Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የግጥም ዳሰሳ.pdf


  • word cloud

የግጥም ዳሰሳ.pdf
  • Extraction Summary

ኩራቱና መታበዩ ሳይገታ እነደውም እያየለ አስከ ምርጫ ዋዜማ ድረስ በትዕይንት መስኮትና በህትመት ውጤቶች ኢትዬጵያአንደ ኢትዬጵያ የሚል ስብከቱን ተያያዘው በኩራት አበጡ በፅብሪት ተለበጡ አመጋቢት ድረስ ባረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለማቶች በኩል ምስጢሩን ገለጡ በዚህ መልክ ቀጥለው በግንቦት ምርጫ ወቅት ቅንጅት ከፍተኛ ድምፅ አገኙይሁን አንጂ ብዙም ሳይቆይና ህዝቡ ለቅንጅት ያለው ፍቅር ሳይጠግግ የፓርቲው እንቅስቃሴ ዶግ አመድ ሆነ ሁልጌዜ ውብ ነገር ፅጣው ይኸው ነው ወይ።

  • Cosine Similarity

በእአችክችክ የግጥም መድብል ላይ የተደረገ የይዘት ትንተና በ ወለላ እዴቻ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነፅሁፍ ትምህርት ክፍል ለአርትስ ባችለር ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ የቋንቋዎች ጥናት ተቋም ሰኔ ዓም መግቢያ ናዳራ ህ እ ተ ተተተ ተተን ንቂ ቴቴቴቄዓ የጥናቱ አላማ ከ ከ ከ ን ን ሄሄ ሄን ንሄለን ሄ የጥናቱ ጠቀማታሒ ከ እኪ እ ከ ተ ሊን ን ን ንቄ ን ሄሄ ሄሄ ሄሄ ንቴ ቴዘ የጥናቱ ወሰን ኔ ህህ ተ ሲን ከ ሲቲ ሲን ንን ሄሄ ደ ቴቴ ቴቴ ሄቴ የጥናቱ ዘዴሒ ከ ከ እ ከ ከ ከ ሊን ን ደ ዘ ን ንዘ ለን ንህ ክለሳ ድርሳን ትወራዊ መሰረ ተ ተ ዜን ህንን ተ ሪ የስነ ግጥም ምንነት የስነ ግጥም ይዘት ትንተና የተዛማጅ ፅሁፎች ቅኝትሥ ዢዜ ዜዜዜዜ በእችክችክ የግጥም መፅሀፍ ውስጥ በተካተቱ ግጥሞች የይዘት ትንተና ማህበራዊ ጉዳዮች « ፍቅር ከ ከ ከ ከ ሲከ ተ ሊዘ ዘ ሄሄ ንሄ ፈቴ ዘ ቴቪቄዘዘቴቪ« ስለ እኩይ ባህርያት የሚያወሱ ስለ ሰናይ ባህርያት የሚያወሩ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ግጥሞች ሪገ « ሀገራዊ ጉዳዮችን የሚቃኙ ፊዛ አዩ ጥቅሶች በመገኛ ቋንቋቸው « ምስጋና በቅድሚያ ለዚህ ላበቃኝ አምላክ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው በማስከተልም ጥናቱ የተሳካ አንዲሆን ተጀምሮ እስኪያበቃ ድረስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሰይሉ እርማትና ጠቃሚ ምክራቸውን በመለገስ ከጎኔ ላልተለዩት አማካሪዬ ለአቶ የወንድወሰን አውላቸው ልባዊ ምስጋነዬን አቀርባለሁ ከዚህ በተጨማሪ አዚህ እንድደርስ የዘወትር ድጋፋቸው ላልተለየኝ ቤተሰቦቼ እንዲሁም ያላሰለሰ የሞራልና የገንዘብ አገዛ በማድረግ ለተንከባከበኝ ጓደኛዬ ፍቅረ በረቀዐ ላቅ ያለ ምስጋናን ሳልለግስ አላልፍም በመጨረሻም መፅሀፉን በመተየብና በማረም ያለመታከት ላገዘችኝ ሰብለ ባንትይርጉ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ምዕራፍ አንድ መግቢያ የጥናቱ ዳራ ሥነ ጽሁፍ ገሀዱን አለም መሠረት አድርጎ የሚሰናዳ ሲሆን የማህበረሰቡን ህይወት መፈተሻና መግለጫ መንገድ ነው ስነግጥም ከስነፅሁፍ ዘርፎች አንዱ ነውና ሌሉች የስነፅሁፍ ዘርፎች ለማህበረሰቡ የሚያበረክቱትን ፋይዳ ግጥምም ይጋራል እንዲያውም ከስነዕሁፍ ዘርፎች አንጋፋ እንደመሆኑ ከሰው ልጅ ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው ዘሪሁን ስነግጥም በእጅጉ ጥንታዊነት እንዳለው የሚነገርለት የኪነጥበብ ዘር ነው የሰው ልጆች ለብዙ ዘመናት ደስታና ሀዘናቸውን ምኞት ፍላጎታቸውን የአኗኗር ሁኔታቸውንና ልዩልዩ ገጠመኞቻቸውን በማንጎራጎርና በማዜም ሲገልፁበት ኖረዋል ስለዚህ ስነግጥምን መመርመር ማለት የየዘመኑን ማህበረሰብ ልዩልዩ የህይወት ገጠመኞች ማጤን ይሆናል ግጥሞችን ተወዳጅ የሚያደርጋቸውም ከቅርፆቻቸው ባሻገር ያለው ትውልድን የማሳየት ብቃታቸው መሆኑን መገንዘብ ይቻላል በተጨማሪም ለዛ ባለው መንገድ ሀሳብንና ስሜትን ለማቅረብ ያስችላልአሜሪካን አካዳሚ ኢንሳይክሎፒዲያ የግጥም ቃል ልዩ ትርጉም ያለው ሊሆን መዝገበቃላት ውስጥ ካለው ትርጉም ነፃ የሆነና ከመደበኛው ቋንቋ ያፈነገጠ ነውይላል ያፈነገጠ ነገርን መመርመር ያስደስታልና በዚህም ነው በ ዓም ታትሞ በወጣው የአቶ አብርሃም ረታ እችክችክ መፅሀፍ ውስጥ በተካተቱ ግጥሞች ጥናት ለማድረግ የታለመው አቶ አብርፃም ረታ ዓለሙ በይርጋለም ከተማ ከቤተሰቦቹ ጋር በኖረባቸው ከዎቹ በፊት በመምህርነት ሞያ ከተማዋን ሲያገለግል የቆየ ሲሆን በ ዓም በመገናኛ ብዙሃን ማሰልጠኛ ተቋም በጋዜጠኝነት ሠልጥኗል እንዲሁም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እርስዎ ለእርስዎ እምድር ላይ ይሰራ ነበር ምንም እንኳ ይህ ደራሲና ገጣሚ በአሁኑ ወቅት ከዚህ አለም በሞት የተለየ ቢሆንም ከላይ በተጠቀሰው አምድ ላይ ሲሰራ ለሚነሱ ጥያቄዎች አዝናኝ መልስ በመስጠት ይታወቅ ነበር ይህ ደራሲና ገጣሚ በጥራዝ መልክ አኑሮ ያለፋቸው መፃህፍት አከራይ ተከራይአካከራይ በአከራይና ተከራይ ህይወት ዙሪያ የሚሜያጠነጥን አልንተባልን አስባልን አባባ ሰው የለውም የዶር አብርሃም ፈለቀ የግጥም ስብስቦች የያዘው ቢላዋ እና ብእር ና ለዚህ ጥናት የተመረጠው አችክችክ የግጥም መፅሀፍ ነው በአችክችክ መፅሃፃፍ ላይ ትኩረት እንዲሰጥ ተፅእኖ ያደረገው አንቺ እናት ለሞኔ በሚል ርዕስ የተገጠመው ግጥም ነው ይህም የሆነበት ምክንያት ገጣሟው ለእናቱ ያለውን ፍቅር አውርቶ የማይጠግብና እንደውም ሟች እናቱን ለማስታወስ ከሞቱባቸው ቀን ጀምሮ ያነደዳቸው ሻማዎች ከአመታት በኋላ በአንድ ትልቅ ትሪ ላይ ቢያንስ ግማሽ ሜትር ከፍታ መስራቱን ይነገራል እናም በግጥሙ ይህንን የጠነከረ ፍቅር የምትሸረሽርን ሴት በማመስጠር የገለፀባት መንገድ ስለሚያስደምም ነው የዚህ ግጥም ይዘት የፈቀደውን ባሻው ሰዓት እየለገሰች ነፍስያውን በሀሴት የምትሞላለትን ሴት የሚያሞካሽበትና በተቃራኒው ከእናትም በላይ በላቀው ፍቅሯ ከአብራኳ የተካፈላትን አንዲዘነጋት በማድረጓ ግን ጠላቱ እንጂ ወዳጁ ብቻ እንዳልሆነች ይገልፃል ይህም ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የግጥም መፅሀፍ የቃላት ሀብታምነትና ብቃትየሀሳቦቹ ጥልቅነትና ጥቅልነት ለመተንተን የተዘጋጁ በመምሰላቸው የግጥም መፅሀፉን ምርጥና ምጥቅ አሰኝተውታል ስለሆነም እንደዚህ ዓይነት ፅሁፍን መተንተን አንድም ትፍስህትን ያመነጫል አንድም ደግሞ የግጥሙን ሀሳብ በማፍታታት መልዕክቱን በቀላሉ ወደ አንባቢ አይንና ጆሮ ለማድረስ ያስችላል የጥናቱ አላማ የዚህ ጥናት ዓላማ በአእችክችክ የግጥም መድብል ላይ የቀረቡ ግጥሞች ላይ የይዘት ትንተና በማድረግ በግጥሞቹ የተዳሰሱ አበይት ጉዳዮችን ማሳየት ነው የጥናቱ ጠቀሜታ የዚህ ጥናት ጠቀሜታ በመፅሀፍ ላይ ጥናት ሲደረግ የመጀመሪያው እንደመሆኑ መጠን ከዚህ በኋላ ጥናት ለማድረግ ለሚሹ ሁሉ እንደመነሻነት ያገለግላል የጥናቱ ወሰን ይህ ጥናት በአቶ አብርዛም ረታ በተገጠመውና በ ዓም ታትሞ በወጣው አችክችክ የግጥም መፅሀፍ ውስጥ በሚገኙ ግጥሞች ላይ የይዘት ትንተና ብቻ ማድረግ የጥናቱ ዘዴ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀዳማይ ተግባሩ የመፅሀፉን ግጥሞች በጥልቀት ማንበብና ከይዘታቸው አንፃር መፈረጅ ነው ለትንተናውም ከየፈርጁ ይበልጥ የሚወክሉ ግጥሞች በመምረጥ ተወስደው ገላጭ ዘዴን በመጠቀም ትንተና ተካሂዶባቸዋል ምዕራፍ ሁለት ክለሳ ድርሳን ትወራዊ መሰረት የስነ ግጥም ምንነት ስነ ግጥም በጣም ረጅም አድሜ ያለውና የሰው ልጅ ማህበራዊ ኑሮን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለመግባቢያነት ሲጠቀምበት እንደኖረ የተለያዩ መረጃዎች ያትታሉ መነሻውን ማህበራዊ ገጠመኝ ማድረጉና አንጋፋ መሆኑም አንድ ወጥ ብያኔ አንዳይገኝለት አድርገዋል አንድ ወጥ ብየና መስጠት ማስቸገሩን ዘሪሁን አስፋው ሲገልፁ ስነግጥም በኪነጥበብ ዘመነታሪክ ብዙ የኖረ ለመሆኑ እንደየዘመኑ ፍልስፍና አንደየዘመኑ ገናን የኪነጥበብ ፈለግ እንደየገጣሚውና እንደየስነፅሁፍ አዋቂው አተያይና የኪነጥበብ ዝንባሌ የተለያዩ ብያኔዎች ሲሰጡ ቆይተዋል ይላል ምንም እንኳ ስነግጥም አንድ ወጥ ብያኔ መስጠት አዳጋች ቢሆንም የዕለትተዕለት ነባራዊ ዓለምን ዕውነታ ለምናብ አግዝፎ ለማቅረብ የሚያስችል የፈጠራ ጥበብ መሆኑን ግን መናገር ይቻላል ሰፊ ሀሳብን ቁጥብ በሆነና ስሜትን በሚነኩ ቃላት የመግለዕ ኃይሉ ከሌሎች የጥበብ ዘርፎች እንደሚለየውም እንዲሁ ብርፃኑ ገበየሁ የአማርኛ ስነግጥም በሚለው መፅሀፍ የተለያዩ ምሁራን ስለ ግጥም ምንነት ያሉትን ካቀረቡት አንዱ ሳሙኤል ጆንሰን የተናገረው ነው ይህም ስነግጥም ምንድንነው። ፁ ተብሎ ሲጠየቅ አዬ ጌታው ስነግጥም እንዲህ ነው ከማለት ይልቅ ያልሆነውን ነገር መናገር እጅግ ቀላል ነው ሁላችንም ብርፃን ምን አነደሆነ እናውቃለን ነገርግን ስለብርሃን ምንነት ለመግለፅና ለማብራራት እንቸገራለን ብለዋል ከላይ እንደተመለከተው ለስነግጥም ወጥ ብያኔ ያልተገኘለት ገሚሱ በራሱ አተያይና ገጠመኝ እንዲህ ነው ስለሚለውሌላው ታላላቅ ስሜቶች የሚዘከርበት መሆኑን ስለሚያንፀባርቅ የተቀረው ከሰው ልጅ የዕለትተፅለት ትግል ጋር ስለሚያቆራኘው አንዳንዱ ደግሞ ጥልቀት ያለውን ሀሳብ ማቅረቢያ ነው የሚል ዕሳቤን ስለሚያቀርብ ነው በአጠቃላይ ስነግጥም የሚሰጠው ብያኔ የሚገለፀው የስነፅሁፍ አዋቂው ከዕይታ መጠኑ አና ለእርሱ ከሚመስለው ነገር ተነስቶ ነው ለማለት ያስደፍራል የስነግጥም ይዘት ትንተና የይዘት ትንተና በርካታ ርዕስ ጉዳዮችን በመዳሰስ በውስጣቸው የሚገኙትን ሀሳቦችመልዕክቶችና ስሜቶች ለመገንዘብ የሚያስችል ዘዴ ነው የይዘት ትንተናን ምንነት በተመለከተ የስነ አእምሮ መዝገበ ቃላትን ጠቅሶ ደረጀ ገብሬ እንዲህ አስቀምጦታል የይዘት ትንተና የተለያዩ ጭብጦች የያዙ ሰነዶች መልዕክቶችና ሀሳቦችና አስተያየቶችን የሚተነተኑባቸው የተለያዩ ዘዴዎችን የሚያቅፍ ነው እንዲህ ያለ ትንተና በአብዛኛው የተወሰኑ ቃላትሀረጋትግብ መች የሀሳብ መግለጫዎች የመሳሰሉት በሰነድ ውስጥ ስንት ጊዜ እየተደጋገሙ እንደሚመጡ ለማወቅ የሚያስችል ላቅ ያለ ስልታዊ ዘዴዎችን ሁሉይይዛል ረቦር ትንተና የታመቁ ሀሳቦችን በማፍታታት በሀሳብ ውስብስብነት የተፈጠረ ብዥታን ያጠራል ስለዚህም አንድን የፅሁፍን ሥራ ደጋግመን ካነበብን በኃላ ያለውን ረብ ገላልፆ ማሳያ መሣሪያ ነው ማለት ይቻላል የስነግጥም ይዘት ትንተናም ገጣሚው በህይወት ገጠመኞቹ ከቃረማቸው ተሞክሮዎች በመነሳት ለተደራሲያኑ ማስተላለፍ የወደዳቸውን ቁምነገሮች በተንታኙ ዓይን ማቅረቢያ መንገድ ነው እንዲሁም በግጥም ቃላት አማካኝነት የሚተላለፈውን መልዕክት በማፍታታት ማቅረቢያ ስልትም ነው የግጥም ትንተና ግጥሞችን ከቅርፅ ከይዘትና ከታሪክ አኳያ የመፈተሻ ዛደት ሲሆን ዓላማውም የራስንና የሌሎችን አረዳድና ለስራው የተሰጠውን አድናቆት ያካትታል ከዚህ ክዘነ በአጠቃላይ የአንድን ግጥም ይዘት ይህ ነው ለማለት አስቀድሞ ግጥሙን በጥልቀት ማንበብና መፈተሽ ተገቢ ነው ምክንያቱም አንድን ግጥም በአንዴ ንባብ ይዘቱን በትክክል ለመረዳት ስለሚያዳግት ነወ ጠልቆ ለማንበብ የገጣሚውን ስሜት ለመረዳትና ጥሩ ትንተና ለማድረግ ያስችላል ትንተናውም ተነባቢነት እንዲኖረው ያግዛል አንባቢን ማስደሰት ያስችላል የግጥም ትርጉም ስሜትንአመለካከትንና አስተሳሰብን ያካትታልየግጥም ትርጉም ጠቀሜታ የአንባቢን ስሜት መንካት መቻል ነው ሀበ የተዛማጅ ፅሁፎች ቅኝት በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ስነፅሁፍ ክፍል የቀረቡበግጥም ይዘት ላይ ትንተና ያደረጉ ስራዎች አሉ እነዚህ ዲማፆች በአብዛኛው በቃላዊ ግጥሞችና በጋዜጣዎች ለይ በወጡ ግጥሞች ለይዘትና ቅርፅ አይታ ትኩረት የሰጡ ሲሆን የተወሰኑት ደግሞ በመዕሀፍ ታትሞ በወጡ ግጥሞች የይዘት ትንተና አፅንዖት አንደመስጠቱ መጠን ተዛማጅ የተደረጉት በመፅሀፍ ላይ ከተሠሩ ጥናቶች ብቻ ናቸው ጥናቶቹ በተፃፉበት ዓመት ቅደም ተከተል ስንመለከት መጀመሪያ በአፈር ያነሳ ስጋ የግጥም መፅሀፍ ውስጥ ባሉ ግጥሞች ሂሳዊ ትንተና ንጉሴ የተደረገበት ጥናት ነውበዚህ ጥናት ውስጥ ንጉሴ ስለጭብጥ ምንነት ከገለፀ በኋላ ግጥሞቹ የህብረተስቡን የኑሮ መልክ የሚያሳዩ የተፈጥሮን ሂደት የሚያንፀባርቁ በኑሮ ገጠመኝ ላይ የሚያተኩሩ ስለሰው ልጅ የህይወት ትርጉም ጥያቄ የሚያቀርቡ በማለት ከፋፍሎ ትንተና አድርጎባቸዋል ። እንዲሁም ስለ ምት ስለ ዘይቤና ቃላት አጠቃቀም አሳይተዋል ሌላው የመዘክር ክፍሉም አቤ ጉበኛው ግጥም መዕሀፍ የተጠናበት ሥራ ነው ይህ ጥናት በቀደምትነት በሀገራችን ስለሚሰራባቸው የግጥም ዓይነቶች እንደ አብነት እየጠቀሰ አሳይቷልቅርፅን አስመልክቶም ገጣሚው የተጠቀመባቸውን የግጥም ዓይነቶች አሠኛኘትቤት አመታት ዘይቤያዊ አነጋገሮች የቃላት አጠቃቀምና የአፃባፍ ስልት አሳይቷል በመተንተንም ጭምር አመልክቷል በይዘቱ ስር ስለሀገራችን አድገት ተፈጥሮ ስለፍቅር ሀይማኖትን የሚመለከቱ መልዕክቶች የሰው ልጅ የተለያዩ ክስተቶች ቅኔያዊ መልክ ያላቸው ብሎ በመከፋፈል የይዘታቸውን ተንትኗል ግጥሞቹ ቀስቃሽ መካሪና አዝናኝ መሆናቸውን ገልዷል አንዲሁም የግርማ ገብሬ ሁለት በታተሙ የአቶ አያልነህ ሙላቱ የግጥም መፅሀፎች የይዘትና የቅርፅ ትንተና የሚል ነው በዚህ ዲማፅ የግጥሞቹን ቅድመእና ድህረ ስልሳስድስት ተብለው በመመደብ የይዘት ትንተና ተደርጐባቸዋል በእነዚህ ታሪካዊ ወቅቶችም የተፈፀሙትን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊእና ፖለቲካዊ አመለካከቶች የታዩባቸው መሆናቸው ተገልዷል እንዲሁም የአገጣጠም ስልት የተቃኘበት ሲሆን አስኛኘት የቃላት ምርጫና የዘይቤ አጠቃቀም ተጐሏል በአጠቃላይ ከላይ የተመለከቱት ፅሁፎች አፅንኦት የተሰጡባቸው ጉዳዮች ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ናቸው ይኸውም የተለያዩ ገጣሚያንን ስራዎች ፖለቲካዊና ማህበራዊ ብሎ በመመደብ የይዘት ትንተና የቅርፅአሰኛኘት ቤት አመታትና የቃላት ምርጫን ተመልክተዋል ይህ ጥናትም ከቀረቡት መመረቂያ ፅሁፍች ጋር ተመሳሳይ ሲሆን በእችክእችክ መፅሀፍ ላይ በመስራቱና በይዘት ትንተና ላይ ብቻ ትኩረት በማድረጉ ከተጠቀሱት ዲማያች ይለየዋል ምፅራፍ ሦስት በእችክችክ የግጥም መፅሀፍ ውስጥ በተካተቱ ግጥሞች የይዘት ትንተና ማህበራዊ ጉዳዮች በዚህ ክፍል በዓሦ ታትሞ በወጣው የአብርሃም ረታ የግጥም መፅሀፍ ውስጥ በተካተቱ ግጥሞች የይዘት ትንተና ተደርጎል በመፅሀፉ ውስጥ ከሚገኝ ግጥሞች ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚያነሱ ሲሆነ በመቀጠል ፖለቲካዊና ሀገራዊ ይዘት ያላቸው ናቸው በጥናቱ ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚያነሱ ግጥሞች ታይተዋል በዚህም ስለፍቅር ስለኑሮህይወትስለእኩይና ሠናይባህርያትስለአጉልልማድና ሌሎችም ሲነሱ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን የሚያወሱት ደግሞ ናቸው በዚህ ስር እንደንዑስ የታዩት ምርጫ ስለነፃነትዲሞክራሲ ናቸው የሀገር ውበትና ጀግንነትም እንዲሁ በሀገራዊ ጉዳዮች ስር የተተነተኑ ናቸው ፍቅር በዚህ ስር የምንመለከታቸው የፆታዊና ወላጆችን ፍቅር የሚቃኙ ግጥሞችን ነው በቅድሚያ ለማየት የተሞከረው ብቅ ያለ ሰው የለ በግጥሙ እንደነፍሱ የሚወዳት ግን የተለየችው ፍቅረኛው ከዛሬ ነገ ትመጣለች በሚል መንፈስ የሚጠብቅ ሰው ይታያል ይኸው ዞሮ መጣ ሰኔ ተመለሰ መንገድ መንገዱ ላይ ዕንቤ እየፈሰሰ ዱካዋ ባለመገኘቷ እንባዉ እንደጅረት እየወረደ ቢጠብቃት ብቅ አለማለቷ እንዳስደነገጠው ይገልፃል አእንደጥቅምት ቁር አጥንት የምትመታ አእንደሐምሌ ነሓሴ ብርዷ የሚያሰቅቅ ልቤስ አልቆረጠም አለ እየጠበቀ አለ እየታገለ ብቅ ያለ ሰው የለ ፍቅሯ ውስጣዊ ነፍሱን ሲያንዘፈዝፈው እርሷ ግን ከመዳፉ ባትገኝም ላም አለ በሰማይ እንዲሉ እሱም በዳጐስ ተስፋ እየጠበቃት መሆኑን ይናገራል በአጠቃላይ መለየት ምን ያህል እንደሚጉዳና ሰቀቀንን በሰው ላይ ዘርቶ እንደሚያሳቅቅ በማሳየት የፍቅርን ሀያልነት ያስረግጣል ሌላው በአንዲት ሴት ፍቅር የቀለጠን ሰው ያመለክታል ምነው ቀን ባልነበር ምነው ሌት ባልነበር መምሸትም ባልነበር መንጋትም ባልነበር ሁልጊዜእኔናንቺ ተቃቅፈን እንድንኖር ይህ ሰው ለሔዋኑ ባለው የጐነ ፍቅር ከጐኑ ባትርቅየሚለያያቸው አንድም ነገር ባይኖር ሀሴት እንደሚሰማው ይገልፃል በጠረንሽ አጥነው በከናፈር ሽገንዘው በወዝሽ ከፍነው ፍቅርና ሞት በእቅፏ ጥላስር ሆኖ ዋልያ ወደምንጭ ውዛ ይናፍቅ ዘንድ እንዲል ታላቁ መፅሀፍ ቅዱስአሱም ከናፍሯንወዚን ልቧንና ጡቷን እንደሚሻ ያመለክታል እንዲሁም ከሁለመናዋ አጐዳኝታው በፍቅሯ ባጅተው ዝንተ አለም ከአርሷ ጋር የሚኖርበትን ሁኔታ ቢያመቻቹለት እንደእንቦሳ ጥጃ እንደሚያዘልለው ያሳያል በአጠቃላይ ማንም ሰው ያፈቀረውን ሲያጣ አውላላ ሜዳ ላይ እንደቀረ ይሰማዋል በመሆኑም መቼም ቢሆን ከፍቅሩ ባይለይ እንደሚመርጥ ለመመልከት ያስችላል ቀጥሎሔዋን የሚለው ግጥም ሴት ልጅ የትኛውንም መንገድ ተጠቅማ ወንድን በቁጥጥር ስር ማድረግ እንደምትችል ይጠቁማል ባይንሽ ባካፄሄድሽ በሴታዊነት ብልዛፃት ንገሪው ጥቀሽው በይ ተሸኩርመሚበት ሔዋን ፍንጭ ሰጥታው ጥቅሻና ምልክት አዳም መቼም ቢሆን አልታየም ሲያመልጣት የምን ዕባብ በለስ ምን ማፈር መቅለስለስ የምን ዓቤል ቃዬል ምን ገሃነም ሲዖል ጥቀሽው ይጥቀስሽ አውድቂው ያውድቅሽ አንቺ ከጅለሽው ማንም አያመልጥሽ። የሚሰለች ነገር ታዲያም በከንቱ ውዳሴ የታጀበ ፍቅር ይጎፈንናል ስለሆነም ይህ እኩይምግባር በማህበረሰቡ ውስጥ ማቆጥቆጥ እንደሌለበትና ተመንግሎ እንዲወጣ ይገልፃል ስለ እኩይ በህሪያት የሚያወሱ በዚህ ርዕስ ስር የሚመለለከቱት ግጥሞች ያልታገሉበትን ጥቅም መሻት ክፋትና እኔ ብቻ አዋቂ ነኝ ባይነት ቅናት ጥልቅባይነትና ከበራን መሻት ያሳያሉ በቀደምትነት የተተነተነው ግጥም አፌላይትፉብኝ የሚለው ግጥም ሲሆን ይህ ግጥም ስለ ጥቅማጥቅም ሁለነገሩ ላይ እንደፈቀዳቸው እንዲፎልሉበት ራሱን አሳልፎ የሰጠና ስለነፃነቱ ቅንጣት ታህል ደንታ የሌለው ይልቅዬን ለጊዜው ፈንጠዝያ የነከሩት ቦታ የሚዘፍቅ ሰውን ያመለክታል ስለመስት ግዴታ ጠልቆ ቢገባኝም ስለሀላፊነትና ተጠያቂነት ጠንቅቄ ብረዳም ስመኝ የኖርኩትን ስራብ የከረምኩትን ሳልም የባጀሁትን ሥልጣን አስታቀፈኝ መብት ግዴታ የሚሉ ቃላት ለእኔ ከቃለትነታቸው በዘለለ ምንም ስሜት አይሰጡኝም በዚህች ምድር ለይ ለእኔ ትልቁ ቁምነገር ስልጣን ማግኝት ነውየተንደላቀቀ ህይወት የሚመሩ ሰዎች ዓይነት ኑሮ ከተቸረኝ የመሻቶቼ ሁሉ ጥም ከተቀረጠልኝ ወሰኑ ያልተገደበ ደስታ ይኖረኛል ከዚህ በኋላ እንደመዳዳታቸው ከአግራቸው ስር አጋድመው የእግራቸውን ትቢያ ቢያስልሱኝ ምናምንት ቅሬታ አይሰማኝም የምን ዲሞክራሲየምን አኩልነት ባፍንጫዬ ይውጣ የቃላት ስርርቶ አፌላይ ትፋብኝ ዲሞክራሲም መብቴ ይከበር ብዬም አልከራከርም እንደውም ዲሞከራሲ እኮ ቃላት ተቀናጅተው የሚፈጥሩት ቃል እንጂ ሌላ ምንም አይደለም በማለት ይናገራልበአጠቃላይ የሚደረግበት በደል ከአእምሮው በላይ ሆኖ እንደአሬትቢጎመዝዘውም እንኳ ያሻው ይፈፀምለት እንጂ ለህሊናው ሳይጨነቅ መሬት ልሶ የሚኖር ለከርስስ እንጂ ለህሊናስ የማይኖርን ግለሰብ ያሄሳል ቀጣዩ ግጥም በወዳጁ ላይ ገደብ የለሽ ቅናት የተጣባውን ሰው ያሳየናል እንደማያልፍ የለም ሁሉም ነገር አልፏል ልፈታ ተዳርሷል ግንባርክን ሳነበው ወሬህን ስሰማ ገርሞኛል ደንቆኛል በለመደ ዐመልህ የበለጥኩህ መስሉህ መታሰር ሀብት ሆኖ ትቀናብኛለህ ጸረ ይህም ሲያንሰው ገድለውልኝ ባረፍኩ ሆነ አሉ ስዕለትህ ይህ ወሰን ያጣ ቅናት የተንፀባረቀው ይበልጠኛል ብሉ ባሰበውና በእስር ለይ ባለ ሰው መሆኑን ይገልፃል ይህ ሰው በጓደኛው ላይ የሚያነባቸው አሉታዊ የአካል ገፅታዎች እንዳሳዘኑት ይናገራል የቅናቱ የክፋቱ ክፋት በጓደኛው አስራት እንኳ ሳይቀር እንዲመቀኝ ስታጋፍጠው ዝም ብሎ መቀበሉ አስደንቆታል መታሰር ጥሪት አእነዳልሆነና የአርሱ መሞት ለምን ደስታ ሊሰጠው እንደቻለ አስገርታል ምናልባት ሁለቱም አፈር ናቸውና ምስጥ ሆኖ ሊበላው እንደማይችልም ያሳያል ስለሆነም እንዲህ በቅናት ጆንያ መጠቅለሉ ጠቀሜታ እንደሌለውና በደረሰበት የምቀኝነት ውርጅብኝ ልቡ የተሰበረ ሰው መሆኑን ያመለክታል በአጠቃላይ ግጥሙ ቅናት ማህበረሰቡን የሚጎዳ ነቀርሳ በመሆኑ እንዲወገድ ለማሄስ ሞክሯራል በማስከተል ቢንቢ የሚለው ግጥም ውስጥ ቢንቢ ውኩል የተደረገው ህይወቱን በሙሉ በሰው ላይ ክፋትን በማድረግ ስመጥር ለሆነ ሰው ነው ባወቅሁት ታሪክህ በቀደመው ዝናህ አጅግ ስለምፈራህ ባጐበር ውስጥ ሆጌ ነው የምወዳጀጅህ ቢንቢ ይህ ሰው የሰርክ ተግባሩ ተንኮልን ማድረጉ ስለሚታወቅ የርኩሰት ስራው አንዳይነካን ጓደኛ ማድረግ ካለብን በከፍተኛ ጥንቃቄ ተሞልተን መሆን አንዳለበት ይገልፃል በአጠቃላይ ግጥሙ የሰውን ህይወት ለማበላሸት የመይቦዝኑ ሰዎቸወን በብልሃት መከታተል እንዳለብን ያሳስበናል ሌለው ግጥም አንዳችም በሌላቸው ተሰጥኦ ራሳቸውን ከደራሲያን ከተዋንያን ከገጣምያንና ከሌሎች ሁሉ ጐራ በመመደብ እኔ ልታይበት የሚያዘወትሩ ሰዎችን ያመለክታል መህበር ተከልለው ሙያ ተጠልለው ስለሚተካቸው ትውልድ የሚትከነከኑ ከእነርሱም አብልጦ የሚሰራ ተተኪ ምቾታቸውን ይነሳቸዋል በባዶአቸው አቅም አድምተው ከሚሰሩና ጥበባቸው ሰዎችን ከሚማርክ ባለሙያዎች ጋር ራሳቸውን መፈረጅ ምንም ረብ እንደማይሰጣቸው ይገልፃል አሸም በሉን ሲሉ አንቱ በሉን ሲሉ አንሸላለም ሲሉ ገረሙኝ እነሱ አሻምበሉን ራሳቸውን ሰማይ ጥግ በመድረስ ሌሎች በሚሰጧቸው ከበራና ቁልምጫ ርካታን ለመሸመት ይራራጣሉ ትኩረት ቢነፈጉም አንደምንም ተፍጨርጭረው ራሳቸውን ለመስወደስ ይሻሉ በማለት ይወርፏቸዋል ስለሆነም እነዚህ ሰዎች ይህን መጥፎ ምግባራቸውን እንዲያርሙ መካሪና ገሳዒ ያስፈልጋቸዋል ለማለት ታጣወይ ጠፋወይ እነእነአንቱዬን ሃይ ባይ። ይህ አልባሌ ተግባራቸውን ከምመለከት ግን መሞት ይሻለኛል ምክንያቱም ባደረግሁላቸው ነገር ተጠቃሚ ሳይሆኑ ልመናቸው ካልቀረ ምንም አልፈይድምና መቶ ዓመት መድፈኑ ምን ረብ አለው ላያመሰግኑ ታክመው ላይድኑ ካልጨመርኩኝ ምንም ምን ያደርጋል ታዲያ መቶ አመት መድፈኑ የአቡክያ ድምፅ በአጠቃላይ አባቶች በሰሩላቸው ብቻ ልባቸውን አንሰራፍተውና ሀሳባቸውን ጥለው አልባሌ ኑሮአቸውን በአባቶቻቸው ሀብት ላይ የተከሉ ይህም አልሳካ ሲላቸው መናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም ገንዘብ የሚቃርሙትና ውዳቂ ህይወት የሚመሩ ትውልዶችን ያሔሳል የድሮ አባቶችም በአሁኑ ትውልድ ያለመርካት እነንደሚታይባቸው ያመለክታል በመቀጠል በጊዜ ለኩሉ የሚለው ግጥም ሲሆን ሁሉንም ነገር በአርምሞ ብንከታተል እያንዳንዲ ጉዳይ የምትሳካበት ጊዜ አንዳለው ያጠይቃል ትዕግስት ላደላቸው ቦጊዜ ለኩሉ ሥርየት ይከተላል ርጋታ ያገመው ቁስልም ይጠግጋል የታሰረ ቢሆንይዘገያል እንጂ ቆይቶ ይፈታል ያጣም ዕድሜ ሲያገኝ ባለፀጋ ይሆናል በሽተኛም ለምዶት ከህመሙ ይስማማል ፍትሕ የጐደለው በትርዕ ይካሳል በጊዜ ለኩሉ ለሁሉም ጊዜ አለው አንዲል መፅሀፉ መክብብ በችግርና ስቃይበረሀብና ስቃይ ቢታለፍ ትዕግስት ካለ ሁሉም በጊዜው ይከናወን ዘንድ ግድ ነው በግጥሙ አስረግጦ ለመንገር የታሰበው ያሰቡት ነገር ባሰቡት ሰዓት ካልተፈፀመላቸው በቁጣና በብስጭት ራሳቸውን የሚጎዱ ያሹት ጉዳይ በወደዱ ጊዜ ካልተተገበረ ራሳቸውን በተስፋ መቁረጥ አርጩሜ የሚገርፉ ሰዎች እንዳሉ ለማሳየት ነውነገር ግን ይህ ባህርይ አጓጉል በመሆኑ እያንዳንዲን የሰከንድ ሽርፍራፊ በትዕግስት የተሞላ ህይወት መምራት እንዳለብን መምከር የፈለገ ይመስላል ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ግጥሞች በዚህ ዐብይ ርዕስ የምንመለከታቸው የግጥም ይዘቶች የሚዳስሷቸው ጉደዩች ስለቅንጅት ፓርቲስለህዝብና ፓርቲስለዲሞክራሲስለቱርክለሀገር ደንታ ስለሌላቸው ግለሰቦች ናቸው የመጀመሪያው ግጥም አበባ አፈጀች የሚለው ግጥም ሲሆን የሚያመለክተው በግንቦት የተካፄደውን ምርጫ ነው እነሆ ክረምት አለፈ ዝናቡም መጥቶ ሄደ አበቦች ኩሩ አጌጡ አበቦት ውኩል ተደረጉት ለቅንጅት ፓርቲ መሆኑን የምንቀበለው ሐቅ እንደሆነ ከሰዕሉ መመልከት ይቻላል ይህ ፓርቲ ከምርጫው ቀን በፊት ባደረገው ከፍተኛ ቀስቀሳ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ ነበርና ይህም እንዲታበይ በሩን ከፈተበት። ለሁለም የሚፈርድ የእኩል ዳኛ እስኪገኝ ሁሉን አኩል የሚያዝ ህዝቡን ለመክር ምንም ያህል እንካ ተቆርቆሪ አስተዳደር ባታገኝ ሀገርንና ገንን ለመበጥበጥ አሰስገሰስ ወሬዎችን የሚቀባጥሩልህን አእምሮህም ሆነ ልቦናህ አንጥሮ ይመልሰው እንጂ አትቀበላቸው በሁለት ሺህ ያደረስህም የጋራ ፈረስ አለመሆን ነውና በርታ በማለት ያጠናክራል ሌላው ረታ ነው ይህ ግጥም ኢትዬጵያ አንድም ከጥንት ጀምሮ ነፃነቷን አስጠብቃ የኖረችመሆኗን ሲያመለክት አንድም ከድህነት ሳትላቀቅና ለውጥ ሳታሳይ ለሁለት ሺህ መድረሷን ያመላክታል ጦብያ እንደለመደች ይኸውወ ዛሬም ረታች ሺህ ለአልቦ ያው ድል አደረገች ወይም አሸነፈች ወይንም አቸነፈች አጠመንጃ ይልቅ ታሪክና ትዕግስት ይልቀሉ እያለች ኢትዮጵያ ዛሠም ረታች ሀገራችን ትፅግስትን ስንቅ በማድረግና መቻቻል የስፈነበት ህይወት በመምራት ታሪኳን አሰጠብቃ ለሚሊሊየም መድረሷ እንደድል አድራጊ ያስቆጥራታል ሲል በሌላ መልኩ ደግሞ አፈሪካ በግሎባላይዜሽን ሄደት በዝረራ የወጣች አህጉር እንደሆነች ይናገራል በዚህም ኢትዮጵያ በአፍሪካ እንደመገኘቷ መጠን የአፍሪካ መሸነፍ ለኢትዩጵያም ሽንፈቷ ነው ስለሆነም ሌለው ሰልጥኖ ጨረቃ ላይ በከተመበት ዘመን ኢትዮጵያ ግን የግሎባላይዜሽን ጥሩ ተፎካካሪ ሳትሆን ታሪክ የሚለው ቃል ዘወትር አባቶቻችን እንዲህ አደረጉ በማለት ትዕግስት ዝምታን ተረጋግቶ መቀመጥን ጠመንጃ የድህነት ማጥፊያ መሣሪያን ይወክላል ስለሆነም ድህነትን ለማጥፋት ከመትጋት ይልቅ ያለምንም ጥረት መቀመጧ በባዶው ለሚሊኒያም እአንድትደርስ አድርጓታል ለማለት የፈለገ ይመስላል ቀጥሎ አመነትና ፍቅር በሚለው ግጥም የሀደሩ አለመበልፀግ እጅግ ያስደመመውና ልቡ የተነካ ሰው ተስሏል ከለመዱት ገላ ከሚወዱት ጋራ እምነት ፍቅር ካለይገፋል ተራራ ታዲያ ጦቢያ ሀገሬ እምነት አጥታ ነው ወይ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact