እንደተጠበቀ ሆኖ በአስተዳደራዊ የዲሰፕሊን ቅጣት ከስራ እስከመባረር የሚደርስ ከባድ ቅጣትን የሚስያከትል የወንጀል ተግባር ነውወ ማህበረሰቡ እነዚህ ወንጀለኞች ወንጀሉን የሚፈጽሙበትን ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር ከፍትህ አካላት ጋር በመተባበር የወንጀል መከላከል ስራዎችንን መርዳት አለበት።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Commentaires:


memezon

Options de téléchargement | Convertir en PDF | Livre du jour

© dirzon | Conditions d'utilisation | Intimité | Sur | Services | Contact