Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

ስለ_እንደራሴ_ውክልና_ሕግ_አንዳንድ_ነጥቦች.pdf


  • word cloud

ስለ_እንደራሴ_ውክልና_ሕግ_አንዳንድ_ነጥቦች.pdf
  • Extraction Summary

ጪ ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር ውክልናን እንደተረጐመው ውክልና ማለት ተወካይ በተሠጠው የውክልና ሥልጣን ያለአግባብ ተጠቅሟል ሊባል ይችላል።

  • Cosine Similarity

በኢትዮጵያ ፍትሃብሄር ሕግ አንቀፅ ቁ ውክልና ወይም እንደራሴነት አንድም ከሕግ በሌላ መልኩ ደግሞ ከውል ሊመነጭ እንደሚችል ተመልክቷል ከሕግ የሚመነጨው ውክልና ከላይ እንደተገለፀው የውክልና ትርጉም አይነት ወካይና ተወካይ በመስማማት ስምምነት ላይ የሚደርሱበት የውክልና አይነት ሳይሆን ተወካይ የወካይን ተግባሮች ወካይ ባልፈቀደበት ሁኔታ ሊተገብረው የሚያስችለው አይነት ውክልና ነው ይህም የውክልና ተግባር በህጉ ከተፈቀዱት የውክልና ሁኔታዎች ውጭ ሊመሠረት አይችልም ለዚህ አይነቱ የውክልና አይነት እንደምሣሌነት የሚጠቀሱት ለአካለ መጠን ያልደረሰን ልጅ ንብረት ለማስተዳደር ሕግ የፈቀደላቸው ጠባቂዎች ውክልና አይነት እና በፍትሃብሄር ህጉ አንቀፅ ቁ ላይ በተቀመጠው መልኩ ተግባሮችን የሚተገበሩ በዎች ውክልና አይነት ናቸው ህከበ ሀየ ፐበበ ርከበበ። ወካዩ የውክልናውን ወሰን በውክልናው ውል ላይ በግልፅ ካስቀመጠ ወሰኑ በግልጽ በተቀመጠው መሠረት ይሆናል በሌላ በኩል ደግሞ ውክልናው ለአንድ ልዩ ጉዳይ ወይም ለእያንዳንዱ ጉዳዬች ወይም ለወካዩ ጉዳዮች ሁሉ ጠቅላላ ውክልና ሊሆን ይችላል ፍብህቁ ዐ ን። ይህ ማለት አንድ ሰው ለአንድ ለተወሠነ ጉዳይ ብቻ ወይንም ለተለያዩ ከአንድ በላይ ለሆኑ ጉዳዬች ወይንም ለሁሉም ጉዳዩቹ ውክልና ሊሰጥ ይችላል ማለት ነው ስለሆነም ከላይ በተጠቀሰው የውክልና ወሰን መሠረት ውክልናን ጠቅላላ ውክልናና ልዩ ውክልና ብለን ልንከፍላቸው እንችላላን። በመሆኑም በጠቅላላ ውክልና የውክልና ሥልጣን የተሰጠው ተወካይ ከላይ ከተዘረዘሩት ሥራዎች ውጭ የመሥራት ወይንም የመከወን ሥልጣን የለውም። ብህቁ ከተቀመጡት የአስተዳደር ሥራዎች ውጭ ያሉ ሥራዎችን ማሠራት የፈለገ ወካይ ስራዎቹን በልዩ ውክልና መሠረት ለተወካይ ማስተላለፍ አለበት ማለት ነው ልዩ ውክልና ልዩ ውክልና ማለት አንድ ሰው ከአስተዳደር ሥራ ውጭ ያሉ ሥራዎችን በወኪሉ ለማሠራት የሚያስችለው የውክልና አይነት ነው ፍብህቁ ስለሆነም በልዩ ውክልና የውክልና ስልጣን የተሰጠው ተወካይ ተለይተው በዝርዝር የተመለከቱ ጉዳዬችንና እንደ ጉዳዩ አይነትና እንደ ልማድ አሰራር ከጉዳዩ ጋር ተከታታይነትና ተመሣሣይነት ያላቸው ነገሮችን ማከናወን ይችላል ማለት ነው ፍብህቁ ዐገን ከዚህ ባሻገር አንድ ተወካይ ልዩ የውክልና ሥልጣን ከሌለው በስተቀር ሊፈጽማቸው የማይችላቸው ተግባራቶች በፍብህቁ ዐ ስር ተዘርዝረዋል። ወጭ የመሥዌጠትና የማወራረድ ግዴታ ተወካይ በውክልና ስልጣን የተሠጠውን ኃላፊነት ለመወጣት ወይንም ተግባሮቹን ለማከናወን ወጭ ማውጣት ያስፈልገው ይሆናል ስለዚህ ወካዩ ለሥራው ማስኬጃና ማከናወኛ የሚሆን ወጭ ተወካዩ ሥራውን ከመጀመሩ በፊት ወይንም አስቀድሞ ሊሠጠው ይገባል ከዚህ ውጭም የተሠጠውን ሥራ በጥሩ ሁኔታ ለመሥራት ሲል ተወካይ ያወጣቸውን ሌሎች ወጭዎችም ወካይ ለተወካይ መክፈል ይኖርበታል የፍትሐብሄር ሕግቁ ገን እና ጋን ተወካይን ክግዴታ ነ ማውጣት ተወካይ በወኪልነቱ ለወካዩ ጥቅምና ለውክልናው ሥራ መልካም አካሄድ ሲል ከገባው የውል ግዴታ ወካይ ነፃ ሊያወጣው ይገባል ይህ ማለት ተወካይ በተሠጠው የውክልና ሥልጣን መሠረት ተግባሮችን በሚያከናውንበት ወቅት ለወካዩ ጥቅምና ለውክልናው ሥራ መልካም አካሄድ ሲል የውል ግዴታ ሊገባ ይችላል ወይንም ውል ሊዋዋል ይችላል። ከዚህ ብመቀጠል ደግሞ የጥቅም ግጭት ርዐበቨርከጵርኮክናመቸሬክአመዋከራሰፍኝፒ ከቦቸቸዋል ርዐበኩልር አቪከ ዐበፁሬፀን የውክልና ስልጣንን አለግባብ መጠቀምንና ጊዜው ባለፈበት የውክልና ሥልጣን መገልገልን እንመለከታለን ፀርከ የጥትም ግጭት ርክዘርህበፀ በ ሀከወካይ ተወካይ ሂደት ውስጥ የጥቅም ግጭቶች ሊፈጠሩ ይችላሉ ማለት ተወካይ በተሠጠው የውክልና ሥልጣን መሠረት የወካይን መብት በማስጠበቅና የራሱን የጥቅም በማስጠበቅ መካከል ግጭት ሊፈጠር ይችላል የፍብ ህቁ ገፀንእንደሚያብራራው ተወካይ ከኛ ወገን ጋር በፈፀመው ውል ምክንያት የወካዩና የተወካዩ ጥቀሞች የሚጋጩ የሆኑ እንደሆነና ይህን ውል የፈረመው ኛ ወገን ይህን ሁኔታ ያወቀና ሊያውቀውም የሚገባ የሆነ እንደሆነ በወካዩ ጥያቄ መሠረት ይህ በተወካይና በኛ ወገን መካከል የተፈፀመው ውል ሊፈርስ ይችላል እዚህ ጋር ተወካይ ከኛው ወገን ጋር የፈፀመው ውል ሲባል ተወካይ ከወካይ ባገኘው የውክልና ሥልጣን መሠረት ከኛ ወገኖች ጋር የገባቸውን ውሎችን ለማመልከት ነው ወካዩም ከላይ የተገለፀውን አይነት የጥቅም ግጭት መፈጠሩን ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ውሉን ለማፍረስ አሳቡን ማስታወቅ እንዳለበት የፍብህቁ ፖነይደነግጋል በዚህም መሠረት ወካዩ ውሉን የማፍረስ አሳቡን ቢያስውቅና ከተዋዋዩቹ መካከል አንዱ ማለትም ከተወካዩ ወይም ከኛው ወገን አንዳቸው የወካዩን ማስታወቂያ ከተቀበለ ወዲህ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ውሉን የመቀጠል አሳቡን ቢያሳውቅና ከተዋዋዬቹ መካከል አንዱ ማለትም ከተወካዩ ወይም ከኛው ወገን እንዳቸው የወካዩን ማስታወቂያ ከተቀበለ ወዲህ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ውሉን የመቀጠል አሳቡን ያልገለፁ እንደሆነ ውሉ ይፈርሳል የፍብህቁ እዚህ ጋር ግን ሊነሣ የሚችል ነጥብ አለ እሱም የጥቅም ግጭት መኖሩ ተረጋግጦ ኛው ወገንም ይህን የጥቅም ግጭት ያወቀው መሆኑ ሲረጋገጥና ወካዩ በፍብህቁር መሠረት የውል መፍረስ ሃሳቡን ቢያሳውቅ እንዲሁም በፍህቁ ፀፖር መሠረት ኛው ወገን የውሉን መቀጠል መፈለጉን ቢያሳውቅ የወካዩንና የኛው ወገን ፍላጐት እንዴት እኩል ማስኬድ ይችላል የሚለው ጉዳይ ነው በዚህ አይነት ሁኔታ ነገሩ ወደ ፍርድ ቤት ነው ማምራት ያለበት ፍርድ ቤቱም በፍብህቁ ፖርገን መሠረት የነገሮችን ሁኔታ አይቶ ውሉን ሊያፈርሰው ይችላል ምክንያቱም ፍህቁ ፀን ስንመለከተው የጥቅም ግጭት በሚፈጠርበት ጊዜ ውሉ መፍረስ አለበት ሳይሆን ሊፈርስ ይችላል ነው የሚለው ይህ ማለት ደግሞ ውሉ የመፍረስ ያለመፍረስም ዕድል እንዳለው ያመለክታል ነገር ግን ተወካዩ የራሱን ጥቅም አስቀድሞ የወካዩን ጥቅም የሚጐዳ ሥራ ስለሰራ በፍብህቁ የተጣለበትን ግዴታ አልተወጣም ማለት ነው ስለሆነም ወካዩ ያጣቸውን ጥቅሞች በህጉ መሠረት የማግኘት መብት ይኖረዋል ያም የሚሆነው አንድ ውል ሲፈርስ ተከትለው የሚመጡትን መብቶች መሠረት አድርጐ ነው ከራስ ጋር መዋዋል ዐበከ ህቪከ ዐበኗቨ ከራስ ጋር መዋዋል ማለት ተወካይ ለራሱ ጉዳይ በመሥራትም ሆነ ወይም በሌላ ሰው ስም ለሌላ ሰው ጉዳይ ለመሠራት ውሉን ከራሱ ጋር ሲያደርግ ነው ፍብቁፀ ይህ ማለት ከራስ ጋር መዋዋል በሁለት መልኩ ሊፈጠር ይችላል ማለት ነው ይህን በምሣሌ ብናያው በቀላሉ መረዳት ይቻላል የመጀመሪያው አንድ ወካይ ተወካዩን የሆነ ዕቃ እንዲሸጥለት ውክልና ቢሰጠውና ያን ዕቃ ተወካዩ ራሱ ቢገዛው ተወካዩ ከራሱ ጋር የሺያጭ ውል ተዋዋለ ማለት ነው ሁለተኛው ደግሞ አንድ ሰው ለሁለት ወካዬች ተወካይ ቢሆን ማለትም ከሁለቱም ወካዬች የውክልና ስልጣን ቢያገኝና አንድኛው ወካይ የሆነ ዕቃ እንዲሸጥለት ቢያዘው ያኛው ወካይ ደግሞ ተመሣሣይ ዕቃ እንዲገዛለት ቢያዘው ያኛው ሽጥልኝ ያለውን ለዚህኛው ወካይ ቢሸጥለት ለሁለቱም ተወካይ ራሱ ስለሆነ ውሉን ከራሱ ጋር እንደተዋለለ ይቆጠራል ማለት ነው ስለዚህ በሁለቱም ሁኔታ ተወካይ ይህን ባደረገ ጊዜ ወካዩ ይህ ውል እንዲፈርስ ለመጠየቅ ይችላል ፍብህቁ ገን የወካይ ሀሳቡን የማፍረስ ጥያቄ ማሣወቅና የመፍረሱ ሁኔታ ከላይ በጥቅም ግጭት ላይ እንደተብራራው ነው የሚሆነው ወይንም በሌላ አነጋገር በፍህቁ። ህዐበ ክዐህሃ አንድ ተወካይ በተሰጠው የውክልና ስልጣን ሊሰራው ከሚገባው ተግባር ባሻጋር ሌላ ወካዩ ዚን ሞ ተወ ተግባር ቢኩናውን ወ ገ ነ ሾኮፅጠውን የውክልና ሥልጣን ያለአግባብ ተጠቅሟል ሊባል ይችላል። ጄሠሇደግሞ ተወካዩ የተጣለበትን አደራ በአግባቡ አለመወጣቱን ያሣያል የተሰራውን ስራ በተመለከተ ደግሞ ወኪሉ ተወካዩ የፈፀመውን ተግባር ማፅደቅ ወይም ውድቅ ማድረግ ይችላል ፍትህ ብሄር ሕግ ቁ በአጠቃላይ ግን የተሰጠውን የውክልና ስልጣን ያለአግባብ የተጠቀመ ተወካይ በፍትሃ ብሄር ሕግ ከአንቀፅ ዐ በሠፈረው መልኩ የሚገዛ ይሆናል ጊዜው ባለፈበት የውክልና ሥልጣን መገልገል አንድ ተወካይ የተሰጠው የውክልና ስልጣን ዘመን ካበቃ በኋላ ወይንም የውክልናው ሥልጣን ከተሻረ በኋላ በውክልናው ሥልጣን የሚገለገል ከሆነ ጊዜው ባለፈበት የውክልና ሥልጣን ተገልግሏል ለማለት ያስችላል በተሻረ የውክልናው ስልጣን አማካኝነት የተሰራውን ስራ ደግሞ ወካይ ሊያፀድቀው ወይንም ሊሽረው ይችላል ፍትሃብሄር ሕግ ቀ ። የዚህን አይነት ስህተት የፈፀመ ተወካይም ከላይ በተጠቀሱት የህጉ አንቀፆች መሰረት ማለትም በፍትሃብሄር ሕግ ከአንቀፅ በሠፈረው መልኩ የሚገዛ ይሆናል ዕውክልናሥጳጣን መቅረት ወይም መቋረጥ የውክልና ሥልጣን ከዚህ በታች በተቀመጡት ሶስት ምክንያቶች መሠረት ሊቀር ወይንም ሊቋረጥ ይችላል እነሱም የውክልናን ሥልጣን በወካዩ መሻር የተወካዩ የውክልና ሥልጣኑን መተው ኀ የወካዩ ወይም የተወካዩ መሞት ከአካባቢ መጥፋት ለመሥራት ችሎታ አቅም ማጣት ወይም በንግድ መክሰር » ያውክልጂናው ሥሷጣን በወካዩ መጃ አንድ ወካይ ለተወካይ የሠጠውን የውክልና ሥልጣን በፈለገው ጊዜ መሻር እንደሚችል እንዲሁም ተወካዩ የውክልና ሥልጣኑን የተቀበለበትን የውል ፅሁፍ እንዲመልስለት ሊያስገድደው እንደሚችል የፍብህ አንቀፅ ደንግጓል በሌላ መልኩ ደግሞ ይህን የውክልና ሥልጣንን በፈለገ ጊዜ የመሻር መብት ሊቃረን የሚችል ቃል በውላቸው ውስጥ ቢያካትቱ ቃሉ ፈራሸ እንደሚሆን በዚሁ የሕግ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ላይ በገልፅ ተደንግጓል ወካዩ የውክልና ሥልጣኑን ለመሻር ለተወካዩ ምንም አይነት በቂ ምክንያትም ማቅረብ ሆነ ቅድመ ማሥጠንቀቂያ መስጠት አይጠበቅበትም መሻር በፈለገ ጊዜ ብቻ መሻር ይችላል ነገር ግን የውክልናው ሥልጣን የተሠጠው በብዙ ወካዮች ከሆነ የውክልናውን ስልጣን በአንዱ ወኪል ብቻ ለመሻር በቂ ምክንያት ከሌለ በስተቀር የውክልናውን ስልጣን ለመሻር ሁሉም ወካዮች መሥማማት አለባቸው በቂ ምክኒያት በሌለበት ሁኔታ ግን አንዱ ወካይ ብቻውን ተወካዩን ሊሽረው አይችልም ፍብህቁ እንግዲህ በዚህ መልኩ የውክልና ሥልጣን ከተሻረ በውክልናው ስልጣን መሻር ምክንያት የውክልናው ሥልጣን ይቀራል ወይም ይቋረጣል ማለት ነው ነገር ግን የውክልናው መሻር በተወካይ ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በፍብህቁ ኃኃያ መሠረት ወካዩ ለተወካዩ የጉዳት ኪሣራ መክፈል አለበት የወካዩ የውክልና ሰፈጳጣኑን መተው ተወካዩ የውክልና ሥልጣኑን ካልፈለገ በማንኛውም ጊዜ የውክልና ሥራውን ትቻለሁ ሲል ለወካዩ ማሳወቅ ይችላል ለወካዩ ሣያሣውቅ ግን የውክልና ሥራውን መተው የለበትም። ሠ በሌላ በኩል ወካይ የሞተ እነደሆነ በሥፍራው አለመኖሩ የተረጋገጠ እንደሆነ ለመሥራት ችሎታ ያጣ እንደሆነወይም በንግድ መውደቅ ኪሣራ የደረሰበት እንደሆነ የውክልና ሥልጣኑ ወዲያውኑ ይቀራል ይህ በእንዲህ እንዳለ ከላይ እንደተባለው እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎች ቢከሰቱም የውክልና ሥልጣኑ ቀሪ እንዳይሆን የሚገልፅ በውክልና ውሉ ውስጥ ተቃራኒ የውል ቃል ካለ ግን በወካዩ ላይ የደረሰው ክስተት የውክልና ሥልጣኑን ቀሪ አያደርገውም የፍብህቁ በዚህ ጊዜ ግን ተወካዩ ይህ ክስተት እስኪነገረው ድረስ ስራውን መቀጠል አለበትፍብህቁ ወካይ ተወካይና ያውክልሷና ማሰረጃውን የሟሰቋጡ ጳዛካሎቸች ምንም እንኳ ብዙ ሰዎች በአንድም ሆነ በተለያየ ምክንያት ስራቸውን በውክልና ቢያሰሩም ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ተገልጋዮች ግንዛቤያቸው እጅግ በጣም ውስን መሆኑንና ውክልና ከመስጠት ሂደት ጋር ተያይዞ ብዙ ክፍተቶች እንዳሉ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽቤት ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ ባለሙያዎች ይናገራሉበ በወካዮች በኩል ያሉትን ክፍተቶች ስንመለከት ሠነድ አሟልቶ አለመገኘት ለተወካይ የሚሰጡ መብቶች የሚያስከትሉትን ውጤት ቀድሞ ያለ መረዳት ለተወካይ ሊሰጡ ያሰቡትን መብቶች በውል ያለ መረዳት ጉዳዩን ያለማወቅ ማለትም ስለሚሰጡት ውክልና የግንዛቤ እጥረት መኖር የተወካይን ሥነምግባር ያለማወቅ ለተወካይ የሚሠጧቸውን መብቶች በይሉኝታ ለተወካይ ሙሉ በሙሉ አሣልፎ መስጠት ለተወካይ ሊሰጥ የታሰበውን የውክልና ስልጣን ማሰረጃ ሠነድ ይዘት በቸልተኝነት መመልከት በጥንቃቄ ያለመረዳትን የውክልናን ክብደት ካለመረዳት በግዴለሸነት ውክልናን በመስጠት ለአደጋ መጋለጥ ዋነኞቹ ክፍተቶች ናቸው በመሆኑም ወካይ የሚከተሉትን የጥንቃቄ እርምጃዎችን መከተል አለበት የተወካይ ማንነት እና የሥነምግባር ሁኔታ ጠንቅቆ ማወቅ የተወካይ የግል ባህሪና የስራ እንቅስቃሴ ሁኔታን ወካይ በውል ማወቅ ይኖርበታል ምናልባትም ተወካይ የግል ጥቅም አገኝበታለሁ ብቻ ብሎ ከዚህም ባሻገር የተወካዩን ጥቅም ለመጉዳት በማሰብም ጭምር ሊሆን ይችላል የውክልናውን ስልጣን የሚቀበለው የወካዩን ጥቅም ለመጉዳት አስቦ የተነሳ ወይንም ለራሱ ጥቅም ሲል ብቻ የውክልና ስልጣኑን የሚቀበል አይነት ሰው እንኳን ባይሆን በውክልና የተቀመጡትን ተግባሮች በአግባቡ ሊያከናውን የማያስችል ስነ ምግባር ወይም ተግባሮቹን ባልተፈለገ ሁኔታ ሊያከናውናቸው የሚያስችል ስነ ምግባር የተላበሰ አይነት ሰው ሊሆን ስለሚችል ጥንቃቄ መውሰድ ተገቢ ነው ስለዚህ በተለይ ተወካዩ ከውክልና ስልጣኑ ጋር ተያይዞ ሊኖረው የሚችለውን የተለየ ግንኙነት ወካይ በአትኩሮት በመመልከት ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ወካይ ለተወካይ የሚሠጣቸውን መብቶች እና የሚያስከትሉትን ውጤት ማለትም በሕግ መነሻ የሚያስከትሉን ውጤት በሚመለከት ግንዛቤ ማዳበር ህዐበ ዐሀ ፐፎፀፀቋበባ ርከጪከበፀ። ሠካይ ዲነ መያሰባቸው መብቶች ከሕግ አንፃር ምን አይነት ውጤት ሊያስከትሮድቹኝጅይሚችሉ ብሎም በራሱ ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ ሊኖራቸው እንደሚችል አስቀድሞ ማጤንና መገንዘብ ይኖርበታል ወካይ ለተወካይ የሚሠጣቸውን መብቶች መጠን ቀድሞ መለየት ብዙ ጊዜ የውክልና ውል ሊዋዋሉ ወደ ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽቤት የሚያመሩ ወካዮች የውክልናውን ፎርም የሚወስዱት በጽቤቱ አካባቢ ከሚገኙ የጽህፈት ስራ ከሚሰሩ የንግድ ቤቶች አንዴ ተፅፎ የተቀመጠ የውክልና ፎርምን ነውሳ ይህ አካሄድ ደግሞ የተቀመጠው ፎርም አንድ ወካይ ለተወካይ ሊሰጣቸው የሚችሉ የውክልና ስልጣን አጠቃላይ ዝርዝር የያዘ በመሆኑ ወካይ ለተወካይ በውክልና ስልጣን ሊሰጠው ካሰበው የስልጣን ወሰን በላይ ተጨማሪ ስልጣን ከመስጠቱም በላይ ተወካይ ወደ ተግባር ሲገባ ወካይ ከሚገምተው በላይ ጉዳት በወካይ ላይ ሊያስከትልበት እንደሚችል ግልፅ ነው ስለዚህ ወካዮች ፎርሙን ቀጥታ ከመጠቀም ይልቅ በራሳቸው ፍላጎት ማሻሻያ እንዲደረግበት በማድረግ የፈለጉትን የስልጣን ወሰን ብቻ ለተወካይ እንዲተላለፍ ማድረግ ይችላሉ አንዳንድ ስነምግባር የጎደላቸውና ለግል ጥቅማቸው ብቻ የቆሙ ተወካዮች ደግሞ ማንበብ በማይችሉ ወካዮች ላይ የወካዮቹን አለማንበብ እንደጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ በውክልና ስልጣኑ ላይ የሚፈልጉት ነገር እንዲፃፍ የሚያደርጉበት ሁኔታ አለከ በመሆኑም ማንበብ የማይችሉ ወካዮች እንደዚህ አይነት ክፍተቶችን ለመሙላት አንድም የኔ የሚሉት ሰው በውሉ ጊዜ አብሯቸው እንዲሆን ማድረግ ወይንም የሚያዋውለውን ባለስልጣን የውክልና ውሉን ሰነድ እንዲያነብላቸው መጠየቅ ይኖርባቸዋል በአጠቃላይ በተዘጋጀው የውክልና ስልጣን ሠነድ ላይ የተካተቱ ይዘቶችን በሚገባ መረዳት ማወቅ ማለትም ማንበብ ወይም ማስነበብ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ካሉ ጠይቆ ለመረዳት መቻል ተገቢ ነው ወካይ በሠጣቸው የውክልና ስልጣን እና መብቶች መነሻ የተወካይን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ለመከታተል የሚያመች ሥርዓት በተቻለ መጠን መዘርጋት ለምሣሌ የሚሠሩ ስራዎች ሪፖርት መቀበል እና በአግባቡ ለተፈፀሙ ተግባሮች ይሁንታ መስጠት እና ማስተካከያ ለሚሹ ተገቢ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማድረግ የእለት ተእለት እንቅስቃሴን መከታተል አንድም የተከሰቱ ችግሮች ካሉ ለማወቅና ተገቢውን እርምጃ ወይንም ማስተካከያ ለመውሰድ በሌላ በኩል ደግሞ ሌላ ተጨማሪ ችግሮችና ክፍተቶች እንዳይፈጠሩ ቅድመ ጥንቃቄ ለመውሰድ ይረዳል ከዚህም ባለፈ ተወካይ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በወካይ ላይ ጉዳት አድርሶ ከሆነ ሌላ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ ወካይ የውክልናውን ስልጣን የመሻር እርምጃ እንዲወስድ ይረዳዋል ስለሆነም የወካይ የተወካይን አንቅስቃሴ መከታተል ብሎም ሪፖርት መቀበል ተገቢና አስፈላጊ ነው በሌላ በኩል ደግሞ የሰውን ንብረት ለመውሰድ ህጋዊ ያልሆኑ ሰነዶች ወይንም የርፀበ ፅዕርዕሀበባፀበ ይዞ የመምጣት ሁኔታም ይታያልቬበ በብዛት የተጭበረበረ ሠነድ በተለይም የሶስተኛ ወገን ሙሉ መታወቂያ ካርታ ለዚሁም አስመስለው የሚሠሩት እንዳለ ሆኖ ማለት ነው ይዞ ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽቤት የመሄድ ሁኔታዎች ይከሰታሉከክ ለዚህም የመንግስታዊ ተቋማት ወጥ ያልሆነ አሠራር የችግሩ ማባባሻ እንደሆነ ይታመናልኩዝ ለምሳሌ ከቀበሌ መስተዳድሮች ከሚሠጡ መታወቂያዎች ጋር በተያያዘ በሃሠተኛ የማንንት ማረጋገጫ መታወቂያዎች ለመገልገል የሚመጡ ባለጉዳዮች አሉሀቧ ከዚህም ጋር ተያይዞ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽቤት በሕግ አግባብ ተረጋግጠው ያልተመዘገቡ ሀሠተኛ የውክልና ስልጣን ማስረጃዎች በመያዝ እጅ ከፍንጅ የሚያዙ ባለጉዳዮች በፈፀሙት ወንጀል አሰተማሪ እና ተመጣጣኝ ቅጣት ለማሠጠት ጽቤቱ ከፖሊስ ከአቃቤ ሕግ እና ከፍቤቶች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ለመረዳት ተችሏል በተወካይ በኩል ያለውን ክፍተት ስንመለከት ደግሞ የተሠጠውን መብት ወይም ስልጣን ወካይን በሚጐዳ መልኩ ያላግባብ መጠቀም አልፎ አልፎ የወካይን ጥቅም ለማስጠበቅ ቸልተኛ መሆን ስለሚፈጽማቸው ስለሚያከናውናቸውን ጉዳዬች ለወካይ ሪፖርት ያለማድረግ የጥቅም ግጭት የሚያስከትሉ ጉዳዮችን በውል ያለመረዳት እንደ ወካይ ሆኖ በተሠጠው መብት ስልጣን መሠረት በቂ በሆኑ ምክኒያቶች ተግባሮችን ያለመፈፀም እና ተግባሮቹ የሚያስከትሉትን ውጤት ያለ መረዳት ውክልናውን ቶሎ የማግኘት ጉጉት ማሳየት እና ሠነድ ባለመሟላት ህዐበ ዐሀ ፐፎፀፀቋበባ ርከጪከበፀ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact