Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ዝንጀሮ አንድን ክምር በልቶ ከጠገበ በኋላ ክምሩን አፈ ራርሶና በታትኖ እንደሚሔድ ወያኔም ኢትዮጵያን አፈራርሶ ሕዝብን ለያይቶ ታሪክንና ባሕልን ደምስሶ ለመጥፋት የቆረ ጠ ነው። ወያኔ ብሎ የጨመረው ቃል በትክክል የዓመፅ ግብሩን የሚገልጽ ነው። መጽሐፉም ፊታችሁን ወደ ምሥራቅ አዙሩ የሚለው ተመልከት ዓላማህን ተከተል ባህልህን የሚል መሆኑም መዘንጋት የለበትም በዚህ በኛው ምዕተ ዓመት ለማመን አስቸጋሪ የሆኑ ድርጊቶች መከሰታቸው ነው። ከምሁራንና ከሃይማኖት መሪዎች መካከል በዘር የሚያመልኩ በቋንቋ የሚሰግዱ የጎሳ ድርጅት አባሎች አሉ መባሉ ነው። ይህ የአፍሪቃውነትን ምንነት ማጥፋት ማለት ነው። ታዲያ ይህን ያህል ገንዘብ ከተዋጣ በኢትዮጵያ ያሉትን ችግሮች ለማስወገድም ሆነ ሕዝባዊና ፍትሐዊ መንግሥት ለማቋቋም የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት በተቻለ ነበር መረዳዳት መተሳሰብ ካለ የራቀው ይቀርባል የሞራል ድጋፍ የሰጡኝ የዘመኖቻችን ዕድሜ ሰባ ዓመት ነው ቢበዛ ግን ድካምና መከራ ነው።
ነ በ ሎዛ ቿ ብላታ ዳዊት ገብረ እግዚ አቶ ተስፋዬ ገብረ እግዚ አቶ ገብረ መስቀል ክፍለ እግዚ ልአቶ ገብረ እግዚአብሔር ፍራንሷ አቶ ጎይቶም ጴጥሮስ ብላታ ኤፍሬም ተወልደ መድኅን በኢትዮጵያ ጦርና የፖሊስ ኃይሎች ከፍተኛ ማዕረግ የነበራቸው ኤርትራዊያን ጀኔራል ያዕቆብ ገብረ ልዑል በጦር ኃይሎች ጀኔራል ኢሳያስ ገብረ ሥላሴ በጦር ኃይሎች ጀኔራል ኢያሱ መንገሻ በጦር ኃይሎች ጀኔራል አማን ሚካኤል አንዶም በጦር ኃይሎች ጀኔራል መብራቱ ፍስሓ በፖሊስ ሠራዊት ጀኔራል ምሕረተአብ ተድላ በጦር ሠራዊት ጀኔራል ጎይቶም በፖሊስ ሠራዊት ጀኔራል መስፍን አምባዬ በፖሊስ ሠራዊት ጀኔራል ገብረ ማርያም አዛዚ በፖሊስ ሠራዊት ጀኔራል በረኸት በፖሊስ ሠራዊት እንዲህ ያለ ከፍተኛ ማዕረግና ሥልጣን እየሠጠ አቀማጥሎ በክብር የያዘ መንግሥት በባርነት ገዛ ማለት ያስችላል ወይ። ክቡር ጀኔራል አስፋው ወልደ ጊዮርጊስ ከጠላት ወረራ በፊት ወደ ውጭ አገር ተልከው የውት ድርና ትምህርት የተማሩ ጥሩ አገር ወዳድ ጀኔራል ነበሩ። ክቡር ጀኔራል ኢሳይያስ ገብረ ሥላሴ የምድር ጦር ዋና አዛዥ የነበሩ የውትድርና ትምህር ታቸውን ከጠላት ወረራ በፊት በገነት ጦር ትምህርት ቤት ያጠናቀቁ ወደ ውጭ አገር ሒደው ክፍተኛ የውትድርና ሙያ የቀሰሙ አምስት ዓመት ወራሪውን ጠላት በዓርበኝነት የታገሉ አገር ወዳድ ጀኔራል ነበሩ። የተቃወሙ በትም ዋና ምክንያት አንደኛ ንጉሠ ነገሥቱ ዓፄ ኃይለ ሥላ ሴ ለአገራቸው አገልግለዋልና በእርጅናቸው ግዜ ሊያዝኑ አ ጄኔራል ኢሳኢያስ ገብረ ሥላሴ ወልደ ጊዮርጊስ ውጭ አገር ተልከው የውት አገር ወዳድ ጀኔራል ነበሩ። ጀኔራል አማን የኛ ክፍለ ጦር አዛዥ በነበሩበት ግዜ ያት በአመራር ችሎታቸው የሚመካባቸው በአስተዳደር ጥበ ባቸው ከመጠን በላይ የሚወዳቸው የሚመሩት ሠራዊት ብቻ አልነበረም። የክብር ዘበኛ ጦር ዘመናዊ እንዲሆን ለማድረግ ከስዊድን መንግሥት ጋር በመስማማት የመኮንኖች ማሠልጠ ኛ ትምህርት ቤት እንዲከፈት ከፍተኛ ጥረት ኣድርገዋል። ክቡር ደጃዝማች ነጋ ከፋሽስቱ ጦር ጋር በጦር ሜዳ ፊት ለፊት በአደረጉት ፍልሚያ የጠላት ታንክ ይደፈጥጠኛል በአውሮፕላን በቦምብ ይበጣጥሰኛል ብለው ሳይፈሩ የያዙት መሣሪያ ሲግልባቸው ከጠሳት ታንክ ላይ ወጥተው በታንኩ ውስጥ የነበሩትን የጠሳት ወታደሮች በጎራዴ የጨፈጨፉ አንጡ ድገሙ ቢባል ምሥል የሌላቸው ጀግና ናቸው በቆራጥነታቸውና በድፍረታቸው በፈጸሙት ጀብድ ያልተደነቀና ያልተገረመ አልነበረም ነጋ በጎራዴ የሚለው ቅጽል ስም የወጣሳቸውም በዚያን ግዜ ነው በየዘመኑና በየትውልዱ አንድ አንድ ጀግኖች ይወለዳሉ በሃየኛው ምዕተ ዓመት ከተወለዱት ጀግኖች ነጋ በጎራዴ አንዱ ናቸው ለአንድ አገር ሠላምና ጸጥታ አስተማማኝ ዋስትና የሚኖረው በአገር ፍቅር የታነፀ ሠራዊት ሲኖረው ብቻ ነው ለአገር መከላከያ ብዙ የጦር መግሪያ ከመሸመት ይልቅ ወጣቶችን በአገር ፍቅር ትምህርት ኮትኩቶ በማነጽ ያሳደገ አስተማማኝ የመከሳከያ ሃይል ይገነባል ማለት ነው በአገር ፍቅር የታነጸን ሠራዊት ለደመወዝ ሲል የሚያገለግል ዘመናዊ መሣሪያ አስታጥቆ አገርን ከአጥቂ ለማዳን ማሰብ ቋያ እሳት ሲነሳ በገለባ ምሽግ የመከላከል ያህል ነው። ኮ ጅሎ መቁ መመ መመመ አመ ሠዬ ቁመው ወጣቱ ምሁር ልጅ ገርማሜ ንዋይ በኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ወጣት ምሁራን ውስጥ ልጅ ገርማሜ ንዋይ አንዱ አገር ወዳድ ም ሁር ነበሩ። እነ ፕሳቶን ሩሶ ሔግልና ማርክስ ቴኦሪያቸውን ከመዘርጋታቸው በፊት ኢትዮጵያውያን ፍልስፍናን በርኅራጌ ላይ መሥርተውት እንደነበር ታሪክ በተግባር ገልፆታል ኢትዮጵያ በረጅሙ የነፃነት ዘመኗ በሁሉም እረገድ ራሷን የሚያስችሉ የተሟላ ዕውቀት ያፈራች ስትሆን በኛው ምዕተ ዓመት ያለ ትውልድ ከውጭ አገር አስተማሪዎች ማምጣቱ በታሪክ የሚያስወቅሰው ነው ትውልዱ ያፈራቸው ምሁራን አንዳንዶቹማ ይግረማችሁ ብለው በውጭ አገር ያሌ በአገራቸው ቋንቋ የተጻፈን ታሪክ እንደ ኋላ ቀር እየቆጠሩ በመናቅ በውጭ አገር ሰው በአስተርጓሚ የጻፈውን ያነባሉ ከጠላት ወረራ ከዓም በፊት ቀደም ብሎ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የውትድርና ሞያ አስተማሪዎች ፈረንሳይንና ቤልድግን ከመሳሰሉ ኮሎኒያሊስት አገሮች አስመጥተው ነበር ይህም አዲስ ሥልጣኔ ከጀመሩ ያውም አፍሪካውያንን በቅኝ እየገዙ ከሚያሰቃዩ አገሮች አስተማሪ ማምጣት የራስን ሥልጣኔ የሚያዳፍን የማስተዋል ጉድለት ነበር ወታደራዊው ቡድን ደርግም ሥልጣን እንደያዘ የኮምዩኒስትን ርዕዮት ካልተከተልክ መንግሥቱ አይፀናልህም ተብሎ ወደ ሶቪየት ቻይና ጎራ ብቅ ብለው የተመለሱ አክራሪ ምሁራን ባደረጉበት ግፊት የሕዝብን ዕድገት ሳይመረምር አጠቃላይ ሁኔታውን ሳይገመግም በጭፍን ያለወቅቱ ኅብረተሰባአዊነትን ሶሻሊዝምን ያወጀው በሥልጣን ለመቆየት እንጂ ሥርዓቱ ለሕዝብ ይበጃል አገሪቱን ያሳድጋል በሜል ሃሳብ አልነበረም። ይህም ከውጭ በመጣ ስልት ሳይሆን በኢትዮጵያዊያን የውጊያ ጥበብ ነው የኢትዮጵያ ብርሃን በመባል የሚታወቁት እቴጌ ጣይቱ ብጡልም መቀሌ ላይ መሽጎ የነበረውን የኢጣሊያ ወራሪ ጦር ያንበረከኩት በውጊያ ጥበብ ነው የመስፍኑ የራስ ዓሊ አማች የዳሞቱ ገዥ ደጃዝማች ዘውዴ በመሳፍንቱ ላይ አምፀው በመነሳታቸው የአገው ምድር ገዥ ከነበሩት ከደጃዝማች ኤሊያስ ጋር ለውጊያ በተሰሳለፉበት ወቅት ደጃዝማች ዘውዴ አንድ ሺህ ግልገል በቅሎ ደረቅ ቁርበት አስጭነው በሌሊት በደጃዝማች ኤሊያስ ጦር ማሀል እንዲለቀቅ በማድረጋቸው የደጃዝማች ኤሊያስ ጦር ጠሳት ገባብን ብሎ ሌሊቱን ሙሉ ሲታኮስ አድሮ ጥይቱ ሲያልቅበት ደጃዝማች ዘውዴ በጦራቸው ምንም ጉዳት ሳይደርስ ደጃዝማች ኤሊያስን ማርከዋቸዋል እንዲሁም ከጎጃሙ ገዥ ከደጃዝማች ደስታ ጋር ለውጊያ በተሰለፉበት ወቅት ደጃዝማች ዘውዴ ያገሩን ሁሉ ከብት ሰብስበው ዙሪያውን በአጥር አስከብበው በራሜዳ ላይ ከብቱ እንዲነዳ አድርገው አቧራው ወደ ሰማይ ሲጎን ያዬ የደጃዝማች ደስታ ቃፊር ጦር የሚግተለተለው ሰው መስሎት ወደ ደጃዝማች ደስታ ጦር ሔዶ ከንጉሥ ሠራዊት የሚበልጥ ሺናሺ ነው የሚቻል አይደለም ብሎ በመንገሩ የደጃዝማች ደስታ ጦር ውጊያውን ጥሎ በመፈርጠጡ በደጃዝማች ዘውዴ ጦር ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይድርስ ደጃዝማች ድስታን ማርክዋል ደጃዝማች ዘውዴ ሁለቱንም ደጃዝማቾች ጉዳት ሳይደርስባቸው ከማረኩ በኋላ ሲፎክሩ አገውን በቁርበት ጎጃምን በከብት ድል አደረኳቸው አንድ ሰው ሳይሞት ብለዋል። ከቴዎድሮስም ሆነ ከሌሎች የውጊያ ጥብብ ሌላ በአምስቱ የኢጣሊያ ወረራ ወቅት የኢትዮጵያ ዓርበኞች በየጎራውና በየሸንተረሩ ግዙፉን የኢጣሊያ ወራሪ ሠራዊት በአነስተኛ ኃይል እያቸነፉ ወደ መጣበት ይመልሱት የነበረው ዘመናዊ የጦር መሣርያ ከያዘው ግዙፍ ሠራዊት ይልቅ የኢትዮጵያ ዓርበኞች የተሻለ የውጊያ ስልት ስለ ነበራቸው ነው ታዲያ የሚገርመውና የሚከነክነው ይህን ተያይዞ የመጣን የውጊያ ጥበብ ያስተዋለው ክፍል አለመኖሩ ነው እኔ በጦር ትምህርት ቤት የተማርኩት ከፈርንጅ የመማርያ መጽሐፍ ማኑዋል በተተረጎመ እንጂ በኢትዮጵያዊያን ስነ ልቦና የተዘጋጀ አልነበረም። በተግባር እንደታዬው ጨካኝ ሠራዊት ከኃይል ጋር አገናኝተው እሳትና ጭድ በመሆን በልቶ ጠፍቷል የተራማጅ አዢ ወዳዶችን እንቅስቃሴ ያሰናክሳሉ አድኃሪ ኃይሎችም ቅጣቸው ጠፍቷል በመስታወት ቤት ውስጥ ዘምነው ይኖሩ የነበሩ ነዋይ አምላኪዎችም በሞራል ያልገነቡት ሥር ያልነበረው የሰው ላብ የመጠጠው ተቋማቸው በማታለል በማጭበርበርና በመዝረፍ የተገነባ በመሆኑ ተፈረካክሷል መቼም አብሮ የኖረን ውስብስ ችግር በአንድ ግዜ አስወግዶ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመትከል የዳበረ የሕሊና ማሳ የለም በሁሉም ዘንድ ያለውን ዕውርነት ለማስወገድ ከተፈለገ ወገብን በድግ አስሮ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል ማኅበረ ሰቡን አዲስ አድርጎ ፈጥሮ በዕውቀት ለማሳደግ የማኅበረ ሰብ ጥናት መሐንዲሶች በሙሉ ኃይልና ፍሳጎት በመስራት በየአንዳንዱ ዜጋ የዴሞክራሲን ችግኝ መትከል ይኖርባቸዋል በአሁኑ ግዜ የዴሞክራሲ ችግኝ የሚፋፋበትን የሕሊና ማሳ አለስልሶ በቅድሚያ ማዘጋጀት ግድ ይሳል ማኅበረ ሰቡን በዴሞክራሲ አንጾ በዕውቀት ገንብቶ የመብቱ ጌታ ለማድረግ በእውነተኛው ሳይንሳዊ እምርታዎች ማራመድ የምሁራንና የአገር ወዳዶች ቀዳሚ ተግባር ነው ቀደም ብሎ አገር ወዳዶች ሕዝቡን ለመብቱ እንዲንቀሳቀስ መገፋፋትን ዓይነተኛ ዓላማ አድርገው የተንቀሳቀሱ ብዙ መሰናክል እየገጠማቸው እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ እንደ ታገሉት አሁንም ለሕዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ቆመናል የሚሉ ሁሉ ተስፋ ሳይቆርጡ በመታገል በአድኅሮት ኃይላት ላይ በመራመድ ሠፊውን ሕዝብ በሥልጣን ዙፋን ላይ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል የዴሞክራሲ ጽንሰ ሃሳቦች ሁሉንም እኩል የሚያስተናግድና የሚያሳትፍ የሁሉንም መብት የሚያስከብር በመሆኑ ቢያንስ ቢያንስ ስብዕናን ለማወቅ ይርዳል። ወደ ፊት ግን የትምህርቱ አሰጣጥ ዘዴ ሁለመናን አያይዞ በመገጣጠም ኅብረታዊ ኃይልን በሚገነባ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባዋል በዚህ በኛው ምዕተ ዓመት መገባደጃ አስፈላጊ ያልሆኑ የወጣቶችን አእምሮ የሚበክሉ መርዛም ስብከቶች ተነዝተዋል ከአገር ወዳድነት ይልቅ ያገር ጠሳትነትን ከኀብረት ይልቅ መነጣጠልን በራስ ታሪክና ነፃነት ከመመካት ይልቅ በባዕዳን ታሪክ መመካት የቅኝ ገዥን ታሪክ እንደራስ ታሪክ አድርጎ መውሰድ የመሳሰሉትን የሚያስተምሩ አንዳንድ ጎጠኛ ባንዳ መምህራን መከሰታቸው አልቀረም እነዚያ በሬ ወለደ ታሪክ የሚያስተምሩ ወደ ጥፋት የሚመሩ በማኅበረ ሰቡ የተናቁ ጉድለት ያለባቸው ናቸው ያን በጋርዮሽ የኖረ ማኅበረ ሰብን የተበቀልን እየመሰላቸው ማንኛውንም እያጣመሙና እያወላገዱ በማስተማር የውጣቶችን አእምሮ በመጥፎ የቀረጹ አያሌ ናቸው በተለይም በውጭ አገር ሚሲዮን ትምህርት ቤት የሚሰጠው ትምህርት በጎሣና ነገድ ከፋፋይ ነው ወጣቱ ትውልድ ነባሩን ሥርዓተ ትምህርት መንደርደሪያ ካላደረገ በስተቀር የአገር ፍቅር ስሜት ሊኖረው አይችልም። እንግዲህ አፍሪቃዊ ምሁር ማለት አፍሪቃን በጎሣና በቋንቋ ከመሸንሸን አልፎ ዓይኖቹ በአፍሪቃ ጠላቶች ላይ ያተኩራል ማለት ነው በአጠቃላይ አፍሪቃዊ ምሁር አፍሪቃ እንዳትጠፋ ሕልውናዋን ይዛ እንድትኖር ሕሊናውን አስፍቶ እነ ከዋሚ ንክሩማ አቅደውት የነበረውን ፓን አፍሪካኒዝም በአዲስ መልክና ቅርፅ አፍሪቃውያንን ለማዋቀር ይጥራል እንጂ አፍሪቃውያንን ያውም የአንድ አገር ዜጎችን በጎሣና ቋንቋ የሚከፋፍል ምሁር አይደለም በተለይም የጥቁር ዘር የማንነት መታወቂያ የሁለመናቸው መገኛ የታሪካቸው መነሻ የሆነች ኢትዮጵያን በጎሣና ቋንቋ የጎጥ መንግሥት ለማቋቋም የሚሯሯጡ ምሁራን ሳይሆኑ አእምሮአቸው የተዘጋ ከዳተኞች ናቸው ሐ የሃይማኖት መሪዎች የሃይማኖት መሪ በአግዚአብሔር ወኪልነቱ ለሁሉም ፍጡር እንደፀሐይ እኩል ብርሃን የሚሰጥ እንደ ኦክስጂን አየር ለሁሉም እኩል የሕይወት እስትንፋስ የሚሰጥ እንደ መሬት ሁሉን እኩል የሚሸከም ለሁሉም ያለ አድልዎ እኩል የሚያስብ ማለት ነው። እንግዲህ ጨቋኝነትና በዝባዥነት ከመንግሥት ወደ መንግሥት እየተወራረሰ የተላለፈው የጭቆናን የብዝበዛን ሥርዓት ዛሬ ደግሞ ለወያኔ ተላልፎለት በከፋ መልኩ በመቀጠሉ የግፍን ድርጊት ለማስወገድ አገር ወዳዶች በቆራጥነት ታጥቀው በመነሳት ማንኛውንም ስብዕና የሚጎዱ ነገሮችን ከሥሩ ነቅሎ በመጣል ሕዝቡን አርነት ለማውጣት ከፍተኛ ጥ«ት ሊያደርጉ ይገባቸዋል ምሁራን የሕዝብ ውክልና ኖራቸው አልኖራቸው ለፍትሕና ለትክክለኛ ሕዝባዊ ሥርዓት በጥብቅና ለመቆም ሞያቸው ያስገድዳቸዋል ምሁር ማለት በንቃቱ ሳይ ገደብ የማያደርግ እንደ ብርሃን ለሁሉም የሚያበራ እንደ አየር ርክ እኩል እስትንፋስ የሚሰጥ ተራራ የማይጋርደው ውቅያኖስ የማይገታው የጠመንጃ አፈሙዝ የማይለጉመው በመሆኑ ለመላው ሕዝብ መብት የመቆም ኃላፊነት አለበት አንድ ሰው ተምሮ የሊቅነትና የሊቀ ሊቃውንትነት ማስትሬትና ዶክትሬት ከፍተኛ የፍልስፍና ማዕረግ እያለው ዕውቀቱን ለተገቢው ሥራ ለሠፊው ሕዝብ ጥቅም ካላዋለው በንቃቱ ሳይ ገደብ በማድረግ የምሁርነት ማዕረጉን በድክመቱ ገፈፈው ማለት ነው በሌላ አባባል ጥይት የሌለው ጠመንጃ ሳይሆን በምሁርነት ያገኘው ዕውቀቱ ጠብመንጃ ልሳኑ ጥይት ሁኖ ሰብአዊ አውሬዎችን መምታት ይገባዋል። እውነተኛ ምሁር የአእምሮ ኃይል አለውና የሕዝብን ሕይወት ይፈጥራል ምሁር ማለት እኮ ከአውሬነት ወይም ከእንሰሳት የተላቀቀ ዓዋቂ ልዕለ አዕምሮ ያለው አስተዋይ ማለት ነው ሕዝብ እየተቆላ እንደ ተልባ ሲንጫጫ ድምፅ ያሳሰማ ምሁር ከወንጀለኞች ጋር እንደ ተባበረ ተቆጥሮ የምሁርነት ማዕረጉን ያሳጣዋል የምሁር ዓይኖች የሚያተኩሩት የግፍ ድርጊት በሚፈጸምባቸው በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ጉዳዮች አድልዎ በሚደረጉባቸው ላይ የማያተኩር ከሆነ ማኅበረ ሰቡ ካብ አይገባ ድንጋይ ብሎ ይጥለዋል ምሁር ደንቆሮውን ጨለማ አስወግዶ እንደ ፀሐይ ለሁሉም እኩል ብርሃን ሰጭ መሆን ነው ያለበት። ምሁር በምሁርነት ግዴታዎቹ መሠረት እውነትንና ታማኝነትን እኩልነትንና ወንድማማችነትን ፍቅርንና ቸርነትን ሰላምንና ርኅራጌን ነፃነትንና በራስ መመካትን የመሳሰሉትን በሕዝብ ሕሌና ዘርቶ መብትን አምርቶ ማስታቀፍ ከተግባሮቹ ዋነኛው መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም ለኢትዮጵያ ምሁራን የምመኝላቸው በአንዳንድ አገሮች የተከሰቱ እውነተኛ ምሁራን የደንቆሮውን ጨለማ ሠራዊት ጎሰኝነትንና ዘረኝነትን ክፋትና ጨካኔን ቅንዓትንና ምቀኝነትን ማን አህሎኝነትንና ከማን አንሼነትን ትዕቢትንና ምቀኝነትን ለባዕዳን አጎብዳጅነትንና ሎሌነትን ልክስክስንነትንና ወራዳነትን በቋንቋና በሃይማኖት ከፋፋይነትን ተዋግተው ድል አድርገው ከአገራቸው እንደ አስወጡት እንዲሁም የኢትዮጵያ ምሁራን እነዚህኑ የተጠቀሱትን የድንቁርና ሠራዊት ታግለው ከአገራቸው አስወጥተው ሕዝብን ነፃ እንዲያደርጉ ነው ቋንቋ የሃሳብ መግለጫ መሣርያ እንጂ የዘር መለያ ባለመሆኑ መሬትም የይዞታ እንጂ በዘር የመለያያ አይደለም አገርም የተለያዩ ብሔረ ሰቦችና ነገዶች የሚኖሩባት መሆኑን ዝቅተኛ ዕውቀት ያላቸው ሁሉ የሚያውቁት ሲሆን በራሳቸው ምንነት የማይተማመኑ የማኅበራዊ ኑሮ ራዕይ የሌላቸው አንድን ሕዝብ በዘርና ጎሣ የሚለያዩትን ግብዞች ማንነታቸውን የሚያዩበት መስታወት ምሁራን በተለይ የታሪክ ሰዎች መስጠት ይገባቸዋል ይህ ካልሆነ ምንግዜም ሰላምና ፀጥታ ሊኖር አይችልም በመንግሥት ሥልጣን ሳይ የነበሩ መሪዎችም ሆነ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች የዘር ማምለኪያ ጣዖቶች አይደሉም ዮሐንስ ሲነሳ ትግሬው ቴዎድሮስ ሲነሳ ጎንደሬው ምኒልክና ኃይለ ሥሳሴ ሲነሱ ሸዋ ኮምዩኒስት ሲነሳ ኢሠፓ ወያኔ ሲነሳ ትግሬው ኦነግ ሲነሳ ኦሮሞው መላው አማራ ሲነሳ አማራው ካኮረፈ አንድነትና ሰላም ሊኖር አይችልም የመንግሥትና የፖለቲካ ድርጀቶች መሪዎችን ከሕዝብ ነጥሎ ማዬት የተገባ ነው ለምሳሌ ያለፉት ንግሥታት በዙሪያቸው ለተኮለኮሉ መኳንንትና ሎሌዎቻቸው እን ለሕዝብ ደንታ አልነበራቸውም እንዲሁም ወያኔ ለአባሎቹ እንጂ ለሠፊው ሕዝብ የሰጠው ጥቅም የለም። ፍ ነውናኖ ጉድሎቶችን ማሟላት ሕዝብ ሰብአዊ ፍላጎቱን የሚያሟላበት ንቃት መስጠት ሕይወት የሚጠይቀውን ሁሉ እንደ አስፈላጊነቱ ማሳካት በድብብቆሽና በመላ ምት የሌለ ነገር አስመስሎ በማቅረብ የማኅበረ ሰቡን ክብር የሚጎዱ እርካሽ ነገሮችን እንዲወርስ ያደረጉትን ማጋለጥ ሲሆን ከሁሉም ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ የዕውቀት ጽንሰ ሐሳቦችን በማስፋፋት ሁሉም ነገር ሚዛናዊ እንዲሆን ማድረግ ነው የምሁር ዕውቀት ሒደቱን ጨርሶ ተሰናብቷል ካልተባለ በስተቀር ለእኔ እንደሚገባኝ ምሁር ማለት የዕውቀት ሠራዊትን አሰልፎ በድንቁርና ላይ የሚዘምት እንደ ግዜው ሁኔታ ዘዴውንና ስልቱን እየለዋወጠ የድንቁርና ሠራዊትን ጎሰኝነትን ዘረኛነትን ወገናዊነትን ዘራፊነትን ስግብግብነትን አድላዊነትን የሚያጠፋ ነው ሌላው የምሁር ሚና የዕውቀት ብርሃን እንዲያይ የተዘጋውን የገጠሩን ሕዝብ አእምሮ ከፍቶ የዕውቀት ጭላንጭል ማስገባት ሲሆን ብርሃን በመርፌ ቀዳዳ የሚያዬውን የከተማ ኗሪንም ብርሃን ማያውን ቀዳዳ በማስፋት የተበለጠበትን የዓለም ሥልጣኔ እንዲያይ ማድረግ ነው ቁጥራቸውን ወደ ምሁር ያስጠጉ አንዳድ ሰዎች ተምረው ባገኙት ዕውቀት ስለአልሠሩበት አእምሮአቸው ዝነ ስለሻገተ የዕውቀት መተላለፊያ የደም ሥሮችን ስንፍናቸው አጥብቦ ስለዘጋው እውነተኛ በተግባር ላይ ያሉ ምሁር በቀዶ ጥገና ጥቀርሻውን ጠርጎ አውጥቶ የዕውቀት ኃይል እንዲንሸራሸር ማድረግ የተገባ ነው በዛሬይቱ ዓለም የሚገኙ ምሁራን በሳይንስና ቴክኖሎጅ ምርምር ተራምደው የአሉበት ዓለም ጠባቸው ሌላ ዓለም ፍለጋ ሰማዬ ሰማያትን በሚዳስሱበት ሳይንሳዊ ዘመን የኢትዮጵያ ምሁራን በደንቆሮው ጨለማ ውስጥ ዕውር ድንብራቸውን በጎሣ ፖለቲካ ይተራመሳሉ የሚል ከመስማት የበለጠ አስደንጋጭና አስፈሪ ከቶ ምንም ነገር ሊኖር አይችልም ለምሁር ጎሣ ምኑ ነው። አገራችን ኢትዮጵያን በርስ በርስ ጦርነት የማገዳት ለረኃብና በሽታ አሳልፎ የሰጣት ዕድገቷን ቀጭቶ ወደ ኋላ የጎተታት በድንቁርና ልጓም የሚጎተቱት ተማርን የሚሉ ጠላት የፈለፈሳቸው ጠባብ ጎሰኞች ናቸው እነዚሁ ጠባብ ጎሰኞች በድንቁርና የሚገፋውን ስሜታችውን እርግፍ አድርገው ካልተው የእርስ በርስ ብጥብጥ ረኃብና በሽታ እያገረሹ ይቀጥላሉ ሌላው የኢትዮጵያዊነት ትልቁ ማስረጃ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ አገር አንድ ሕዝብ ሁኖ ሲወርድ ሲዋረድ ተያይዞ የመጣ መሆኑን መቀበልና ማመን መቻል ነው የሕዝብ ሰብአዊ መብት እየተረገጠና ሕዝብ የደም እምባ እያለቀሰ እያለ ያልተከላከለ ምሁር በኃላፊነት ከመጠየቅ የሚያመልጥ ብቻ ሳይሆን በታሪክም በትውልድም ተወቃሽ ያደርገዋል ያር ያ። የኢትዮጵያ ሕዝቦች ችግር በጠንካራ የተባበረ ክንድ ይፈታል ስለ ኮሚቲው ታጋይ ከል አስናቀ እንግዳ አብደል ቃድር እያል ሰው ካርቱም ሰኔ ቀን ዓም ለኮሞዶር ጣሰው ደስታ ለአቶ ደረጀ ደሬሣ ዶር አደም አብደላ ከዚህ በፊት በጽሑፍም በቃልም ያቀረብነውን እንጠቅሳለን እንደሚታወቀው ቀደም ሲል ይህ የአሁኑ ድርጅታችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ኢብዴግ በሚል ስም ተመስርቶ የቆየ ቢሆንም ድርጅቱን ማስፋትና የማንኛውም አገር ወዳድና ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን በነበረው አጠቃሳይ ስምምነትና ዕምነት በ ዓም የኢብዲግ አባላት የነበሩ ኮል አለማየሁ አስፋውና ሻለቃ ዮሴፍ ያዘው በአውሮጳና አሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በድርጅቱ በትግሉ እንዲሳተፉና ለሀገራቸው ነፃነት የጋራ ትግል እንዲያደርጉ ጥሪ በማድረጋቸው «ፕሮግራሙ ተሻሽሎ ስሙም ከተለወጠ እንሳተፋለን» ስለአሉ ለመታገልና ለዲሞክራሲያዊው ትግል አስተዋጽዖ ለማድረግ ፍላጎት ያላቸው ኢትዮጵያውያን እናንተም ጭምር ባሳሰቡት መሠረት ከብዙ ውጣ ውረድና ጥረት በኋላ የኢብዴግን ፕሮግራም መነሻ በማድረግ «የኢትዮጵያ ሕዝቦች ዲሞክራቲክ አንድነት» በሚል መመሪያ መንደርደሪያ ፕሮግራሙ ተዘጋጅቶ ተልኮልን በአካባቢው የምንገኝ አባሳት በሰፊው ተወያይተንበት የሚጨመረውንና የሚቀነሰውን በመጥቀስ በመጨረሻ ጊዜ ታትሞ እንዲመጣልን መሳላካችን ይታወሳል ፕሮግራሙም በመጨረሻ መልኩ ታትሞ በአስቸኳይ እንዲላክልንና የድርጅቱም ዋነኛ የትግል መስመሩ ትጥቅ ትግል መሆን እንዳለበት ለአንዳንድ ጉዳዩን አያምኑበትም ለተባሉ አባላት በውይይት እንዲያሳምኑ በተጨማሪም በአገር ቤት ድርጅቱ ሀ ብሎ ሲመሠረት የመሠረቱና በስሙም ለሚታገሉ ታጋይ አርበኞች አስፈላጊውን እርዳታ የሚገኝበትን ጥረት እንዲደረግ በማለት ከጊዚያዊ አመራር ኮሚቲ ሁለት አባላትን ወክለን ልከን የነበረ መሆኑ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በሥልጣኔ ወደ ኋላ መቅረትና መበለጥ የሚያስቡ ብዙ አገር ወዳዶች ነበሩ ኮሎኔል እምሩ ግን ያበዛው ነበር የሚገርመው በዓፄ ኃይለ ሥሳሴ ዘመነ መንግሥት ዓመት በደርግ ዓመት በድምሩ ዓመት መሆኑ ነው በወህኒ ቤት ዓመት አብረን በነበርንበት ግዜ ከወህኒ ቤትም ከወጣን በኋላም ሁልግዜ የሚያነሳቸው ነጥቦች ኢትዮጵያን ከኋላ ቀርነት ለማላቀቅ ምን መደረግ አለበት። በኢትዮጵያ አገር ወዳዶች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኢአወዴድ እና በኋላም በኢትዮጵያ ሕባዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ድርድት ኢሕዲአአብረን በትግል ሳይ በነበርንበት ግዚያትና አሁንም በስደት በአለንበት በተገናፔን ቁጥር የሚያነሳልኝ ኮሎኔል እምሩ ከሚያነሳቸው ነጥቦች የተለየ አይደለም ኢትዮጵያ በጎሣና ቋንቋ መከፋፈሏ የኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠል በእርስ በርስ ውጊያ ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ በሕዝብ ላይ ረኃብና በሽታ የሚፈራረቁበት በመሆኑ እያሳዘነው ሌት ከቀን ከመተከዝ ያቋረጠበት ግዜ የለም። ሌላው የአያል ሰውን የሕሌና እረፍት የነሳው በምዕራባ ውያን ቡራኬ ሥልጣን የያዘው ወያኔ ያወጣው ሕገ መንግሥት ነው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ብሎ ራሱን የሚጠራ ቡድን አንድ ወጥ አስተሳሰብና አመለካከት የነበረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በጎሣና ቋንቋ ከፋፍሎ የአንድነት ኃይልን በማዳከሙ ከመጠን በላይ እየ ከነከነው የወያኔውን የጎሣ መግሥት ለማስወገድ የሚቻልበትን ዘዴ ከመፈለግ የቦዘነበት ግዜ ያለ አይመስለኝም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት ኢድኃቅ እና በኢትዮጵያ የሰላምና የዴሞክራሲ አማራጭ ኃይሎች አባል በመሆን ብዙ ጥሯል። አሁንም ተስፋ ባለ መቁረጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፌዴራል ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲን ሕብረ ሕዝብ ሲቋቋም ከመሥራቾቹ አንዱ በመሆን ያለ ዕረፍት በትጋት በመሥራት ላይ ነው ይህችንአጭርማስታወሻእንድፅፍያስገደደኝከአያልሰው ጋር ተገናኝተን ስለ አገራችን ጉዳይ በምንወያይበት ግዚያት ሁሉ አጥንት ሰብሮ የሚገባ አሳዛኝ ኃይለ ቃል እየወረወረ በእሳት ላይ ቤንዚን ማለት ነው መንፈሴን እያሻቀለው በሕዝብ ሳይ ክፉ ድርጊት ሲፈጸም እየሰማሁ መታገስ ከማልችልበት ሁኔታ ላሳይ እየደረስኩ እራሴን ለመሷይትነት ያዘጋጀሁት ግዜ ስለ ነበር ነው በእርግጥምበተገንጣዮቹበጎሣድርጅቶችበወያኔናሻዕቢያ በደርግ መካከል በሚደረግ ውጊያ በሕዝብ ላይ ይፈጽሙት የነበረው አረመኔአዊ የሚዘገንን ጨካኝ ድርጊት ወኔው ላልበረደ እንደ አያል ሰው ላለ ወጣት ቀርቶ ወኔው ለበረደ እንደ እኔ ያለውን ሽማግሌ መንፈስ ሳይቀር እየገሸለጠ የሚቀሰቅስ ነበር አያል ሰው ባህሉን አክባሪ ጠፍ ያለ የማይልከሰከስ በጭዋነቱ አገሩን የሚወክል መኮንን ነው ወደፊት ኢትዮጵያን ከሚገነቡት አንዱ እንደሚሆን አልጠራጠርም። ግራና ቀኝ የሚያይ አስተዋይ ነው ኛ ተገንጣይ ድርጅቶች የትግራዩ ወያኔና የኤርትራው ሻዕቢያ ያሰለፉትን ሠራዊት በስልትና ዘዴ ሳይመሩ የሰው ቁጠባ በሌለበት ከተጠናከረ ምሽግ ውስጥ እያስገቡ የጥይት መቆስቆሻ አድርገው እየማገዱ በግፍ በማስጨፍጨፋቸው ኛበእርስበርስጦርነት ሠላማዩውን ሕዝብ በጦርነት ስለ አሰቃዩት ሕይወቱን ለማዳን ሦስት ሚሊዮን ያህል ሕዝብ ወደ ጎረቤት አገሮች ተሰድዶ ከብርቱ ችግር ላይ ስለ ጣሉት ኛ በጦርነትናበድርትጉዳትየደረሰበትንየምሥራቅትግራይ ሕዝብ ከቦታው አፈናቅለው የዕርዳታ መለመኛ ለማድረግ ወደ ሱዳን አግተልትለው ወስደው ለጤና ተስማሚ ካልሆነ ወባና ልዩ ልዩ የበረሃ በሺታ ከሚፈላበት ውድ ኮሊና ውድ ሺፈፎ ከተባለው ቦታ አስፍረው ከሰላሳ ሺህ በሳይ የሚሆን ሕዝብ ረግፎ የሱዳን መሬት ማዳበሪያ ሁነው በመቅረታቸው ኛበዘመናዊባሪያፍንገሳየተሰማራውየእሥራኤልየስለሳ ክፍል የኢትዮጵያን አይነተኛ ዜጎችነገደ ፈሳሺያን ወደ ቅድስቲቱ አገር እየሩሳሌም ትገባላችሁ እየተባሉ በስነ ልቦና ሰለባ ሺህወችን በአንድ ግዜ አግተልትለው ወደ ሱዳን አስገብተው ዶካ ኡምራኩባ ከተባለው ቦታ አስፍረው በምግብ እጥረትና በልዩ ልዩ በሺታዎች በተለይም በመረተ በርሜል ውኃ እያደሉ አንጀታቸው እየተበጣጠሰ ከ ሺህ በላይ የሚሆኑ በአሳዛኝ ሁኔታ በማለቃቸውና ተቆርቋሪ የሌለው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከንቱ በመጥፋቱ ኛበ ዓም ደርግ በታሪክ ያልተሰማ በየትኛውም ዓለም ክፍል ያልተደረገ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ብሎም ለሕዝብ መሠረታዊ መብቶች ጥያቄ የወጣውን ሠላማዊ ሠልፈኛ በጥይት ገድሎ ሬሳ በገንዘብ ለወላጆች በመሸጡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትና የዓለም ኀብረተ ሰብ ዘግናኙንና አሰቃቂውን ድርጊት ባለ ማውገዙ ኢትዮጵያ ደጋፊ የሌላት ብቸኛ አገር መሆኗ እጅግ ያሳዝነዋል ኛ ኢትዮጵያዊያን ወጣት ልጅ አገረዶች በአገሪቱ በተፈጠረው ቀውስ ከችግር ላይ በመውደቃቸው ቤተሰባቸውን ለመርዳት የባህልና የእምነት ግንኙነት ወደ ሌላቸው ወደ ዓረብ አዝር ሒደው ለመሥራት ከግንባራቸው ሳይ የመስቀል ምልክት ውቅራት ያሳቸው ምልክቱን ለማጥፋት በአሲድ ሲፈገፍጉ ብዙዎች መልካቸውን አጥፍተዋል በዓረብ አገር የመስቀል ምልክት ያለው ስለ ማያስፈልግ ሒደው በግርድና ሲያገለግሉ አንዳንዶቹ ክብረ ንጽህናቸውን በማስገደድ እየተደፈሩ አንዳንዶቹም በጭካኔ እየተገደዱ በመጣሳቸው ኢትዮጵያ ያፈራቻቸውን አገር ወዳድ ትውልድ አባቱ የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብረት ኢዴኅ ልጁ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ኢሕአፓ እያለ ደርግ ያለ ፍትሕ በመደዳ ከጨፈጨፋቸው ያመለጡ ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን ተሰድደው ድርጅት አቋቁመው ትግል የጀመሩትን አገር ወዳድ ድርጅቶች በጠላትነት እየተመለከቱ ለተገንጣይ የጎሳ ድርጅቶች ለወያኔና ሻዕቢያ ግን የምዕራቡ ዓለም በማናቸውም አቅርቦት እየ ረዳ ለአገር ወዳድ ድርጅቶች ግን ምንም ዓይነት እርዳታ ባለ መስጠቱ በኢትዮጵያ ላይ የውጭውም የውስጡም በጠሳትነት የተሰለፉበት ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ በመሆኑ ኢትዮጵያዊያን አዢ ውዳዶች በአገር ውስጥ በጭፍን ብሔርተኛው በደርግ እና በተገንጣይ የጎሣ ድርጅቶች በመዋከባቸው። በውጭ አገር በምዕራባዊያን ኢምቴሪያሊስት ኃይሎች ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ታጥቀው በተነሱ ከባድ ተጽዕኖ ተደርጎ እንዳይንቀሳቀሱ በመደረጉ ከሁሉም በላይ የሚያስገርገመውና የሚያስደንቀው ጭፍኑ ብሔርተኛ ደርግ ተገንጣዮችን ወያኔንና ሻዕቢያን የውጭ ኃይል ከኋላ ሁኖ የሚገፋቸው ያሰለፋቸው መሆኑን ሳያውቅ የትም አይደርሱ እያለ በመናቅ በቸልታው ኮትኩቶ እያሳደገ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚያስቡትንና የሚቆረቆሩትን አገር ወዳዶች በመደዳ እየጨፈጠፈ አገሪቱን ያለ ተቆርቋሪ ሁነኛ በማስቀረቱ አያል ሰውን ያንገበግበው ነበር ወጣቱመኮንንአያልሰውለአገሩአርቆየሚያስብትልቅሰው ነው በመንግሥቱ ኃማርያም ሳይ በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በተገደሉት ጀኔራል መኮንኖች ለብዙ ቀን አዘንተኛ ሁኖ ነበር ዘመዶቹን ሲረዳ አዝኖ የማያውቀው ለመጀመሪያ ግዜ በጀኔራሎቹ መገደል ግን መሪር አዘን ተሰምቶት ነበር። ምክንያቱም ኢትዮጵያ ምርጥ አገር ወዳድ ልጆቿን አጣች በሚል ነውበተለይም በእንግሊዝ የጦር አካዳሚ አንደኛ ሁኖ የወጣው ጀኔራል ተስፋዬ ትርፌን የመሰለ ልዕለ አእምሮ የነበረውን ማጣት ለኢትዮጵያ ትልቅ ጉዳት ነው እያለ እስከ ዛሬ እንዳዘነ ነው አያል ሰው ደስዬ የሰው ቃርሚያ አይደለም አይነተኛ ኢትዮጵያዊ ነው። በዚህ ስሌት ካሥሩ ሰዎች መካከል አንዱ ክፉ አድራጊ ነው ማለት ይሆናል መቼም ሞራል የሌለው ሰው ኃይል ካላስገደደው በስተቀር የግል ጥቅም ከማፈንፈን አይገታም ወራዳ ልክስክስ ሰው ሕግም ሆነ ስብዕና መጥፎ ነገር ከማድረግ አያግደውም በረዶ በበጋ ዝናብ በመክር እንዳይገባ እንዲሁም ለሰነፍ ክብር አይገባውም ምሳ እንዳለው ሰሎሞን በምሳሌው እንደነዚህ ያሉትን ሰዎች ማኅበረ ሰቡ በመጥፎ ምግባራቸው እንዲያፍሩ ማድረግ አለበት በእንፃሩ ደግሞ እንደ ዶክተር አንድ ውጅ ደላ ሻሽ ዊት ፈዬ ጋ ዓለም ሙላውና ሻምበል ሳሙዔል ጥሩነህ ላሉት ቅንና ደግ ሰዎች ደግሞ ለሚያበረክቱት ቅን አገልግሎት ማኅበረ ሰቡ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል እነዚህ አገር ወዳዶች ዶክተር አንድ ዓለምና ሻምበል ሣሙዔል እንዳደረጉት ሁሉም ቢረዳዳ ማንኛውንም ችግር ማስወገድ በተቻለ ነበር።