Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እኔ ከአንድ ኢጣሊያ ከሠራው ሕንፃ ውስጥ ነው የምንኖረው የሻለቃ አዛኙ ጌታሁን ከፎቁ ላይ እኔ ምድር ቤት ከጽሕፈት ቤቱ ጎን ነበርኩ እረ ለመሆኑ ጌታሁን እኔን ለመግደል ቦምብ ያስጣለብኝ ምገ አደረገኝ ብሎ ነው። የሚጠብቁትን ሕዝብ ባይዘርፉ ኖሮ ወንጀለኛ ሆነው አይከሰሱም ነበር ማንኛውም ሰው ጥፋት ሲሰራ የሚከሰው የራሱ ወንጀል ነው ወንጀል ሲሠራ የሚያዩ ሰዎች ደግሞ ለማጋለጥ ኃሳፊነትና የሞራል ግዴታ አለባቸው አንድ ሥርዓት የሚበላሽ ከሳይ ባመራር ላይ ያሉ ባለሥልጣናት በጥፋት ላይ ሲሰማሩ ነው የዓፄ ኃይለ ለፊ መግሥት ስለ ቅንቅኖችም ሆነ ነቀዞች ግድ አልነበረውም ብረት የሚያፈራ ለመንግሥት አይተኮርበትም ነበር አደገኛ አይደለም እየተባለ እነዚሁ በአስተዳደርና በዳኝነት ሥልጣን ላይ ያለውን ግፈኛ ጨቋኝ መንግሥት ለማንበርከክ ሁኔታዎችን ማሟላት ተገቢና አስፈላጊም ነበር ይህ ባለመሆኑ ከዝግጅት ጉድለት የተነሳ በይድረስ ይድረስ በስሜት የተጋፈጠው ትውልድ ለውጥ ሊያመጣ አልቻለም እነዚያ የለውጥ ሕልም የነበራቸው ጥቂት ወጣቶች የሕዝብን ስሜት ነካክተው በማነ ሳሳት ያደረጉት ሙከራ ከባል በፊት ልጅ ይስጠኝ ሆነና ሕልማቸው እውን ሳይሆን ቀረ ሸክም የማይከብደውን ሕዝብ ከሁሉ አስቀድሞ ምን አንደተሸከመ የማያውቅ በመሆኑ የተሸከመው ነፍስ የሌለው የሰው ቅርፅ ያለው ድንጊያ ጀርባውን እንደአጎበጠው ትከሻውን እንዳቆሰለው ቁስል ፈዋሽ መድኃኒት እንዲፈልግ መሔጃ መንገድ ማሳዬት ይገባ ነበር። ሕዝብ ሰምቶ የሚቀበለው ዓይቶ የሚፈጽመው በድርጊት የተካሔደበትን ግፍ በዓይኑ ያየውን ሕገ ወጥ ድርጊት እያነፃፀሩ ሲነግሩት ብቻ ነው። ወይንስ ከብዙ ከበርቴ በላተኞች ስለ አሉ በየፊናው የሠራተኛውን ጉልበት ሲመጡት መቋቋም እየተሳነው በጉስቁልና ኑሮ የሚሰቃዬው እጅግ ብዙ ነው። የጥፋት ኃይሎች ሁል ግዜ የሚታያቸው አጥፍቶ የሚጠፉበት ጎዳና ነው። እነዚያው ከሕሊናቸው የተሰናበቱ በአጋጣሚ መንግሥታዊ ሥልጣንን የያዙ ያስተላለፉአቸው ግዙፍ መመሪያዎች ከራሳቸው የሥልጣን አኳያ እንጅ ከሰፊው ሕዝብ ጥቅም አንፃር ሲታይ ጥልቀት በሌለው ፖለቲካዊ ቴወሪ መራራውን በጣፋጭ ሸፍኖ በሽንግላ ዋንጫ ለመጋት ነው። ታማኝነቱም ለአገሩ እንጂ ለጨቋኝ የገዥ መደቦች ወይም ለበዝባዥ ከበርቲዎች አይሆንም ሠራተኛው ሲያምፅ የሚያዘው አዝር እንጂ ሌላ ባለሥልጣን አያዘውም ለአገሩ ክብርና ነፃነት ግን በግንባር ቀደም ተሠላፊ ሠራተኛው ኃይል ነው። ስግብግብ ባለ ሥልጣኖች ኃጢአታቸውን የሚያበዙት በቆሳቁሶች ሳይ ወሳኝ ሚና በመጫወት ብቻ ሳይሆን ማኅበረ ሰቡንም ደኅንነት ይጠብቃል ሠራተኛው መብቱ ሲጓደልበት ዓመፅ አያደርግም ብሎ ማመን ሞኝነት ነው። ይጫጫልም ጠቢብ በጥበቡ አይመካ ኃይልም በኃይሉ አይመካ ባለጠጋም በብልፅግናው አይመካ ነገር ግን የሚመካ ምህረትና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ በሚያደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ እንዚህ ናቸው ኤር ፀ ይላልና እግዚአብሔር ፈጣሪያችን ጠባቂያችን አለኝታችን መመኪያችን ጋሻችን መከታችንና አዳኛችን ነው። መንግሥት ማለትስ ምን ማለት ነው። በአሁኑ ወቅት ደግሞ ባለ ጠመንጃ ወይስ መሬት የለሹ የሚረገጠው ሠፊው ሕዝብ።
ሸክም የማይከብደው ሕዝብ በአስናቀ እንግዳ ኮሎኔል ዋሽንግቶን ዲ ሲ መጋቢት ዓ ም ማውጫ መቅድም መግቢያ ክፍል አንድ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ምዕራፍ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥታዊ አስተዳደር ምዕራፍ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ጠንካራና ደካማ ጎኖች ምዕራፍ የሥልጣን ብልግናና ንቅዘት ምዕራፍ ሹመት ሽልማት በስብቀት ፍርድ በትዕዛዝ ምዕራፍ የአዲስ አበባ ዓለም በቃኝ ወህኒ ቤት ትዝታዎች ምዕራፍ የኢትዮጵያ ጎሳዎች ኅብረታዊ መሠረት ምዕራፍ ። ፀሐይ ለሁሉም እኩል ፍትሐዊ ብያኔ ትሰጣለች ነፃነትም በአየር ኦክስጂን ይመሰሳል አየር ለሁሉም እኩል እስትንፋሺ የሕይወት ምግብ እንደሚሰጥ እንዲሁም ነፃነት ለሁሉም እኩል ኑሮ እኩል ሥራ እኩል የዜግነት መብት ይሰጣል እንዲሁም የመናገርና የመጻፍ የመሰብሰብና የመቃወም መብቶች በመሣሪያና በባለሥልጣን ድንጋጌ የማይታገዱ ተፈጥሮአዊ መብቶች ናቸው ይሁን እንጂ ሌላ ፍጡርና ሌላ ዓለም ካልተፈጠረ በቀር አሮጌው ዓለም የጥቂት አጭበርባሪዎችና መልቲዎች መኖሪያ ናት በዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግስት ዴሞክራሲ ለባለ ሥልጣን ጥቅም ብቻ የተከለለ ሲሆን በደርግ ደግሞ ዴሞክራሲ በጥይት ቆሰለች በወያኔ ዘመነ መንግሥት በዘር ልዩነት በጎሣ ዱሳ መገደሏ በየምዕራፎቹ ተገልሷል ነፃነት ያለ ሕግ ሕግ ያለ ነፃነት ሕይወት ፈፅሞ የሳቸውም እንዲሁም ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቶቹ ተጠብቀውለት በሕግ ጥሳ ስር በሰላምና ፀጥታ በተደላደለ ኑሮ ነፃ ሁኖ ካልኖረ እንዳአለ አይቆጠርም ስለዚህም ነው ብዙ አገር ወዳዶች ሕግ ከሌለ ነፃነት የለም ብለው ሕግን ለማስከበር መሷይት ሲከፍሉ የኖሩት የግፍ ድርጊቶች ክዓፄ ኃይለ ሥላሴ የዴሞክራሲ አፈና ጀምሮ እስከ ደርግ የመደዳ ጭፍጨፋ ቀይ ሽብር እና እስከ ወያኔው ማፍያዊ ሥርዓት እያፈኑ መግደልና ዝርፊያ ያለው በትክክል ቢጻፍ አያሌ መጻሕፍት ይወጣዋል ከልታማዋ ውድ ባለቤቴ ልባም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት ምሣሌ ብዙ ኢትዮጵያዊት ሴቶች ለቤተሰቦቻቸው መመኪና መኩሪያ ለባለቤታቸውም ቅን አስተሳሰብና የምኞቱም ተካፋይና ረዳት ከመሆን አልፈው እንደ እናት አፍቃሪ እንደ እሕት መካሪ ሆነው ይኖራሉ ከነዚያም ባለቤቴ አንዱዋ ናት። ዛሬ በእርጅናዬ አባቴ ብለው የሚንከባከቡኝ ልጆቼን የሞት ፍርድ ፈርጄባቸው ነበር ቀደም ብሎ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ ቆራጭ ፈላጭ መንግሥት በኋላም የደርግን የጭራቅ መንግሥት ለመቃወም ቆርጨ ስነሳ ዴሞክራሲ በታፈነበት ሰብአዊ መብት በተረገጠበት በግፋዊ አስተዳደር በችግር የጉስቁልና ኑሮ ከሚሰቃዩ ልጆቼም ሆኑ እኔ አለመኖራችንን ምርጫዬ አድርጌ ነበር በዓም አሁን በሕይወት ካለ ወዳጅ ጋር ከሐረር ወደ ድሬዳዋ በአንድ ጂፕ መኪና ስንሄድ ንጉሠ የአየር ኃይልን ትርዒት ለማዬት ድሬዳዋ መጥተዋል ሁኔታው አመች ከሆነ አስፈላጊ ርምጃ መወሰድ ያስፈልጋል የሚል ቃል ብሰነዝር ያ የማምነው ወዳጄ ሞትን ደፍረህ በእርሳቸው ላይ ርምጃ ብትወስድ ልጆችህን ይገድሏቸዋል ይህን ሃሳብህን ብትተወው ይሻላል ብሎ መከረኝ እኔም ቀጠል አድርጌ በግፋዊ አስተዳደር ውስጥ በመኖርና አለመኖር መካከል ልዩነት የለውም በአድሎአዊ ሥርዓት ታፍኖ ከመኖር አለመኖር ይመረጣል ብዬ መልቬለት ነበር ሆኖም ያሰብኩት ባለመሳካቱ ያ የፈራሁት ችግር ልጆቼንና ባለቤቴን ገርፎአቸዋል በዚህ ክህደትና ውስልትና በሞላበት ኛው ምዕተ ዓመት በእምነት ፀንቶ መቆም የታሳቅነትና የስብዕና መለኪያ በመሆኑ ወደር ለማይገኝላት ለታማቿና ለቆራጧ ውድ ባለቤቴ ወይዘሮ አበባ ንጉሜፄ ከጫማዋ በታች ዝቅ ብዬ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ሕዝብ እንዳስቃዩ እነርሱንም ደርግ አሰቃይቶአቸዋልበሕዝብ ሳይ ዳኝነት እንዳጓደሉ በነርሱም ላይ ደርግ ዳኝነት አጓድሎ ያለ ፍትሕ ገደላቸውበእስራትም አሰቃያቸው ያው እነርሱ በሕዝብ ላይ የፈጸሙት ግፍ በነርሱም ላይ ተመሳሳይ ተፈጽሟል መቸም የእግዚአብሔር ፍርድ ድንቅ ነው ዓፄ ኃይለ ሥላሴም መንግሥት ንጉሥ እንደመራቸው ባጠፉትም ሁሉ የጥፋት ንጉሥ ሁነው ተፈረጁ ኛ ልጅ ካሣ አፄ ቴዎድሮስየመስፍኑን የራስ አሊን ልጅ ወይዘሮ ተዋበችን እቴጌ አግብተው ከመስፍኑ ጋር በጋብቻ ተሳስረው ነበርበዚያን በመሳፍንቱ በብላ ተባሳ ዘመን ወታደሩ በየገበሬው ቤት ተሠሪ እየሆነ ሕዝቡን ከመጠን በላይ በማስቸገሩ የተማረረው ህዝብ ደንቢያ ጃንዳ ከተባለው ቦታ ተሰብስቦ ሲወያይ ያገው መፍትሔ የጎበዝ አለቃ መርጦ በመሾም ተሠሪን መቋቋም ከሚል ውሳኔ ላይ ደረሰ ልጅ ካሣን የጎበዝ አለቃ አድርጎ በመሾም ልጃቸውንም አብረው እንዲታገሉ በማድረጋቸው ልጅ ካሣም የሕዝብን ውሳኔ ተቀብለው ከመታገል በስተቀር ሌላ አማራጭ አልነበራቸውም ኛ አፄ ዮሐንስ ከሁሉም በሳይ ያገር ፍቅር እንደነበራቸው ግልጽ ነው መንፈሳዊነትን አጥባቂና አክራሪ በመሆናቸውም አንድ አገር አንድ ሃይማኖት የሚለው እምነታቸውም ለእገራቸው አንድነትና ሉዐላዊነት አስተማማኝነቱን በመረዳታቸው ይመስላል ለአገራቸው ክብርና ነፃነት እየዘመቱ ከውጭ ጠሳት ጋር ተዋግተዋል ዳሩ ግን አርቆ ካለማስተዋልና ከንቃት ጉድለት እንግሊዞችን እነ ጄኔራል ናፔየርን ከቀይ ባህር ጠረፍ ጀምሮ እየመሩ መቅደሳ ድረስ ወስደው ዓፄ ቴዎድሮስን እንዲወጉ በማድረጋቸውና ኢትዮጵያን በውጭ አገር ኃይል ማስደፈራቸው ትልቅ ስህተት ነበር እርሳቸውም የንጉሠ ነገሥታቱን ሥልጣን ተቀናቃኝ የነበሩት ንጉሥ ምኒልክ ከድተዋቸዋል። ሕዝብ ተብሎም አይጠራም በአሁኑ ግዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ የኔ ነው የሚለው ተስፋ ስለ ሌለው ከዜግነት ውጭተደርጓልምክንያቱም መብቱ በሕግ አይከበርለት ንብረቱ በሕግ አይጠበቅለት ከርስቱ ተነቅሏል ልጆቹን ተቀምቷል በበሽታ ደቋልበኑሮው ሁሉ ተጎሣቁሏል ለሕይወቱ ዋስትና የሌለው በወያኔ የጎሣ ጅራፍ እየተገረፈ ነውየኢትዮጵያ ሕዝብ በአምስት ሺህ ዓመታት ታሪኩ እንደ አሁን ያለ መንፈሳዊ ሕይወቱና ማኅበራዊ ኑሮው የተቃወሰበት ጊዚያት ፈጽሞ የለም ክፍል አንድ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ምዕራፍ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ አስተዳደር ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ፈላጭ ቆራጭ ቢሆኑም አቋማቸው ሁሉንም ብሔረ ሰቦችን ያጠቃለለ ነበር። አንድ አገር አንድ ሃይማኖት የሚለውን የዓፄ ዮሐንስ ኛን መርህ ባይከተሉም እንኳ አገር በቀል ያልሆኑ የባዕዳን እምነቶች እየቡቡ ሕዝቡን በእምነት አሳበው እንዲከፋፍሉት መፍቀድ አልነበረባቸውም አገሪቷን ከሕዝቡ ዕድገትና ከተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር አላገናዘቡምዓይነተኛዋ ኢትዮጵያዊቷ ተዋሕዶ ሃይማኖት አገር ወዳዶችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን የነፃነት መሠረት የባሕልና ሥርዓት መፍለቂያ የነበረች ቀደም ብሎ የተዳከመች ብትሆንም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ይበልሹን ተዳከመች ከመሠረቷም ተናጋች ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አንዳንድ ተገንጣይ ብሔረተኞች የአማራ ሕዝብ መሪ ያደርጓቸዋል እንደ እውነቱ ከሆነ በአማራነት ተመክተው የማያውቁ ለአማራ ሕዝብ የተለዬ ነገር ያላደረጉ ጎሳዊ ስሜት ፈጽሞ አልነበረባቸውም የንጉሠ ነገሥትነት ሥልጣን ከአማራ አስጠጋቸው እንጂ በዘር ሐረግ ተስበው አይደለም። ማንም የቸገረው ሰው ሹመት እንዲሰጠው በየመጠጥ ቤቱ ሰካራሙ የሚነግረውን እየለቀመ ንጉሠን ዘልፏል ክብራቸውን ነክቷል እያለ ተቆርቋሪ መስሎ ፍርድ ቤት ከሶሶ እያስቀጣ ይሾም ይሸለም የነበረው ብዙ ነው ይህን ተራ አሉባልታ ኮሉኔል ወርቅነህ ገበየሁ በካቢኔው ውስጥ የጸጥታ ክፍል ኃሳፊ በነበረ ግዜ ማንም ሰክሮ የሚናገረውን ክብረ ነክ ዘለፋ እያሉ የሚከሱትን ሰዎች ክስ ፍርድ ቤት መቀበል አይገባውም ከሚዎድዎት ሕዝብ ሆን ብለው ሊለይዎት ነው ያሰቡት ሰዎች መጠቀሚያ አድርጎዎታል ብሎ ያቀረበላቸውን ንጉ ተስማምተው የዘለፋና የክብረ ነክ ክስ ተዘግቶ ነበር ከታኅሣሠ መፍንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ ግን በከፋ መልኩ ቀጥሎ ነበር ክቡር አቶ ብርሃኑ ድንቄ በዩናይትድ ስቴት ኦፍ አሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ተሾመው ዋሽንግተን ዲሲ በነበሩበት ግዜ በኢትዮጵያ ስለነበረው ብልሹ አስተዳደር ለዓፄ ኃይለ ሥላሴ በግንቦት ቀን ዓም የጻፉላቸው ትንቢታዊ ደብዳቤ እንዲህ የሚል ነበር በኀብረት ለመሥራት ካልሞከርን ታላቅ ብጥብጥ እንደሚያስከትልብን ከታሪክ መማር ካልቻልን ከተከታዩ መቅሰፍት የምናመልጥበትና የምንከለልበት ሰው ሠራሺ ዘዴ ይገኛል ብሎ ራስን መደለል በሕልም ዓለም ውስጥ ለመኖር እንደ መፈተን ይቆጠራል በፈጸምነው ስህተት ታሪክ ምሕረት ሊያደርግልን ፈጽሞ አይችልም ጽሁፋቸውን በመቀጠል በብርቱ የሚያሳስበን ስገልጽ አንዳንድ ሰዎች አንተን ምን አገባሕ በማለት በጉዳዩ ባለቤትነት ክፍያ ድርሻችንን ለማሳነስ ቢሞክሩም በኢትዮጵያዊነት ትክክለኛ መብት ላይ አጥብበው ያሰመሩበትን የወሰን ክልል አሜን ብሎ ለመቀበል ከቶ ስለሚያስቸግር እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኃላፊነቱን የማስወገድ ተግባር እንዳለበት አይካድም በአሁኑ አያያዝ እንዲቀጥል የተተወ እንደሆነ በኢትዮጵያ የወገን መለያየትና የደም መፋሰስ እንደሚያሰጋ የመላው የኢትዮጵያዊያን ግምት የወደቀበት ነው መቼም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በሚመስለውና በሚያምንበት ረገድ መልሱን ለመስጠት ሞክሯል አሁንም የጎደለ መስሎ የሚታየው ከዙፋኑ በኩል የሚጠበቀው ብቻ ነው ብለው ገልጸውላቸው ነበር። ትላልቅ መንግሥታት ትናንሽ መንግስታትን መውረር ለዓለም ጸጥታ አስጊነቱን በመግለጽ በወራሪዋ ኢጣሊያ አስፈሳጊው እርምጃ ካልተወሰደ ዛሬ በትናንሽ መንግሥታት የተካሄደው ወረራ ነገ በትላልቅ መንግሥታት በየአንዳንዱ ላይ የሚደርስ መሆኑን አሳስበዋል በማህበሩ ስብሰባ ሳይ የተናገሩት ራዕይ ትንቢቱና ማስጠንቀቂያው ሳይዘገይ ደርሶ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፈንድቶ ለ ሚሊዮን ሕዝብ እልቂትና ለብዙ ንብረት መውደም ምክንያት ሆነ ንጉሥ ውጭ አዢ በሥደት ቢቀመጡም በጽሑፍ በማበረታታቸውና በማጽናናታቸው አለኝታና መኩሪያ በመሆን ለዓርበኛው ከፍተኛ የሞራል ብርታት ሰጥቷል ጠላት ድል ሆኖ ወደ ዙፋናቸው ሲመለሱ ዓርበኛውን ሥደተኛውንና ለጠላት አድሮ ባንዳ ሆኖ ያገለገለውን አስማምተው ምንም ዓይነት ግጭት ሳይኖር ደም ሳይፈስ የተበታተነውን ሕዝብ በዓንድ ላይ አጠቃለው በመምራታቸው ተደንቀውበታል የመንግሥታቸው መዋቅርም ሁሉን ብሔረስቦችና ዜጎች ልዩነት ያላደረገ ዕኩል ያቀፈ መንግሥት በመመስረታቸው አገሪቱ ፈጥና እንድትቋቋም አስችሏታል ምንም እንኳን የሥልጣኔ ግፊት ቢሆንም የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ዘመናዊ ትምህርት ቤቶችን ከፍቷል ዘመናዊ የጦር ኃይል አቋቁሟል የየብስና የአየር የቴሌኮሙኒኬሽን መገናኛዎችን ዘረገቷል እንዲሁም ማዕከላዊ መንግሥትን አጠናክሯል ምዕራፍ የሥልጣን ብልግናና ንቅዘት እኔ እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ እንደ ሥራው ፍሬ እሰጥ ዘንድ ልብን እመረምራለሁ ኩላሊትንም እፈትናለሁ ኤር የንፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ባለሥልጣን ሁሉ በጥፋት ላይ ተሰማርቶ ነበር ዓለም በሥልጣኔ በሚገሠግሥበት ሳይንሳዊ ዘመን ያሉ አይመስሉም ነበር ከሕዝብ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ያልነበረው የጦር ሠራዊቱ ሳይቀር አጋጣሚ ሲያገኝ ያጭበረብር ነበር በጠር ሠራዊቱ ውስጥ ዓመት ሳገለግል አብዛኛውን ግዚያት ከነቀዞች ጋር በመዋጋት ነበር ከዚህ ላይ የማሳስበው ከአጥፊዎቹ ወይም ከነቀዞቹ ጋር ያደረግሁትን ትግል ለመግለጽ እንጂ የግል ታሪኬን ለማንጸባረቅ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ በእየዕለቱ ከሕዝብ ጋር የሚገናኙ ነቀዞች ሲሆኑ ቅንቅኖች ደግሞ ከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩ ናቸው በ ዓም ሜጄር ፒጂ ሪንግሮስ ከኢጣሊያ ሠራዊት ጋር በተደረገው ጦርነት ከንጉሠ ከዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘንድ አቅርበው ስላደረግነው ትግል የምሥክርነት ቃላቸውን ስለ ሰጡ ንጉም አመስግነውን ሥራ ይሰጣችኋልና ተጠባበቁ ብለውን ባልደረባም ተሰጥቶን ነበር እኔ ግን ወደ ጎንደር ወዲያውኑ በመመለሴ ጓደኞቼ ሥራም መሬትም የተሰጣቸው መሆኑንና እኔም እንድቀርብ መታዘዙን ስለ ጻፉልኝ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ ቀጥዬ ደሴ ስደርስ የትግራይ ምሥራቁ ክፍል በብዲ ኃይለ ማርያም መሪነት ወይኖ ስለ ነበር እንድዘምት ተገደድኩ። በዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የመኳንንትና የባለሥልጣን ልጅ አጥፍቶ ሲቀጣ አላየሁም ለይማም ብሩም የረዳው የደጃዝማች ልጅ መሆኑ ነው በሻምበል ይማም መሪነት የሚጠበቀውን የመቀሌን ከተማ የወረረ ጦር ወደ ሌሎች የሻለቃ ጦር እንዲበታተን ተደረገ እኔም የወያኔ ጦር እንደተደመሰሰ ተገድጄ ነውና የዘመትኩ ልቀቁኝ ብዬ በዚያን ግዜ የሬዥማ አዛዥ ለነበሩት ለኮሎኔል አበበ ደገፉ ባመለክት አይሆንም ብለው በሻለቃ ጌታሁን አስፋው ለሚታዘዘው ለኛ ሻለቃ ጸሐፊ አድርገው ደለደሉኝ ሻምበል ይማም ብሩና የመቶ አለቃ ዘለቀ ማዕረጋቸውን ተገፈው ሦስት ሦስት ዓመት እሥራትና የማሩን ዋጋ እንዲከፍሉ በክቡር ራስ አበበ የፍርድ ጉባዔ ሦስት ዓይነት ቅጣት ስለተፈረደባቸው ሻለቃ ጌታሁንና ሻምበል በዕደማርያም አመዴ እኔን እንዲበቀሉላቸው መማጸናቸውን ሰማሁ። እንዲሁም ያወቅት ንጉሠ ዓፄ ኃይለ ሥላሴን እርጅና እየተጫናቸው ብልጠታቸው እያከተመ የሔደበት ብለዋል እየተባለ በቀላጤ የተሰራበት ባለሥልጣን እርስ በርሱ የተከፋፈለበት ማዕከላዊ መንግሥት የላላበት የትግራይና የወሎ ክፍላተ አገር ሕዝብ በድርቅ ምክንያት በረኃብና በበሸታ ያለቀበት እንዲሁም የግብርና ልማት ከምን ግዜውም ይልቅ የተጧጧፈፈበት ወቅት ነበር በታኅሣሥ ቀን ዓም የክብር ዘበኛ ባልተሳካ መፈንቅለ መንግሥት አከታትሎ ሦስት ቀን በሬዲዮ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ከገለጸለት በኋላ በጦር ሠራዊቱ ውስጥ የነበረው ጠንካራ ስነሥርዓት ዲስፕሊን እየላላ የበታች ለበላዩ ይሰጠው የነበረው አክብሮት እየተቀነሰ ወደ ሥርዓት አልባነት ዕያዘነበለ በያለበት የጦር ሠፈር መብታችን ተጓደለ እያለ ያሜረበትና ያደመበት ወቅት ነበር ታዲያ እያንዣበበ የመጣውን መቅሰፍት ተመልክቶ መፍትሔ የፈለገ ባለሥልጣን አልነበረም መንግሥት ልትገለብጡ አሲራችኋል ተብለን የተከሰስነው መኮንኖች አንድ ሲቢል በጠቅላላው ነበርን። የሚቀጥለው ቀጠሮ ወደ ዓም መስከረም ወር መተላለፉን በበቀጠሮ ተነግሮን ተለያየን በተለይ እኔ መንግሥት ለመገልበጥ ተሰብስበው መክረዋል በተባሉትና እኔም ተናግሯል በተባልኩበት ቀን ሐረር በሥራ ሳይ እንደ ነበርኩ ስድስት መኮንኖች አረጋግጠው ሲመሰከሩ የአቃቤ ሕግ ምሥክር ሁነው የቀረቡት ግን በቤጌምድርና ሰሜን ክፍለ አገር የሰሜን ክፍለ አገርን ሕዝብ የሚወክል በመንግሥት ከፍተኛ አመራር በካቢኔ ውስጥ የለም የቤጌምድርና የሰሜንን ሰው ምን ቢማር በሲቪል ከአውራጃ አስተዳዳሪነት በወታደር ከኮሎኔልነት አያልፍም የሚሾሙት የሸዋን ሰው ብቻ ነው የዚያን የጀግና የቴዎድሮስን አገር የይሁዳ ወንድም ይጫወትባታል በሚል እና እናንት የአገሬ ልጆች ቆራጦችና ታማኞች ስለሆናቸሁ ወንድሞቻችሁን አሳልፋችሁ አትሰጡም ብለሃል የሚል ነበር በተከሳሾች ላይ ለምሥክርነት የቀረቡት የሃምሣ አለቃ ንጋቱ ከበደ ትውልዱ ላስታ ጎንደር የኖረ የሃምሳ አለቃ ፍልፍሉ ትውልዱ መርሐ ቤቴ የአሥር አለቃ ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም ትውልዱ ሰሜን ሁሉም ጎንደር ኛ ብርጌድ የኛ ሻለቃ ባልደረቦች የነበሩ በታኅሣሱ ዓም በክብር ዘበኛ መፈንቅለ መንግሥት አንደኛ ሻለቃ ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ተዛውሮ በአዲስ መልክ በተዋቀረው ክብር ዘበኛ ተመድቦ በነበረው ውስጥ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው በ ዓም በቀጣዩ ቀጠሮ ምል አፈ ንጉሥ ኃይሌ ወልደ ሚካል በጡረታ ተገልለው በሳቸው ምትክ ዋና ዳኛ በሆነው በከበደ ከልል ሰብሳቢነት በተሰየመው ጠፍቤት ክርክራችንን ቀጠልን ጀነራል ደግነህ ጉግሣ የኛ ክፍለ ጦር ምአዛዥ በቀጠሮው ቀን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርበው ጥር ቀን ዓም ሐረርጌ እንደ ነበርኩ የምሥክርነት ቃላታቸውን ሰጡ። ልዩ ጥቅም የሚገኘው ወፍ ጥሬ እንደምትለቅም ሥራዬ ብሎ ከሰው አንደበት የሚወጣውን ቃላት እየለቀመ ማቅረብ በመሆኑ ጀነራል ደበበ ኃይለ ማርያምም የክብር ዘበኛ ክፍለ ጦር አዛዥ በመሆኑ የአገሪቱ ሉዓላዊነት የሚጠጠበቅበትን ዕቅድና ስልት እያጠና ከማቅረብ ይልቅ ከንጉሠ ፍርፋሪ ለማግኘት የሆነ ያልሆነውን ወሬ እየለቀመ ማቅረብን እንደትልቅ ሥራ የቆጠረ ሰው ነበር ሌላው አቃቤ ሕግ ሁኖ ይሞግተን የነበረው ኮሎኔል ተፈራ ዝማርያም የተባለ የፖሊስ ሠራዊት ባልደረባ የለየለት አጭበርባሪ ለተመደበበት ሥራ ያልታመነ ክብሩን በጉቦ እየተደለለ ቸርቻሪ ሰው ነበረየወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንቀጽ ያሰበ ይሞታል በሚለው ተከሰን ወህኒ ቤት ከነበርነው መኮንኖችና ሲቪል መካከል አንዱ የመቶ አለቃ ነጋሽ ተሰማ ለአቃቤ ሕጉ ለኮሎኔል ተፈራ ዝማርያም ጉቦ ከሰጠነው በነፃ እንለቀቃለንና ገንዘብ አዋጥተን እንስጠው ብሎ አማከረን እኛ ግን የመንግሥቱን የሥልጣን ብልግና ንቅዘቱንና ሙስናውን እየተቃወምን የጥፋቱ ተባባሪ በመሆን ጉቦ ሰጥተን ከመፈታት ይልቅ የፈለጉትን ይፍረዱብን ብለን መታሰርን ወይም ሌላ የሚወሰድብን ርምጃ ለመቀበል የወሰነው ኮሎኔል እምሩ ወንዴ ኮሎኔል አሰፋ አንዳርጌ ኮሎኔል አስናቀ እንግዳ ሻለቃ ታደሰ አሲ ሻምበል ዘውዴ ወልደ ቂርቆስ ሻምበል ጥላሁን ዳምጠው ሻምበል ፋንቱ በቀለ ሻምበል ሽፈራው ከበደ ሻምበል ደገፋ ማሬ አቶ በቀለ ሥዩም ነበርንየመቶ አለቃ ነጋሽ ተሰማ ግን ቀደም ብሎ እንደ ተናገረው በሚስቱ በኩል ለኮሉኔል ተፈራ ገማ ጉቦ ሰጥቶ ከ ዓመት እሥራት በኋሳ በነጻ ተለቀቀ የዓፄው መንግሥት የተበላሸ እንደነበረ ከዚሁ አቃቤ ሕግ ከተባለው ሰው ሥልጣኑን በጉቦ እየተደለለ ከሚቸረችር መረዳት ይቻላል ሰብሳቢ ዳኛ ሁኖ አዲስ የተሰየመው ከበደ ከልል ለሹመት የቋመጠ ነበርና በእኛ ላይ ፈርዶ ለመሾም ሲል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በልዩ ዝግ ችሎት የወሰነብን የእሥራት ቅጣት ማፅደቅ ወይም መሻር ወይም መቀነስ ሲገባው እኛ ተከሳሾቹ ያለአገባብ ተፈርዶብናል ብለን ባቀረብነው ይግባኝ ምንም እንኳ የወጣው ሕግ በትክክል በስራ ላይ ባይውልም ከሕጉ ውጭ በከፍተኛው ፍቤት ዓመት በተፈረደብን ላይ ሁለት ዓመት ጨምሮ ። ወሬውም ቁም ነገር ያለው ሳይሆን እርስ በርሱ ለመሰረጃጀት ምቀኝነትና ቅናትን በማስተጋባት ነው ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከሥደት ከተመለሱ በኋሳ ከ ዓመት በቆራጭ ፈላጭነት ገዝተዋል በዚህ ዓመታት ውስጥ የወሬ እንዱስትሪ ማቋቋሙን ትተው አገሪቱ የምታድግበትን መርሃ ግብር ዘርግተው ቢመሩ ኑሮ ጃፓን በሃያ ዓመታት ውስጥ ተአምራዊ ዕድገት እንዳሳየች ኢትዮጵያም በሕዝቧ ብልህነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ትደርስ ነበር ዳሩ ግን ከሞት ተሸሽጎ ያመለጠ እንደሌለ እየታወቀ ሕግና ሥርዓት ጠፍቶ በጆሮ ጠቢ የተዋቀረው መንግሥት መውጫ ወደ ሌላው ጉድጓድ ወረደ የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት በሌሎች መበለጡ ቆጭቶት አሰልጣኞችን ከውጭ አገር ቀጥሮ በማስመጣት ልዩ ልዩ የሙያ ትምህርቶችን በአገር ውስጥ በመቆጣጠር እንዲሰጥና በማድረግ ለሳይንሳዊ ዕድገት ከመጣር ይልቅ ኢትዮጵያን የሚያፈራርስ የስለላ ተልዕኮ ያላቸው ፒስኮርን የመሳሰሉ በማስገባት አሲድ ነስንሰው ውስጧን ቦርቡረው አሁን ለተከሰተው ጎሣዊ እንቅስቃሴ መሠረት የጣሉ ናቸው ሌላው ኢትዮጵያ የሃይማኖት ችግር ያለባት ይመስል የኮሎኒያሊስቶችና የኢምፔሪያሊስት ልዑካን ሚሰዮናዊያን በማስገባት ብዙ ወጣቶችን ለአገራቸው ነጻነትና ሰብአዊ መብት እንዳይታገሉ ወኒያቸውን እየገደሉ አገር ወዳድነትንና በራስ መመካትን ከሕሊና የሚያጠፉ ትምህርት እየሰጡ በጀግንነት ባሕል ላይ በረዶ አስገብተው ኢትዮጵያን የወላድ መካን አድርገዋታል የእነርሱ ግርፍ የሆኑና እምነታቸውን የተቀበሉ ለዴሞክራሲያዊ መብት መታገልን ይኮንናሉ ወደ ስለላው ስንመለስ ደግሞ በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ሥነ ምግባርና ወግ አንዱን ከሌላው ጋር የሚያጋጭ የሰማውን ሰማሁ የአየውን አየሁ ብሎ እንዳያወራ ወላጆች ለልጆቻቸው ያስተምሩ ነበር። በቀጠሮ ያለው እስረኛ ፍርደኛ ካለው የሚለየው እንደ ፍርደኛ ኢንዱስትሪ ከሚሉት ወርክ ሾፕ ሒዶ አለመስራቱ ነው ሌላው እግር ዘርግቶ መተኛት ይችላል ከነዚህ በቀር በሌላው ረገድ አንድ ዓይነት አስተዳደርና አመጋገብ ነው የነበረው ልዩነት አልነበረም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የፖለቲካ እስረኞች የሚባሉት አብዛኛው ክብረ ነክ ዘለፋ ንጉሠን ዘልፈሃል የንጉሠን ክብር ነክተሃል የሚል ሲሆኑ ሌላው ንጉሠን ለመገልበጥ አሲረሃል የሚል ነበር የኢኮኖሚ ጥያቄም ወደ ፖለቲካ የተደመረበት ግዜ ነበር ለምሳሌ የጦር ሠራዊት በጠረፍ ጥበቃ የተሠማራው በምግብ እጥረትና በመኖሪያ ቤት እጦት ይሰቃይ ነበር በነገሌ ቦረና በደውሎ ከሶማሌ ጋር በሚያገናኘው ወሰን ሠፍሮ የነበረው የኢትዮጵያ ጦር በአንፃሩ የነበረው የሶማሊያ ጦር ድንኳን ተተክሎለት ውኃና ምግብ እየቀረበለት በደኅና ሁናቴ መያዙን ያይ የነበረ የኢትዮጵያ ሠራዊት በምግብና በውኃ አቅርቦት የተበደለ በመሆኑ ከዕለታት አንድ ቀን አስር አለቃ ኃይለ ማርያም የተባለ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ሲያነብ በጋዜጣው ላይ የንጉሠን የዓፄ ኃይለ ሥላሴን ፎቶ ግራፍ አይቶ አንተ እኮነህ የምታሰቃየን ብሎ ዓይናቸውን በጣቱ ጠንቁሎ በመቅደዱ የንጉሠን ዐይን አጥፍቷል ተብሎ ተከሶ ከነገሌ አዲስ አበባ ዓለም በቃኝ ታስሮ ማስረጃ እስኪቀርብ በቀጠሮ ፍርድ ቤት ሲመላለስ ከቆዬ በኋላ ዓይኑ ጠፍቷል የተባለው ጋዜጣ ለዳኞች በጃኖ ተሸፍኖ ቆርቦ ዳኞቹም ጃኖውን አስገልጠው ጋዜጣውን ሲያዩት እረ ዓይናቸውን አጥፍቶታል ብለው አማትበው አምስት ዓመት ጥብቅ እስራት ፈርደውበት ነፍሰ ገዳይ ከተባሉት ጋር ዓለም በቃኝ ውስጥ ታስሮ ነበር ብጋዜጣ ሳይ ያለ ፎቶ ግራፍ ዓይን አጥፍቷል ተብሎ በከፍተኛ ፖለቲካ ከስሶ የሚያስር መንግሥት ነው የነበረው ጋዜጣ የትም ቆሻሻ ቦታ የሚጣል የሚረገጥ የሚፀዳዱበት መሆኑ እየታወቀ አወዳሾችና ተመጻዳቂዎች የንጉሠሙን ዓይን አጥፍቷል ብሎ የሚፈርድ ምን ዓይነት የዳኝነት ሥርዓት እንደነበር ከዚህ ድርጊት መገንዘብ ይቻላል ሌላው ደግሞ ጽጌ ውልደ ማርያም የተባለ እስፖርተኛ የነበረ አቶ ይድነቃቸው ተሰማን እንኳን ለእስፖርት ኢትዮጵያን ለመምራት ይችላል ብለህ ተናግረሃል ተብሎ ወህኒ ቤት ታስሮ ነበር የአቶ ይድነቃቸውን ችሉታ በመሰከረ እንደ ፖለቲካ ተቆጥሮበት መታሰር ቀርቶ ሊያስከስሰው ይገባል ወይ። መንግሥት ልትገለብጡ አሲራቸኋል ተብለን በዓለም በቃኝ ታስረን የነበርነው መኮንኖች አንድ ሲቪል ነበርን ኮሎኔል እምሩ ወንዴ ከባሕር ኃይል የዱሮው ክብር ዘበኛአአ ኮሎኔል አሰፋ አንዳርጌ ከጦር ሠራዊት አዲስ አበባ ኮሎኔል አስናቀ እንግዳ ከጦር ሠራዊት ሐረር ኛ ክጦር ሻለቃ ታደሰ ዓሊ ብ ጎዴ ሻምበል ፋንቱ በቀለ አዲስ አበባ ሻምበል ዘውዴ ወቂርቆስ ከክብር ዘበኛአዲስ አበባ ጥላሁን ዳምጠው አዲስ አበባ ሺፈራው ከበደ ከፖሊስ ሠራዊት ደገፉ ማሬ መአ ነጋሽ ተሰማ ከጦር ሠራዊት አአ አቶ በቀለ ሥዩም ከሲቪል ዓመት ወህኒ ቤት የታሰረ ሻምበል ታምሬ ገየስ ጦር ሠራዊት ከታሰረ በኋላ መሳርያ ከቤቴ አለና ላስረክብ ብሎ ሒዶ አጃቢዎቹን ገድሎ ተሰውቷል ሻምበል በቀለ ሰጉ ከባህር ኃይል የዱሮ ክብር ዘበኛአአ ተይዞ ከታሰረ በኋላ ከኛ ፖሊስ ጣቢያ በቤት ጣራ ሳይ ወጥቶ አምልጦ አስር ዓመት ከአንድ አስር አለቃ ቤት ተደብቆ ያሳለፈ የ አለቃ ከፍያለው ተፈራ በሌለበት ቤቱ በመበርበሩ ሳይያዝ አምልጦ ሰሜን አውራጃ ዓዲአርቃይ አካባቢ ታሞ የሞተ አቶ አቤ ጎበኛ ከእኛው ጋር ተጠርጥሮ ተይዞ ወደ ኢሉባቦር ግዞት የተላከ ዓለም በቃኝ ያልገባው ጀኔራል መርዕድ መንገሻ ተከላክለውለት ነው ተብሏል ሌሎችም መንግሥት ልትገለብጡ አሚራችኋል ተብለው ዓቃቂ ወህኒ ቤት የታሠሩ የተለያዩ ክፍሎች ነበሩ በፊታውራሪ ደስታ ፍስሐ ጦና መሪነት የወላይታን ሕዝብ ለዓመፅ ቀስቅሳችኋል የተባሉ ሰዎች እነ ፊታውራሪ ገብረ ጊዮርጊስ ኢላላሳ እነ ቀኛዝማች ፍሬው ኢሳላ እነ ቀኛዝማች ዋደን የመሳሰሉ እንደዚሁም የኦሮሞን ሕዝብ ለዓመጽ ቀስቅሳችኋል የተባሉ የሜጫና ቱለማ ማኅበር አባሎች ኮሎኔል አለሙ ቂጤጢሳ አቶ ኃይለ ማርያም ገመዳ ጀኔራል ታደሰ ብሩ ጄኔራል ዳዊት አብዲ ቀኛዝማች መኮንን ወሰኑ ልጅ በቀለ መኮንን የመሳሰሉ ያህል ነበሩ። ከነዚህ ውስጥ አቶ ኃይለ ማርያም ገመዳ ፍርድ ቤት የሚቀርቡት በዊል ቸር ነበር በኋላ ግን መቀመጥ አቅቷቸው በቃሬዛ ላይ ተኝተው ነበር ፍርድ ቤት የሚቀርቡት በ ዓም መፈንቅለ መንግሥት ልታደርጉ አድማችኋል የተባሉ እነ ክቡር ቢትወደድ ነጋሽ ከበደ በዛብህ አለቃ ፈጠነ የመቶ አለቃ በቀለ አናሲሞስ ዮሐንስ ረምሣ አቶ አካሉን ከመሳሰሉት የመቶ አለቃ በቀለ አናሲሞስ ብቻ በዚህ ወህኒ ቤት ውስጥ ነበሩ በክብር ዘበኛ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ተካፋይ ነበሩ ከተባሉት የክብር ዘበኛ መኮንኖች ሻለቃ ተፈራ ወልደ ትንሳኤ ሻለቃ ተሰማ ዋቅጅራ ሻምበል አስራት ደፈረሱ ይገኙበታል ከቀኃሥ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ ናቸው ተብለው ከታሰሩት መካከል ብርሃነ መስቀል ረዳ ዘሩ ክሸን ፋንታሁን ጥሩነህ ማለደ ዘውዱ ታምራት ከበደ ሄኖክ ክፍሌ መለስ ተክሌ ዋለልኝ መኮንን ዱላ አብዲ ይገኙበታል ከልዩ ልዩ ክፍል በፖለቲካ ተጠርጥረው የታሠሩ ቄስ መቶ አለቃ ዘውዴ ከነ ክቡር ደጃዝማች ታከለ ወልደ ሐዋሪያት ጋር መንግሥት ለመገልበጥ እሲረሃል የተባሉ እና አቶ ዓለም ሰገድ ገብረ አግዚአብር ፓርላማ የነበሩ በፖለቲካ የተጠርጥረው የሻዕቢያ አባላት ሙሐመድ ኪዳኔ መሐመድ እድሪስ የተባሉ ብጀኔራል ተሾመ እርገቱ ሳይ ቦምብ ጥላችኋል የተባሉ ኤርትራውያን መሐመድ ሐሰኖና አብደር ሁማን የተባሉየተረሸኑ ከጀኔራል ተድሳ ዕቁቢት ጋር አባሪ ናቸው የተባሉ ሻለቃ በላይ ሻምበል ፀሐዬና ሻምበል ዓረፈ ዓይኔስሙን የማሳስታውሰው ኤርትራዊ ለኤርትራና ለኦጋዴን አማጽያን በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል የጦር መሣርያ እያስመጣችሁ ትልካሳችሁ ተብለው የታሠሩ አቶ በቀለ ብርሃኔ ከአሜሪካ ኤምባቢ የሚሠሩ የዓድዋ ተወላጅ አቶ ኃይሌ መከታ ነጋዴ የኤርትራ ተውፊክ ሸሪፍ ነጋዴ የአደሬ ተወ ው ተወላጅ። ጀኔራል ነጋ ተገኝን ያወቅኋቸው በ ዓም በፖለቲካ ተጠርጥሬ በእስር ወደ ሐረር ስላክ ድሬዳዋ ከባቡር እንደወረድን ከነ ጠባቂዬ መኮንን ሆቴል ቤት ምሳ ጋብዘውን ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋቸው ከዚያ በፊት አላውቃቸው ነበር ከዚያም ሐረር በኛ ክፍለ ጦር ወታደር ፖሊስ ስታሠር ምግብ ያለ ማቋረጥ ይልኩልኝ ነበር በድጋሜ በ ዓም ስታሠር ከእናንት እየአንዳንዱ የባልንጀራውን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ ገላ በሟለው ትዕዛዝ መሠረት ቤተሰቦቼን በገንዘብ በመርዳት አምሳካዊ ትዕዛዝን በትክክል የፈጸሙ አጅግ የማከብራቸው ሰው ናቸው ከወንድም በላይ አብልጦ የሚወደድ ወዳጅ አለ ምሳ የሚለውን ጄኔራል ነጋ ተገኝ በትክክል ፈጽመውታል ምዕራፍ የኢትዮጵያ ጎሳዎች ኅብረታዊ መሠረት የሰው ልጅ ቅድመ ታሪኩ እንደሚያሳው አንድ ሕዝብ ነበር እየተዋለደና እየተራባ ሲበዛ በነገድ ተከፋፈለነገዱም እየበዛ ሲሔድ የጎሣ ማኅበርን ፈጠረ ኅብረሰቡም በጎሣ ማኅበር መንግሥታዊ ሥር ዓት ሳይኖረው በዘልማድ ብዙ ሺህ ዓመታት ተጉዞአል እንደ ጥንተነገሮች ተመራማሪዎች ለክክአርሀጁ እና ለርከ የዛሬው ሥልጣኔ ከተጀመረ ሺህ ዓመት መሆኑን ይገልጻሉየሰው ልጅ በረጅሙ በዘገምታ ህ እየዳኸ የተጓዘው አንድ ወጥ ሁኖ አይደለም በጎሣና ነገድ ተከፋፍሎ እርስ በርሱ እየተባላና እየተጋጨ ነው ምድራዊ ሰው በማኅበራዊ ኑሮ እየተጠጋጋ የሔደው ሥልጣኔ ጨለማውን ድንቁርናን እየገፈፈ ወደ ብርሃን ከመራው በኋላ ነው የከብት ጭራ ተከትሎ ግጦሽ ወደ አለበት ከአገር ወደ አገር መንከራተቱን እየተዎ በአንድ አካባቢ እንዲረጋ ምክንያት የሆነው የማምረቻ መሣሪያዎች ከተፈለሰፉ በኋላ ነው አብዛኛው ወደ ግብርና ሲዛወር ከተሞችንና መንደሮችን እየሰራ መንግሥታዊ ሥርዓት እያቋቋመ በሕግና ሥርዓት መተዳደሩን የቀጠለ መሆኑን ታሪክ ያስረዳል ቅድመ ሥልጣኔ በጎሣውና በነገዱ ተከፋፍሉ የነበረው ዘላን ሕዝብ በጥንት ዘመን ከቦታ ቦታ ለመዘዋወር የሚገታው ክልል አልነበረም ሁሉም በየፊናው ተነቃናቂ በመሆኑ የኔ ነው ባይ በሌለበት ምድር በነፃ የመንተሳቀስ ዕድል ነበረው በኋላ ግን ምድር በአገር ከተከፋፈለች ወይም ከባላባቱ ጋር በመጋጨት ከአንዱ አገር ወደ ሌላው አገር የመዘዋወር እድል እየጠበበ ሔደ ከአገር በቀል ነገዶችና ጎሣዎችም በተጨማሪ በየዘመኑ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የከብት ጭራ በመከተል ግጦሽ ፍለጋ ወደ ኢትዮጵያ ይገቡ እንደነበር ይታወቃል። የሰፈሩበትን አካባቢ ለግጦሽ በጋርዮሽ ይጠቀሙበታል በኢትዮጵያ የታወቀ መንግሥት ከተቋቋመ ሺህ ዓመታት አድርጓል ከክርስቶስ ልደት በፊት ሺህ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በኋላ ሺህ ዓመት ነው ይህም ታሪክ መጻፍ ከተጀመረ ወዲህ ያለው እስከ ንግሥት ሳባ ሺህ ዓመት ከንግሥትሳባ እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ሺህ ዓመት ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ሺህዓመት መሆኑ ነው በድሮው ዘመን የሰለጠነው የኢትዮጵያ መንግሥት መንግሥታዊ መዋቅሩን የዘረጋው ትምህርት ቤቶችን በማቋቋም የሃይማኖት ቤተ ጸሎቶችን በመስራት የዕደ ጥበብ ሙያዎችን የብረታ ብረት ሥራዎችን በማስፋፋት ለማኅበረ ሰቡ መተዳደሪያ ሕጎችንና ደንቦችን በማዘጋጀት ፍትሐ ነገሥትን የመሳሰሉ የአስተዳደርና የዳኝነት ስነ ሥርዓት አፈጻጸሞችን የሕዝብ ምክር ቤት ሸንጎን የመሳሰሉትን በማቋቋም በዘመኑ ተራማጅ ሥልጡን መንግሥት መሠረተ ከአክሱም የተጀመረው ሥልጣኔ ሲሰፋም ሲጠብም በጦርነት ሲዳከም ደብዛው ጨርሶ ሳይጠፋ አዝግሟል በአንዳንድ የዓለም ክፍል ሥልጣኔ ሳይገታና ሳያቋርጥ ዕድገቱን እየቀጠለ ሲጓዝ የሥልጣኔ ጀመሪ የነበረችው ኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነት አጫጭቷት የኋላ ተጓዥ ወይም ሥልጣኔ ተመፅዋች አድርጓታልቋሬ ወያኔ ትግራይ የሚያፈራርሳት ኢትዮጵያ በአንድ ግዜ እንደ እንጉዳይ ቱግ ብላ ያደገች አይደለችም። ደርግም ጭፍን አገር ወዳድ በመሆኑ በር አልከፈተላቸውም ነበር ኢትዮጵያ አንድ አገር አንድ ሕዝብ አንድ ብሔር ሁና የኖረች ጥንታዊት አገር መሆኗ እየታወቀ ዛሬ በመንግሥትነት የማይታወቁ አካሏን በጎሣ እየከፋፈሉ የመንግሥት አቋም እንዲይዙ የሚሸርቡት ሜራ ጎሣዎችን ለመጥቀም ሳይሆን በራስ መመካትንና አገር ወዳድነትን ለማጥፋት ነው የቀደሙ ወላጆች ሕይወት ያለበትን ታሪክ እንዳልነበር አድርጎ ማጥፋት የሜራው አንዱ ክፍል መሆኑ ግልፅ ነው ግንጠላን የሚያራምዱት የኢምፔሪያሊስት ቅጥረኞች የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ መሪዎች የኤርትራ ትግል ከዬት ወደ ዬት በተሰኘው መጽሐፋቸው ክፍል ገጽ ዓም ድሮ ጀምሮ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ነበረች ማለት የአማራው ብሔር የገዥ መደቦች ቡችላ የሆኑ የታሪክ ጸሐፊዎቻቸው በታሪክ ስም የሚያቀርቡትና የሚዘረጉት አፈ ታሪክ ቁጥሩ የማይናቅ ሕዝብ እንደ ትክክለኛ ሐቀኛ ታሪክ አድርጎ ይቀበለዋል። ከአንደኛው በቀር ሁለቱ ጎጠኛ መሥመር የያዙ ናቸውእነዚሁ በዓላማና በአመለካከት የተለያዩ ቡድኖች በኛው ምዕት ዓመት መገባደጃ በ ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ የፈጸሙት ግፍ ምንግዜም የማይረሳ አሰቃቂ ታሪክ ነው በእርስ በርስ ግጭት የከፋ የጦርነት ታሪክ የረኃብና የጉስቁልና ታሪክ የመበታተንና የስደት ታሪክ የውርደትና የበሽታ ታሪክ በጎሳና ቋንቋ የመከፋፈል ታሪክ የመልቲነትና የክህደት ታሪክ የአፈናና የንብረት ዝርፊያ ታሪክ የግዕዝ ፊደል ግዞትና የቅርሳ ቅርስ ዝርፊያ ታሪክ ሥርዓትና ሕግ የጠፋበት ታሪክ አንድ ጎሣ በቆራጭ ፈላጭነት የነገሠበት ታሪክ በእርስ በርስ ጦርነት የድል ሐውልት የቆመበት ታሪክ የኢትዮጵያ ጠላት ኢጣሊያዊ የላቲን ፊደል መማሪያ የሆነበት ታሪክ አገር ገንጥሉልኝ ተብሎ የተጻፈበት ታሪክና አገር ወዳዶች የተጋዙበትና የተገደሉበት ታሪክን ነው ወያኔዎች ያስመዘገቡት ኢትዮጵያን በዘመናዊ ሥልጣኔ አራምዶ የሕዝቡን ኑሮ ለመገንባት የሚንቀሳቀሱ አር ወዳድ ኃይሎች በቅድሚያ የሚጠበቅባቸው በ ዓመታት ውስጥ የተበከለውን ታሪክ ለማደስ በአጭበርባሪዎች የተወናበደውን ሕዝብ አንቅቶና አደራጅቶ መሠረታዊ መብቶቹን እንዲጠይቅ ማድረግ ነው በዚያም ሆነ በዚህ ሕዝብ የኑሮን ጣፋጭ ሕይወት በመልካም ለመምራት የሚበጀው በጎሣና ቋንቋ ለመከፋፈል በመካከሉ የተደረደረውን ከፋፋይ አጉራ በጣጥሶ የጥንት ግንኙነቱን አድሶ ለመራመድ ራሱን ማንቃት ይገባዋል አበው አንድነት ኃይል ነፃነትና ኀብረት ብርቱ የማይበገር መሆኑን በምሳሌ ሲያስተምሩ የተነጣጠለ ዘንግ አንድ በአንድ እንደሚሰበር ከአንድ ላይ የታሰረ ዘንግ ግን የማይሰበር ከብረት የጠነከረ ኃይል መሆኑን በሚታይና በሚጨበጥ ምሳሌ በማስረዳት ነበር። ጉልበቱን ሸጦ የሚኖር ሠራተኛ የሚቀርበት ምንም ነገር ስለሌለ የሚፈራውና የሚያሰጋው ባለ መኖሩ በድፍረትና ቆራጥነት በመታገል መብቱን ለማስከበር የሕልውናው ጉዳይ ያስገድደዋል በማንኛውም ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን ያለበት ሠራተኛው ነው መንግሥት ከሕዝብ ግንኙነት ርቆ የራሱን ጥቅም ብቻ የሚሠራ እንደ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ መሳዩ ያገርን ሕልውና ካደጋ ላይ ይጥሳል የሕዝብን ኑሮም ያዛባል በዚህን ግዜ ነው የአንድነት ዓላማ ይዞ ሕዝብ እንዲቃወም የሚገደደው እያንዳንዱ ከሚመፔውና ከሚያስበው የፅድገት ደረጃ ለመድረስ ቀላል ባይሆንም በዋጋ የማይተመን ሕይወትን ከጭጋግና ከከፋ የወንበዴ ሥርዓት ለማላቀቅ ያለው ብቸኛ ዘዴ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲን ጎሰኝነት የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነት ዝባዝንኬዎችን አስወግዶ በኅብረትና በቆራጥ መንፈስ መታገል የመኖር ግዴታ ብቻ ሳይሆን ታሪካዊ ኃላፊነትም ነው ለመንግሥት መታዘዝና ለሕግ መዝዛት የነበረ የቆዬ ሥርዓት ነው ዳሩ ግን ሕዝብ ጥቅሙን አጥቶ እየተዘረፈና እየተረገጠ ፍዳውንና መከራውን እየተቀበለ በስቃይ እየማሰነ ይኑር ማለት አይደለም መንግሥት ማለት የአገርን ነፃነት የሕዝብን መብት እንዲጠበቅ ሕዝብ ያቋቋመው ማኅበር ነው በዚሁ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው ማኅበር ውስጥ የሚያገለግሉ እንደራሴዎች በሕዝብ ተመርጠው የሚሳኩ ናቸው ታዲያ አገልጋይ ከጌታው አይበልጥምና የሕዝብ አገልጋዮች ሲሳሳቱ ማረም አስተዳደር ሲያዛቡ ማቃናት ሲያጠፉ መቅጣት ወይንም ከአገልግሎት ማስወገድ የጠቅላሳው ሕዝብ መብት ሁኖ ሳለ ሕዝብ በመብቱ አልተጠቀመበትም። በግል ፍላጎት ለመደሰት ወይንም የሚያምርን ለማግኘት ከማኅበረ ሰቡ ተነጥሎ መኳተን ካልታሰበ ብርቱ አደጋ ሳይ ይጥሳል ማኅበረ ሰቡ ፍጹም ብኩን የሆኑትን የተምታታባቸውን በኃይል አርቆ በመያዝ ሥርዓት ማስተማር የሰላማዊ ኑሮ ግዴታዎቹ ናቸው ማኅበረ ሰቡ ከመካከሉ አፈንግጦ የወጣን ስቦ ለማስገባት ኃይል ያለው በመሆኑ በቸልታ ሳያልፈው አስገድዶ ሥርዓት ሊያስይዘው ይገባል ምክንያቱም የማኅበረሰቡን ሥርዓት የማያከብሩ ግለ ሰቦች የሚያመጡት ጠንቅ መላውን ኅብረተ ሰብ ከብርቱ አደጋ ሲጥል እነሆ ታይቷልና ለምሳሌ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሕወሓት እና የኤርትራ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ኤሕነግ በሚል ስያሜ ትግሬንና ኤርትራን ለመገንጠል የታገሉ የወያኔና የሻዕቢያ መሪዎች በአገርና በወገን ፍቅር ታንጸው በስነ ሥርዓት ባለ ማደጋቸው ነው በራሳቸው አገር ላይ አምጸው ወገናቸውን ያስጨፈጨፉ ታሪካቸውን የካዱ ከንቃት ጉድለት ነው ወላጆቻቸው በግብረ ገብ ትምህርት ኣንጸዋቸው ቢሆን ኑሮ ይህን ያህል ጥፋት በአገር ላይ አያደርሱም ነበር በራሳቸው ታሪክ ላይም አያምጹም ነበር ልጆች የሚያድጉት የወላጆቻቸውን ጠባይ ይዘው ነው ወላጅ አባት ከዳተኛ ከሆነ ልጁም ከዳተኛ ይሆናል። ሕገ መንግሥት ተብሎ አይጠቀስም አንድ ሕዝብ ረግቶና ተስማምቶ በሰሳም በዕድገት ጉዞ ላይ ያለን ወደ ኋላ ለመጎተትና ለማደህዬት ሆነ ተብሎ ኃይልን ለመበታተን በተካሔደው ሜራ የራስን ዕድል በራስ መወሰን ከዚያም አልፎ እስከ መገንጠል ተብሎ በወያኔ የወጣው ሕገ መንግሥት ፀረ ሰሳም ፀረ ዕድገት ፀረ ኃይልና ኅብረት ከመሆኑም በሳይ አንድን አካል ሰነጣጥቆ ሕይወት ማሳጣት ነው መከፋፈል ኃይልን ይቀንሳል ዕድገትን ይቀጫል ሥልጣኔን ይጎትታል በሳይንስና ቴክኖሎጅ እንዲበለጡ ያደርጋል በሁሉም መስኮች ደካማና ኮሳሳ አድርጎ ያስጠቃል በሕግ ፊት እኩልነት የሚል የአፍ ማሟሻ የልሳን መላሾ አላቸው በፖለቲካ በምጣኔ ሃብትና በማኅበራዊ ኑሮ መስኮችም እኩል ዜጋዊ ድርሻ መኖሩም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ሕገ መንግሥት መደንገጉ ይታወቃል ወደ ዜጎች የእኩልነት መብት ከመሻረዢር በፊት ነፃነት የሚለው ባዶ ቃል ከሠፊው ሕዝብ አንፃር ሲታይ ምን ትርጉም አለው።