Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

ስሑት_አስተምህሮዎችና_ምግባራዊ_ዝንፈቶች.pdf


  • word cloud

ስሑት_አስተምህሮዎችና_ምግባራዊ_ዝንፈቶች.pdf
  • Extraction Summary

ስሑት አስተምህሮዎችና የተዛነፉ ምግባራዊ ልምምዶች ነበሩ በተለያዩ ወቅቶች ተከሥተው የነበሩ የስሕተት አስተምህሮዎችና ምግባራዊ ዝንፈቶች ምን እንደሚመስሉ ከማየታችን በፊት በወቅቱ የነበረውን አስተዳደራዊ ሥርዐትና በአስተምህሮው ላይ ያለውን ግንዛቤ ቀረብ ብሎ መገንዘብ ጠቃሚ ይሆናል የችግሮቹን ምንጭ እንዲሁም የችግሮቹን ዐውድ በአግባቡ መረዳት ችግሮቹን በውል ለመረዳት ትልቅ ዕገዛ ያደርጋል ከ ዎቹ መጨረሻ አንሥቶ እንቅስቃሴውን በቅርብ ሆኖ ለመከታተልና በአገልግሎቱ ውስጥ ለመሳተፍ የቻሉ ሁሉ የችግሮቹን ሁኔታ በቅርብ ለመመርመር ዕድል አግኝተዋል የሚል ግምት አለ የአርነት ትምህርትዐዩኩዩሺፐካርፍ ይህን ትምህርት ከምንጩ ለማወቅና ለመረዳት በወቅቱ በካናዳና በአሜሪካ ይገኙ ከነበሩት የትምህርቱ አመንጪዎች ጋር በመጻጻፍ የሚያስተምሩባቸውን አብዛኛውን መጻሕፍትና ከመቶ በላይ የሆነ በካሴት የተዘጋጁ ትምህርቶችን ለማሰባሰብ ተቸሎ ነበር በተጨማሪም በስካዲኒቭያን አገሮች የሚገኙ የጴንጤቆስጤ እምነት ተከታዮች ኅብረት በአርነት ትምህርት ላይ የቀረቡትን መረጃዎችና ትምህርቶች በወቅቱ ገፍቶ ለመሄድ ወይም ቆሞ በይፋ ለመከራከር የደፈሩ ብዙዎች አልነበሩም ቤተ ክርስቲያንን ከፍሎ የመውጣት እቅዳቸውም በብዙ ሥፍራ ሳይሠምር ቀርቶአል የአርባ ቀን ጾምና በእሳት መጠመቅና መንጻት ይህም ትምህርት አንደሌሎቹ ከውጭ የተቀዳ ነበር አራሳቸውን በዚህ ልምምድ ውስጥ በማሳለፍ አርባ ቀን ለመጾም ሲሞከሩ እስከሞት የደረሱ ለአእምሮ ሕመምተኛነት የተዳረጉ የሌሎችም በሽታዎች ሰለባ የሆኑ ትምህርታቸውንና ሥራቸውን አቋርጠው በሚያሳዝን ሁኔታ ተንከራታች ሆነው የቀሩ በቅርብ የምናስታውሳቸው በርካታ የዚህ እምነት ተከታይ ወጣቶች ነበሩ ይህ ትምህርት በቅድስናና በጽድቅ ስም ይሰጥ ስለነበረ ጭፍን መንፈሳዊ ቅናት የነበራቸው በርካታ ወጣቶች ሕይወት ተከስቶ የነበረውን ፈተናና አደጋ ሲያስቡ ዛሬ ድረስ ከፍተኛ ጸጸትና ሐዘን ይሰማቸዋል እንግዲህ አነዚህና ሌሎችም በየጊዜው ብቅ ብቅ እያሉ የታዩ የስሕተት ትምህርቶች በአብዛኛው ምንጫቸውና መነሻቸው ከውጭ ቢሆንም በሀገራችን በፍጥነት እንዲሠራጩ ዕድል የሰጣቸው የምዕመኑ ብልህነት የሌለበት የዋህነት እውቀት የጎደለው ቅናትና እንዲሁም እረኛ አስተማሪና መሪ የማጣት ችግር እንደነበረ በግልጽ ይታወሳል እነዚህን የቀደሙ ችግሮችና በቅርብም ባለፉት ዐሥርና ዐሥራ አምስት ዓመታት እየጨመሩ የመጡትን የሐሰት ትንቢቶችና የብልጽግና ወንጌል ስብከቶች በሚመለከት አንዳንዶች የሚያሳስባቸውና በቤተ ከርስቲያን ውስጥ ሊመጣ የሚችለው አንዴት ነው።

  • Cosine Similarity

ስሑት አስተምህሮዎችና ምግባራዊ ዝንፈቶች ከንጉዔ ተፈራ ዶክተር ኮልፌ ሙሉ ወንንጌል ቤተ ክርስቲያን በዐቅብተ እምነት ላይ ባዘጋጀችው አገር ዐቀፍ ዐውደ ጥናት ላይ የቀረበ ጽሑፍ መግቢያ ይህ ጽሑፍ በአብዛኛው ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ካጋጠሙ አንዳንድ ስሑት አስተምህሮዎችና ምግባራዊ ዝንፈቶች አኳያ የራሴን የሕይወት የልምድ ተመከሮ የሚገልጽ በአንጻሩ የተማርኋቸው ትምህርቶች ምን እንደ ሆኑ የሚያትት ይሆናል ጽሑፉ በጊዜው የችግሮቻችን ምንጭና ይህም እንዲባባስ አስተዋጽኦ ያደረጉ ቅድመ ሁኔታዎች ምን አንደ ነበሩ በአጭር ዳሰሳ ያስቃኛል ተሞከሯዊ ትምህርቶችንም ለመንቀስ ይሞከራል በመጨረሻም ካለፈው በመነሣት ዛሬም ለስሕተት ትምህርቶች የሚዳርጉን መሠረታዊ ችግሮቻች ምን እንደ ሆኑ አንዳንድ አስተያየቶችን በመስጠት ያጠቃለላል በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት ታሪከ ውስጥ ያለፉት ሃምሳ ዓመታት የተለየ መነቃቃት ወይም የተለየ የመንፈስ ጐብኝት የታየባቸው ወቅቶች ነበሩ ሊባል የሚቸል ይመስለኛል ከሃምሳ ዓመት በፊት የነበረውን ሁኔታ ካዛ ወዲህ ከተፈጠረው ከሥተት ጋር ለሚያነጻጽር ሁሉ ልዩነቱን ለመገንዘብ የሚያስቸግረው አይመስለኝም በዎቹ መጨረሻና በዎቹ መጀመሪያ ላይ በነበሩት ዓመታት ብዙዎች በተለየ መንገድ ወደ እግዚብሔር መንግሥት የተጨመሩበት በተለይ ወጣቱ ልዩ በሆነ መንፈሳዊ መነቃቃት ውስጥ የገባበትና በተፈጠረውም መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሆነበት የተለየ ጊዜ ነበር ለማለት ይቻላል ይህ የመንፈስ ቅዱስ አንቅስቃሴ እሳት ለበርካታ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትና የመንፈስ ተሐድሶ ያመጣ ብቻ ሳይሆን በበርካታ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በኮሌጆችና በተለይም በመምህራን ማሠልጠኛ ተቋማት ውስጥ የነበሩ ተማሪዎችና መምህራን በእሳቱ ወላፈን ሊቀጣጠሉ የቻሉበትና እግዚአብሔርም በተለየ መንገድ መከበር የጀመረበት ታሪካዊ ጊዜ ነበር በአጠቃላይ ጊዜው በወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት መካከል የመንፈስ ቅዱስ ሙላትና የጸጋ ስጦታዎች ጉዳይ እንዱ ዋና አጀንዳ ተደርጎ መታየት የጀመረበት አዲስ የታሪከ ምዕራፍ ነበር ማለት ይቻላል ይህ ከደርግ ሥልጣን መያዝ ዐሥር ዓመት ቀደም ብሎ መንደድ የጀመረው የመንፈስ ቅዱስ እሳት በወጣቱ ሕይወት ውስጥ መታየት የጀመረው በተለየ የእግዚብሔር ፍቅርና ኀይል ዛሬ ተስፋፍተው ለምናያቸው በጎ መንፈሳዊ ሁኔታዎች ጥንስስ ነበሩ ማለት የሚቻል ይመስለኛል ይህ እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ማቀጣጠል የጀመረው እሳት በሚያምኑት ሕይወት እየተገለጠ የመጣው የቃሉ ብርታትና የእምነት ጽናት በደርግ የከሕደትና የስደት ዘመን ለነበሩ አብያተ ከርስቲያናትም ሆነ በስውር ፎክየዐሀክ እምነታቸውን ይለማመዱና አገልግሎታቸውንም ያከናወኑ ለነበሩ ሁሉ ኀይልና ብርታት እንደ ሆናቸው አናስታውሳለን የደርግ ዘመን የፈተናና የስደት ዘመን ቢሆንም የእግዚአብሔር ሥራ ሙሉ በሙሉ የተቋረጠበት ጊዜ አልነበረም ያ ወቅት ጥቂትም ሰዎች አንኳ ቢሆኑ ለአግዚአብሔር ስም በታማኝነት በቆሙት ሕይወት ለትውልድ የሚቆይና የሚቀጥል ሥራ የተሠራበት ጊዜ እንደ ነበር በውስጡ ያለፉ ሁሉ ይመሰከራሉ ይህ በእግዚአብሔር ጊዜና ፈቃድ የተጀመረው የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያውያን በስደቱ ምክንያት አገራቸውን ለቀው በተሰደዱባቸው አገሮችም ጭምር አብሮ የተጓዘና ለብዙዎች መጽናናትና ጽናት የሆነም ከሥተት ነው ከእግዚአብሔር ዘላላማዊ ዐላማ አንጻር እነዚህ ሁሉ ሐቆቸ በየአቅጣጫው በስውርና በይፋ ሲከናወኑ የታዩ አስደናቂ ከሥተቶች ቢሆንም በውስጥም በውጭም እምነታችንን በሚመለከት ችግር ወይም ተግዳሮት አልነበረበትም ሊባል ግን በጭራሽ አይቻልም ከቸግሮቹ መካከል አንዱና ጐልቶ ይታይ የነበረው ከርስቲያኖች የሚገባውን ያህል በቃሉ ያለመብሰላቸው ስሑት አስተምህሮዎችና የተዛነፉ ምግባራዊ ልምምዶች ነበሩ በተለያዩ ወቅቶች ተከሥተው የነበሩ የስሕተት አስተምህሮዎችና ምግባራዊ ዝንፈቶች ምን እንደሚመስሉ ከማየታችን በፊት በወቅቱ የነበረውን አስተዳደራዊ ሥርዐትና በአስተምህሮው ላይ ያለውን ግንዛቤ ቀረብ ብሎ መገንዘብ ጠቃሚ ይሆናል የችግሮቹን ምንጭ እንዲሁም የችግሮቹን ዐውድ በአግባቡ መረዳት ችግሮቹን በውል ለመረዳት ትልቅ ዕገዛ ያደርጋል ከ ዎቹ መጨረሻ አንሥቶ እንቅስቃሴውን በቅርብ ሆኖ ለመከታተልና በአገልግሎቱ ውስጥ ለመሳተፍ የቻሉ ሁሉ የችግሮቹን ሁኔታ በቅርብ ለመመርመር ዕድል አግኝተዋል የሚል ግምት አለኝ በመጀመሪያዎቹ ዐሥርት ዓመታት በወጣቱ ልብ ተማሪዎችም ይሁኑ አስተማሪዎች ለእግዚአብሔር ራሳቸውን አዘጋጅተው በእምነት ባቀረቡት መጠን አንዲያውም ከዚያ በላይ ጌታ የተጠቀመባቸው መሆኑ እሙን ቢሆንም ከመነሻው ጀምሮ ብዙዎች የቆሙበት የቃሉ መሠረት ጥብቅ ነበረ ማለት ግን አስቸጋሪ ነው ሁሉም ባይሆኑ እንኳ የመንፈስ ቅዱስ እሳት የጐበኛቸውና የአገልግሎቱን አመራር የጨበጡት ሰዎች አየተለማመዱ የነበረውን እምነትና አገልግሎት የሚመጥን የቃሉ እውነት መሠረት አልነበራቸውም ቢባል ስሕተት አይመስለኝም አብዛኛው ምዕመን ይመራ የነበረው ጥቂቶች በተገነዘቡትና በተረዱት ወይም በነበራቸው ልምምድና መገለጥ ላይ ተደግፎ እንጂ ቃሉን በሚገባ አንብቦና አመሳክሮ መረዳትን ይዞ ነበር ማለት አስቸጋሪ ነው በወቅቱ ማንም በእግዚአብሔር ስም ምንም ቢናገር በአብዛኛው አሜን ብሎ ከማዳነቅ ያለፈ ምላሽ አልነበረም በአብዛኛው በጊዜው የነበረው ትምህርት ያተኩር የነበረው በመንፈስ ቅዱስ ማንነትና በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ዙሪያ እንጂ በምዕመኑ ዘንድ የነበረው እምነትና አመለካከት በአብዛኛው የተወሰነ ከመሆኑም በላይ ሚዛናዊ ወይም ቃሉን መሠረት አድርጎ የቆመ እውነት አንዳልነበረ ይታወቃል በአንቅስቃሴው ሂደት በመሪነት ያገለግሉ ከነበሩት ወገኖች አብዛኛው ጌታን በአምነት ከመቀበል የመንፈስ ቅዱስ ሙላትና በልሳን መናገር ለበሽተኞች ከመጸለይና አጋንንትን ከማስወጣት ጋር የተያያዘ ልምምድ ከመሆኑ ባሻገር ረጋ ብለው በሰከነ መንገድ እምነታቸውንና አገልግሎታቸውን ከቃሉ ጋር በማመሳከር ለመማር የቻሉበት ዕድል አልነበረም የብዙዎቹ የአገልግሎት ኀይል በአብዛኛው የተቀበሉትና በውስጣቸው ይሰማናል የሚሉት የእግዚብሔር መንፈስ የሴሎች ምስክርነትና መገለጥ ስለመንፈስ ቅዱስ ሥራና የጸጋ ስጦታዎች ከተለያዩ ምንጮች ተጽፈው ካነበቡአቸው አንዳንድ ታሪኮች የመነጩ እንደ ነበሩ ይታወሳል በወቅቱ በቤተ ከርስቲያን አካባቢ የነበረው ወጣት ለእግዚአብሔር ከነበረው ፍቅር የመንፈስ ግለት የአገልግሎት ቅናትና ቅድስናን ከመፈለግ አኳያ ከውጭ ያገኘውንና በጥቂቱ ያነበበውን እንዲሁም መልካም መስሎ የሚታየውን ሁሉ በአምነት የመቀበልና የመለማመድ ዝንባሌው ከፍተኛ ነበር አብሮ መታየት ያለበት ሌላው ሁኔታ የመንፈስ ቅዱስ ጐብኝትና ሙላትን በሚመለከት በአገራችን የረዥም ጊዜ ታሪከና ልምምድ ያልነበረ በመሆኑ እንዲሁም በገዳዩ ላይ የጠራ ትምህርትም ሆነ የሰከነ አመራር የሚሰጡ በቂ መምህራን አገልጋዮች እንዲሁም ጠቃሚ መጻሕፍት አለመገኘታቸው ችግሩን አባብሶታል ወጣቱ በእግዚብሔር ስም የሚደረጉ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል የሚገለጡ አዳዲስ ከሥተቶችን በተለይም ድንቅና ተኣምራትን በቅንነት አብዝቶ ይናፍቅ የነበረ በመሆኑ ለስሕተት ትምህርት አደጋ መዳረጉ የማይቀር እንደ ነበረ ዛሬ ላይ ሆኖ የነበሩ ሁኔታዎችን ለሚገመግም ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል ስለሆነም ሁኔታው ወይም ችግሩ በተለያዩ ጊዜያት አዳዲስ የስሕተት ትምህርቶች የመምጣታቸው ገዳይ ብቻ ሳይሆን በጨበጥነው መሠረታውያን ትምህርቶች ላይም የጠራ አመለካከትና እርግጠኝነት የመጥፋት ችግር ነበር ሊባል ይቻላል ከዚሁ ጋራ በጊዜው ለቅድስናና ለዕድገት ዋና መለኪያዎች አድርገን ስንጠቀምባቸው የነበሩት ለምሳሌ ትንቢት በልሳን መናገር ጾምና ጸሎትን ማዝወተር ሰይጣንን አብዝቶ መገሠጽ አንዲሁም መሰል ልምምዶች ከፉኛ ለሚዋዥቅ አምነት ዳርጐን ነበር ማለት ይቻላል ቃሉን ማጥናት ዕውቀትንና ጥበብን መፈለግ የሚሉት መሠረታዊ የአምነት ማጽኛዎች ደግሞ እምብዛም ትኩረት ያልሰጠናቸው መሆኑ ጀምረነው የነበረውን የእውነት መንገድ በከፊል እንድንስት አድርጎናል በተጨማሪም በጊዜው ለመንፈሳዊ ዕድገት ለእግዚብሔር አገልግሎት ቃሉን የመማር የሥነ መለኮት ዕውቀት መጨበጥ ተግቶ መጻሕፍትን የማንበብና እውነቱን የማመሳከር አስፈላጊነት በአንዳንዶች ዘንድ እንደ ሥጋ ሥራ የተወሰደ በመሆኑ ሊፈጠሩ ለሚችሉ የስሕተት ትምህርት አደጋዎች በር እንዲከፈት አድርጎአል በተለይ ልጆችሽ ከአግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ መንፈስ ቅዱስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችትኋል የምትናገሩትንም ይሰጣችኋል የሚሉትን እንዲሁም አነዚህን መሰል ጥቅሶች ከዐውዳቸው በማፋታትና እጅግ በመለጠጥ የመማርን ወሳኝ ጐዞ ከፉኛ አደናቅፎት ኖሯል በወቅቱ የአግዚአብሔርን ሥራ ለመሥራት ቃሉን መማርና የሥነ መለኮት ዕውቀታችንን ማስፋት ግድ ይላል ለሚለው ጥሪ በተቃርኖ ይሰጥ የነበረው ምላሽ ይታይ የነበረው የተሳሳተ አመለካከት ዐልፎ ዐልፎም ይሰማ የነበረው ስሜትና ቅናት ለቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት የተሳሳተ እንዲጐለብት አድርጓል ለምሳሌ አገልግሎትንና መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት መግባትን በሚመለከት ይቀርቡ ከነበሩ ከርክሮች መካከል እኛ የእግዚብሔርን ሥራ እንደመሥራታችን ለእግዚአብሔር ሥራ የሰው ዕውቀት ጥበብ መማር አስፈላጊ አይደለም የሥራው ባለቤት አግዚአብሔር የእውቀት ሁሉ ምንጭ ስለሆነ ሳንማር እርሱ በቀጥታ በቃሉ ዕውቀት ይሞላናል እኛ መታዘዝ እንጂ መማር አይጠበቅብንም በሁሉም እግዚአብሔር ይረዳናል እግዚአብሔር የሰው ልጅ የዕውቀት ድጋፍ ወይም እገዛ አያስፈልገውም የአግዚአብሔር አገልግሎት እግዚአብሔር እራሱ የሚሠራው እንጂ የእኛ ዕውቀት ፋይዳ የለውም እግዚአብሔር ቀጥታ በውስጣችን ይናገራል አምላካችን የሰዎች ጥበብ ያፈለቀውን የሥነመለኮትን ትምህርት ድጋፍ አይሻም በቃሉ ላይ የተጻፈው ልጆቾሽ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ የሚል ነው እንጂ ሴሚናሪ ገብታቸሁ ትማራላችሁ የሚል አይደለም መንፈስ ቅዱስ ሁሉ በሁሉ ምሉዕ ነው እኛ የታዘዝነው መንፈስ ቅዱስን ጠብቁ የምትናገሩትን እሱ ይሰጣችኋል የሚል ነው እንጂ ቲዮሎጂ ትምህርት ቤት ገብታችሁ ተማሩ አልተባልንም የሚቀባንና አገልጋይ የሚያደርገን የጸጋ ስጦታዎችን የሚሰጠንና አንደበታችንን የሚከፍተው መንፈስ ቅዱስ በቀጥታ ነው መንፈስ ቅዱስ የሰው ድጋፍ አይፈልግም ለአገልግሎት ዋና ነገር በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተን በልሳን መናገራችንን ማረጋገጥ ብቻ ነው የእግዚአብሔርን ሥራ እሠራለሁ ብሎ ቲዎሎጂ መማር የእምነት ማነስና መንፈስ ቅዱስን ማሳዘን ነው። መጽሐፍ ቅዱስንም በተመለከተ ቃሉ የእግዚአብሔር እስትንፋስ እንደመሆኑ በራሱ ኀይል አለው ቃሉ ሲከፈት መንፈስ ቅዱስ የሚገልጠው ስለሆነ አስተማሪና ተርጓሚ አያስፈልገውም ቃሉን በእምነትና በድፍረት መግለጥና መናገር ብቻ ነው መጽሐፍ ቅዱስ እኛ ትምህርት ቤት ገብተን አጥንተን የምንተርከው ሳይሆን ራሱ ሲገለጥ መንፈስ ቅዱስ በልባችን ውስጥ የሚሞላው እውነት ነው በአጠቃላይ መጽሐፍ ቅዱስ ገላጭ አስተማሪ ወይም ቲዎሎጂያን አይፈልግም የሚል ነበር ይህ የሁሉ አስተሳሰብ ነበር ባይባልም በአብዛኛው ሕዝብ አእምሮ ላይ ተጽዕኖ ያደረገ ትምህርት መሆኑ ግን አጠራጣሪ አልነበረም ስለሆነም አለማወቅ የገዘፈበት ወቅት ብቻ ሳይሆን አለማወቅ የአበበበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል በ ዓም ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁለት የቤተ ከርስቲያናችን ወንጌላውያን ኬንያ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ገብተው እንዲማሩ የተገኘላቸው ዕድል ትልቅ ቁጣ እንደቀሰቀሰ አስታውሳለሁ በወርሃዊ የአባላት ስብሰባ ላይ ከቀረቡት የመወያያ አጀንዳዎች አንዱ መንፈስ ቅዱስ ሙሉ ወንጌልን ለቆ መቼ እንደሄደና ቅባቱ መቼ እንደቆመ መንፈስ ቅዱስን ጠብቁ የሚለው ቃል ቲዮሎጂ ትምህርት ቤት ገብታችሁ ንቁና ታጠቁ በሚለው መቼ እንደተተካ ተማሩ እያሱ የሚገፋፉን ወገኖች ይጠየቁልን የሚል ነበረ እነዚህን የሚመሳስሉ የተሳሳተ አመለካከቶች ለብዙ የስሕተት ትምህርቶች ሲዳርጉን ቆይተዋል በአእምሮ መታደስ ከሚገኝ መለወጥና እድገት አርቆናል ይህ ዐይነቱ የዋህነትና አለማወቅ ለመንፈሳዊ ሕይወት ኪሣራና ከመከፋፈል ደረጃ አድርሶናል እንግዲህ የስሕተት ትምህርትን አመጣጥ ጉዳይ ስናነሣ በተለያዩ መንገዶች ገብተው እምነታችንን በመበረዝና በማጣመም የተገለጡትንና የምናውቃቸውን ብቻ ሳይሆን በውስጣችን ለረዥም ጊዜ ኖረው በድፍረት ልንገልጣቸው ያልቻልነው ቃሉን አለማወቅ የመማር ፍላጎት ማጣት ጭፍን እምነት በስሜት መመራትንና ባዶ ቅናት የመሳሰሉትን ማጤንና በምዕመኑ ላይ አምጥተው የነበሩትን አሉታዊ ተጽዕኖ መረዳት የሚያሻ ይሆናል እንግዲህ ላጋጠሙት ማንኛውም የስሕተት ትምህርቶችና የአስተምህሮ ዝንፈቶች እነኝህ ሁኔታዎች በከፊል በር ከፋች ነበሩ ማለትም ይቻላል የስሕተት ትምህርትን በወቅቱ በመቀበልና በማስተላለፍ የምናስታውሳቸው አንዳንድ አገልጋዮችንም ሁኔታ ስናስብ ከቃሉ ይልቅ በስሜታቸውና በመገለጥ አብዝተው የሚደገፉ ከሐሣባቸው ጋር የሚስማማ አንድ መጽሐፍ ባነበቡ ቁጥር ሁሉን እውነት አድርጎ የመቀበልና ኮፒ አድርጎ የማስተማር ዝንባሌ የነበራቸው እንደሆኑ እንረዳለን አንዳንዶቹ ትምህርቶቹን የራሳቸው መገለጥ አድርገው ለመናገር ቢቃጣቸውም በአብዛኛው በአሜሪካ ካናዳና እንግሊዝ አገር ከነበሩ ልምምዶች የተቀዱ ወይም ቃል በቃል የተገለበጡ እንደነበሩ በጥናት ለማረጋገጥ ተችሎአል በኢየሱስ ስም ብቻ ርክከ በሀገራችን የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴና አገልግሎት አየሰፋ መምጣት በጀመረባቸው ዐዎቹ መጀመሪያ ዓመታት ላይ የመጣው ወይም የተከሰተው የርክከ ትምህርት ተቀባይነት አግኝቶ መስፋፋት የጀመረው አጉል ስሜትና ያልተጨበጠ ቅናት ይገዛቸው በነበሩ የዘወትር ትምህርታቸውና ቅኝታቸው መገለጥ ብቻ ከነበረና ከቃሉ እውነት ተፋተው ከቆዩ ወንጌላውያን እንደነበር እናስታውላን በተለይ ለዚህ ትምህርት መሠራጨት ዋና ምከንያት የሆነው ወንጌላዊ ብዙውን ጊዜ የተለየ ድምፅ ይሰማኛል ተገለጠልኝ የሚሉ ግራ የሚያጋቡ ሁኔታዎችን በድፍረት መናገርና ምእመኑን በትንቢት ስም የመጫን ባሕርይ የነበረው ግለሰብ መሆኑ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል የዘነ ትምህርት በተከሰተበት ወቅት የትምህርቱን ተቀባይና አስተማሪ እንዲሁም ለእርሱ የመሰከሩለትን ሁለት አሜሪካውያን ሚሽነሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ለማነጋገር ጥረት ተደርጎአል ብዙውን ጊዜ መልሳቸው አግዚአብሔር በመገለጥ ካላሳያችሁ በስተቀር በቃሉ ላይ ብቻ በሚደረግ ውይይትና ከርከር መረዳት አትቸሉም የሚል ነበር ወደዚህ ትምህርት የገባው ወንጌላዊም ቢሆን በኋላ መረዳት እንደተቻለው በአብዛኛው በሚሲዮናውያኖቹ በተነገረለት ትንቢትና መገለጥ እንጂ ስለትምህርቱ በቂ ውይይት በማድረግ ግንዛቤ አግኝቶ በመረዳት አልነበረም የስሕተት ትምህርቱ በይፋ አንደተወገዘ ሚሲዮናውያኑ ከወንጌላዊው ጋር በመሆን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ ተርጉመው አዘጋጅተውት የነበረውን በኢየሱስ ስም ጥምቀት የምትል ትንሽ መጽሐፍና በራሪ ወረቀቶች አሳትመው የማሠራጨት ሥራ መጀመራቸው ይታወሳል አንዳንድ ጥረት ቢደረግም ትምህርቱን በዛ ፍጥነትና በዛ ሁኔታ ምላሽ ሰጥቶ በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተደረገው ጥረት የሚመጥን ስላልነበረ አደጋው እየጨመረ ሲሄድ ችሷል ይህን የስሕተት ትምህርት ለምዕመኑ ለማስረዳትና ከአደጋው ለመከላከል በተለያዩ አጥቢያዎች ትምህርት ለመስጠትና የማስተማሪያ ጽሑፍ አዘጋጅቶ ለመበተን ጥረት ተደርጎአል በተጨማሪም በጊዜው የውሃ ጥምቀት በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ በታተመ አንድ መጽሑፍ ውስጥ የትምህርቱን ምንነት ለመግለጽና ትከከለኛውን መንገድ ለማሳየትና ለማስተማር ተሞከርአል የ በኢየሱስ ስም ብቻ የሚለውን የስሕተት ትምህርት በመቃወምና እውነተኛ የሆነውን በማስተማር ሂደት ሌላው በአንዳንድ ሁኔታዎች አጋጥሞ የነበረው ችግር በአስተማሪው የአልተጨበጠ መገለጥና የትንቢት ቃል ልባቸው ተወስዶ የነበረና ወንጌላዊውን እንደተቀባ ሐዋርያ አድርገው በጭፍን ይመለከቱት የነበሩ ከእሱ ጋር በነበራቸው ቅርበት እውነቱን በፈቃደኝነት መረዳት ባለመፈለጋቸው ሰአደጋ ሊዳረጉ ችለዋል በወንጌላዉያን አብያተ ከርስቲያናትም በኩል አውነቱን በሚገባ አጥንቶና ተዘጋጅቶ በወቅቱ ምዕመኑን ለማሳወቅና ከስሕተት ትምህርቱ እንዲጠበቁ ለማድረግ የሚያስችል በቂ የሆነ የእረኝነት ሥራ ሲሠራ ባለመቻሉ ብዙዎች በተለይም በሲዳማና በወላይታ በርካታ ከርስቲያኖች በትምህርቱ ነፋስ በቀላሉ ሲወሰዱ መቻላቸውን አይተናል ትምህርቱ በይፋ እንደታወቀ ወዲያውኑ በተቀናጀ መንገድ አቋም በመውሰድና በማስተማር የቃሉን እውነት ለማሠራጨት ቀጣይነት ባለው መንገድ በቂ ጥረት አድርገን ቢሆን ኖሮ ትምህርቱ ወይም እምነቱ ምናልባት ዛሬ ከደረሰበት ደረጃ አይደርስም ይሆን ነበር የሚል ግምት አለ የአርነት ትምህርትዐዩኩዩሺፐካርፍ ይህን ትምህርት በማስፋፋት የመጀመሪያው ረድፍ ላይ የነበሩት አገልጋዮች ብዙዎቹ የእግዚአብሔር ኀይል አንዲገለጽ የጌታችን የኢየሱስ ከርስቶስ የደሙ ኀይል እንዲታወቅና የሰዎች ፈውስ በተለይም ከአጋንንት መፈታትን በሚመለከት ከፍተኛ ቅናት የነበራቸው እንደነበሩ እናስታውሰለን አንዳንዶቹ ቀደም ብለው ለወንጌል አገልግሎት ዋጋ የከፈሉ እንደነበሩም ይታወቃል የአርነት ትምህርት በከርስቶስ መስቀል የተከፈለውን ዋጋ የሚጥልና የመዳንን ዋስትና የሚያሳጣ አደገኛ ትምህርት እንደነበረ እናስታውሳለን ክርስቲያን ምንም ዐይነት ድካም በሕይወቱ የሚገለጥ ከሆነ በሰይጣን የመያዙ ምልከት ነው የሚለውና ሰይጣን በጸጉር በልብስ በጥፍር በዐይን በሳቅና በጨዋታ ወዘተ ሳይቀር ክርስቲያኖችን ሊይዝ ይችላል የሚል ሲሆን በተጨማሪም በሽታ ሁሉ በአጋንንት ከመያዝ የሚመጣ ስለሆነ ሰዎች አርነት መውጣት አለባቸው የሚለው ትምህርት በወቅቱ ፈጥሮት የነበረው ፍርሃትና መከፋፈል ቀላል እንዳልነበረ ይታወሳል አጋንንት የሚወጡባቸው መንገዶች ተብለው ይሰጡ የነበሩት ትምህርቶችም ሴላው ብዙዎችን የከፋፈሉ የቃሉ መሠረት ያልነበራቸው የስሕተት ትምህርቶች ነበሩ ይህ የአርነት ስሕተት ትምህርት አሜሪካንና ካናዳ ይኖሩ ከነበሩ የትምህርቱ አራማጆች ከጻፉት መጻሕፍትት በቀጥታ የተቀዳ እንደነበር ለማወቅ ተቸሎአል ትምህርቱ ወደሀገራችን ቀደም ብሎ የገባ ቢሆንም ለሁለት ዓመት ያህል ልምምዱ ውስጥ ውስጡን ይፋ ባልሆነ መንገድና በግል በሚደረግ ግንኙነት በተወሰነ ደረጃ ሲስፋፋ ቆይቶአል የትምህርቱ መስፋፋት ሁኔታ በብዙዎች ሕይወት ጭንቀትን የፈጠረ ብቻ ሳይሆን ከእምነታቸው እንዲናጉ ያደረገና ለአንዳንዶችም ከእግዚአብሔር ቤት ለመራቃቸው አንዱ ምከንያት ነበረ ከዚህም በላይ በተለይ በአንዳንድ ቤተ እምነቶች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በመሪዎች ዙሪያ የመከፋፈል አደገኛ አዝማሚያ ፈጥሮ የነበረ መሆኑ ይታወሳል ይህን ትምህርት ከምንጩ ለማወቅና ለመረዳት በወቅቱ በካናዳና በአሜሪካ ይገኙ ከነበሩት የትምህርቱ አመንጪዎች ጋር በመጻጻፍ የሚያስተምሩባቸውን አብዛኛውን መጻሕፍትና ከመቶ በላይ የሆነ በካሴት የተዘጋጁ ትምህርቶችን ለማሰባሰብ ተቸሎ ነበር በነዚህም ላይ ከቃሉ ጋር በማመሳከር የተደረጉት ጥናቶች ምናልባትም ትምህርቱን ከተቀበሉትና ከሚያስተምሩት የበለጠ በጉዳዩ ላይ በቂ ግንዛቤ ለማግኘት ተቸሎ ነበር ማለት ይቻላል ከዚህ በተጨማሪም ይህ የአርነት ስሕተት ትምህርት በአሜሪካ በእንግሊዝና በስካንዲኒቪያን አገሮች በሚገኙ የጴንጤቆስጤ እምነት ተከታዮች መካከል ፈጥሮ የነበረውን አንዳንድ ውዥንብር ለማጥራት በየሃገሩ የተቋቋሙ የተለያዩ የሥነ መለኮት ሊቃውንት የተሰበሰቡባቸው አጥፒ ኮሚቴዎች የደረሱበትንና የወሰዱትን አቋምና ውሳኔ ለማግኘትም የተቻለ ስለነበረ ትምህርቱን ለማጋለጥ መረጃውና ማስረጃው የተጠናከረ ነበረ ለምሳሌ በአሜሪካ ትልቁ የጴንጤቆስጤ እምነት ተቋም የሆነው አሴምብሊስ ኦፍ ጎድና ሌሎችም ህሽ ህጐር ለሳር ለርክክን የመሳሰሱ በዚህ ጉዳይ ላይ ቀደም ብለው የወሰዱትን ጠንካራ አቋምና ያወጡትን መግለጫ አሜሪካ ከሚገኙና ነገሩ ካሳሰባቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖች ተልኮ ለመመልከት ተቸሎ ነበር በተጨማሪም በስካዲኒቭያን አገሮች የሚገኙ የጴንጤቆስጤ እምነት ተከታዮች ኅብረት በአርነት ትምህርት ላይ ያወጡትን የዐቋም መግለጫና ሙሉ ጥናት ኮፒ አዲስ አበባ በሚገኘው ስዊዲሽ ፊላዴልፊያ ሚሽን አማካይነት ለማግኘት በመቻሉ ስለትምህርቱ አደገኛነት ለማስተማር አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር የአርነትን የስሕተት ትምህርት በተደረጉት ጥናቶችና በተሰበሰቡት ማስረጃዎች በማጠናከር አምስት ኪሎ ይገኝ በነበረው በመካነ ኢየሱስ ዩዝ ሆስቴል በየሳምንቱ ቅዳሜ ሰአራት ሳምንት የቆየ ተከታታይ ትምህርት መስጠት ተችሎአል ከዚህም በላይ ትምህርቱን በበርካታ ኮፒዎች በማባዛት በወቅቱ ነገሩን በተረዱና በተለያዩ ከልሎች በሚገኙ ወንጌላውያን አማካይነት ለተለያዩ አብያተ ከርስቲያናት ለማሠራጨት ተችሎአል እነዚህ እርምጃዎች የስሕተት ትምህርትነቱን በማጋለጥና ምዕመኑን በማስተማር አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ የረዱ ቢሆንም በትምህርቱ አጥብቀው ያመኑና አእልከ ውስጥ የገቡ ጥቂት ግለሰቦች የራሳቸውን ቤተ ከርስቲያን አቋቁመው መቀጠላቸው አልቀረም በዴሊቨራንስ አርነት የስሕተት ትምህርት ዙሪያ በወቅቱ ባደረግናቸው ውይይቶች አንዱ መረዳት የቻልነው ዐቢይ ጉዳይ ዛሬም በአንዳንድ ስፍራዎች እንደሚታየው አንዳንድ የቤተ ከርስቲያን መሪዎች ይህን በሚመስል መሠረታዊ ጉዳይ ላይ አቋም ማጣት አድርባይነት ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰዎችን መፍራትና ወዳጅነትን ማስቀደም ይሉኝታና በእውነት ጉዳይ ላይ የሚታይ ዳተኝነት የአመራር ልልነትና በአምነት ጸንቶ የአለመቆም ሁኔታዎች በወቅቱ እውነትን የሚጋፋ ተግዳሮቶች ነበሩ ይሁን እንጂ በትምህርቱ ላይ በቂ ግንዛቤ በማግኘት የትምህርቱን ስሕተት መሆን የተገነዘቡት ብዙዎቹ ከልምምዱ ራሳቸውን ወዲያውኑ በማግለላቸው የተጠራጠሩት ካሉበት ቆመው እንዲያስቡ አድርጎአቸዋል በተጨማሪም በአርነት ትምህርት ላይ የቀረቡትን መረጃዎችና ትምህርቶች በወቅቱ ገፍቶ ለመሄድ ወይም ቆሞ በይፋ ለመከራከር የደፈሩ ብዙዎች አልነበሩም ቤተ ክርስቲያንን ከፍሎ የመውጣት እቅዳቸውም በብዙ ሥፍራ ሳይሠምር ቀርቶአል የአርባ ቀን ጾምና በእሳት መጠመቅና መንጻት ይህም ትምህርት አንደሌሎቹ ከውጭ የተቀዳ ነበር አራሳቸውን በዚህ ልምምድ ውስጥ በማሳለፍ አርባ ቀን በመጾም ቅድስናን ለመግዛት ከሞት ጋር መታከከ የጀመሩ የዋህ ወጣቶች ቁጥራቸው ጥቂት አልነበረም ይህ ሁሉ ጾም ወደ እግዚብሔር የበለጠ ለመቅረብና ለመቀደስ ለመንጻትና ኀጢአትንና ሰይጣንን እስከ መጨረሻው ድል ለማድረግ በአለማወቅና በየዋህነት ግፊት ይደረግ የነበረ ጥረት ነበር ከዚህ የስሕተት ትምህርት የተነሳ አርባ ቀን ለመጾም ሲሞከሩ እስከሞት የደረሱ ለአእምሮ ሕመምተኛነት የተዳረጉ የሌሎችም በሽታዎች ሰለባ የሆኑ ትምህርታቸውንና ሥራቸውን አቋርጠው በሚያሳዝን ሁኔታ ተንከራታች ሆነው የቀሩ በቅርብ የምናስታውሳቸው በርካታ የዚህ እምነት ተከታይ ወጣቶች ነበሩ ይህ ትምህርት በቅድስናና በጽድቅ ስም ይሰጥ ስለነበረ ጭፍን መንፈሳዊ ቅናት የነበራቸው በርካታ ወጣቶች በቀላሉ ተስበው በወጥመዱ ሊገቡ ችለው ነበር በቤተ ከርስቲያን ውስጥ እንደዚህ ዐይነት የስሕተት ትምህርቶችን በቅርብ ተከታትሎ አጥንቶ መንጋውን የመጠበቅ አቅም በወቅቱ ደካማ በመሆኑ ነገሮችን እያዩ እንዳላዩ ማለፍ የተለመደ አካሄድ ነበር እዚህ ትምህርት ውስጥ የገቡትም በአንዳንዶች ዘንድ በመንፈስ የሚቃጠሉ ጠንካራ ከርስቲያኖች ተደርገው ይቆጠሩም ስለነበረ መሪዎች በአግባቡና በወቅቱ በድፍረት የማስተማርና የመገሰጽ ጉልበት አልነበራቸውም ቢባል ስሕተት አይመስለኝም እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚያስችላቸውና ከፍ ካለ የእምነት ደረጃ የሚደርሱ መስሎአቸው በዚህ የስሕተት ትምህርት ውስጥ የነበሩና እግዚአብሔር በኋላ ታድጎአቸው ማምለጥ የቻሉ ዛሬ ሁኔታውን ወደኋላ ዞር ብለው ሲያስታውሱ በፍጹም የጭፍን አምነት መሠረት ባልነበረው ቅናትና ስሜታዊነት የመገዛት አደገኛ አካሄድ እንደነበረ ይመሰከራሉ ከዚህ የስሕተት እምነት የተነሣ ቅድስናን አብዝተን አንፈልጋለን በሚሉ በርካታ ወጣቶች ሕይወት ተከስቶ የነበረውን ፈተናና አደጋ ሲያስቡ ዛሬ ድረስ ከፍተኛ ጸጸትና ሐዘን ይሰማቸዋል እንግዲህ አነዚህና ሌሎችም በየጊዜው ብቅ ብቅ እያሉ የታዩ የስሕተት ትምህርቶች በአብዛኛው ምንጫቸውና መነሻቸው ከውጭ ቢሆንም በሀገራችን በፍጥነት እንዲሠራጩ ዕድል የሰጣቸው የምዕመኑ ብልህነት የሌለበት የዋህነት እውቀት የጎደለው ቅናትና እንዲሁም እረኛ አስተማሪና መሪ የማጣት ችግር እንደነበረ በግልጽ ይታወሳል እነዚህን የቀደሙ ችግሮችና በቅርብም ባለፉት ዐሥርና ዐሥራ አምስት ዓመታት እየጨመሩ የመጡትን የሐሰት ትንቢቶችና የብልጽግና ወንጌል ስብከቶች በሚመለከት አንዳንዶች የሚያሳስባቸውና በቤተ ከርስቲያን ውስጥ ሊመጣ የሚችለው አደጋ የታያቸው ዕድል ባገኙበት ሁሉ ለመግለጽና ለመናገር ጥረት ቢያደርጉም ጉዳዩ በሁሉም ቤተ እምነቶች በቂ ትኩረት ተሰጥቶትና እንደ ዋና አጀንዳ ተወስዶ በተቀናጀ መንገድ ምአመኑን ከስሕተት ትምህርቶች ለመጠበቅ በአግባቡ በቂ ጥረት ባለመደረጉ ውጤቱ ሙሉ በሙሉ አጥጋቢ ሆኖ አልተገኘም በተለያዩ ደረጃዎችና በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉት ጥረቶች በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው መንገድ የተስተናገዱና ቤተ እምነቶችም በአብዛኛው በሙሉ መሰጠት የተንቀሳቀሱባቸው ባለመሆኑ ዛሬም ችግሩ ከምንጊዜውም ይልቅ ሰፍቶ ይታያል ለምሳሌ ከ ዓመት በፊት ይህ የመገለጥና የትንቢት ጉዳይ ዛሬ ከደረሰበት ደረጃ ከመድረሱ አስቀድሞ ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት ኅብረት ደብረዘይት ባደረገው ስብሰባ በዚህ ዙሪያ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ዋና የመነጋገሪያ ርፅስ እንደነበሩ ይታወሳል በጊዜው በአባል ቤተ እምነቶች በተደረሰው ስምምነትና በወጣው የዐቋም መግለጫ መሠረት ሁሉም ቤተ አምነቶች ይህን ጉዳይ ተመልሰው ምዕመኑን በማሳወቅና በማስተማር እርምጃ እንዲወስዱ የተደረሰ ስምምነት የነበረ ቢሆንም በኋላ በተደረገ ከትትል ጉዳዩ ከዐቋም መግለጫ ያሰለፈ አንዳልነበረ ለመረዳት ተቸሉአል እንደገና ከስምንት ዓመት በፊት ይህ ጉዳይ እጅግ ያሳሰባቸው የፊኒሽ ሚሽን የኤስ አይ ኤም ታዋቂ ሚሲዮናውያን እንዲሁም በኢቲሲ የነበሩ መምህራን ተደምረውበት አንድ ነገር ማድረግ ይቻል ዘንድ በኤገስት ተከታታይ ውይይትና ምከከር ከተደረገ በኋላ ከእንግሊዝ አገር ዶር ፒት የተባሉ አገልጋይና ምሁር ተጋብዘው በኢቲሲ ከዐዐ በላይ ለሆኑ መሪዎች አምስት ቀናት የቆየ ትምህርት መሰጠቱም ይታወሳል በጊዜው የተግባር መርሃ ግብር ለማዘጋጀት የተሞከረና የዐቋም መግለጫም የወጣ ቢሆንም ይህም እንደታሰበው ርቆ የሄደ ነገር አልነበረም ማለት ይቻላል ከጥቂት ዓመታት በፊትም ከተለያዩ ቤተ እምነቶች በተውጣጡና ጉዳዩ በሚያሳስባቸው አገልጋዮች ተመስርቶ የነበረው የተሐድሶ ኮሚቴ አንዱ ጥናቱ በዚህ ጉዳይ ላይ አንደነበረ ይታወሳል ይህን ተከትሎ ዐዐ ከሚሆኑ አገልጋዮች ጋር በኢቲሲ የተደረገው ውይይትና በኋላም የተሐድሶ ጥሪ የተሰኘው መጽሐፍ ታትሞ መውጣቱ ይታወሳል ውይይቱና መጽሐፉ በሀገር ውስጥና በውጭም በሚኖሩ ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት መካከል የፈጠረው ግንዛቤ ቀላል አንዳልነበረ ብንረዳም ሥራው የበለጠ ተጠናከሮ እንዲቀጥል አሁንም ብዙ ነገር መደረግ አንደሚኖርበት ሁኔታው ያሳያል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት ኅብረትም አንዳንድ ጥረቶች የተደረጉና እርምጃዎችም የተወሰዱ መሆኑን እንገነዘባለን ይሁን እንጂ ይህን መሠረታዊ ችግር ከመቀነስና ምዕመኑን ከስሕተት ትምህርት አደጋ ከመጠበቅ አኳያ ዛሬም ሩቅ መንገድ እንደሚቀርና በአዲስ መንፈስና ስልት መንቀሳቀስ እንደሚገባ ሁኔታው ያመለከታል በአሁኑ ጊዜ አንዳንድ አገልጋዮች የስሕተት ትምህርት የፈጠረው ውዥንብርና እውነቱን ለመለየት አስቸጋሪ በሆነበት ወቅት ሁኔታውን የሪቫይቫል ወይም የተሀድሶ ዋዜማ ነው የሚለው ትምህርታቸው አደጋውን የሚያሰፋ መስሎ ይታያልለ ሩ የቃሉን መሠረት በለቀቀና ትርጉሙ በተደበላለቀ ስሜትን ለመቀስቀስ ብቻ በሚዘጋጅ ለአዕምሮ መታደስ የማይጠቅም ስብከትና የስሕተት ትምህርት በበዛበት መንፈሳዊ መነቃቃትና ተሐድሶ ሊመጣ የሚችለው አንዴት ነው። ዛሬ ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት የተለያዩ ልምምዶች መገለጦችና የትንቢት ቃል አለን የሚሉትን በርካታ ወገኖች የበለጠ በመቅረብና በመምከር በሚቻል ሁሉ የፍርድ ቃልን ከያዙ ንግግሮች በመቆጠብ እውነቱን በፍቅር በመናገር ለመወያየትና ለመመካከር በልበ ሰፊነት ጥረት ማድረግ አስፈላጊ መስሎ ይታያል ለፍቅርና ለአንድነት ቀድሞ መገኘት ጠቃሚ ይሆናል በሁሉም ሥፍራ የሚታዩት አገልግሎቶች ሁሉ ተመሳሳይና ስሕተት የሞላቸው ናቸው የሚል ፍረጃም የሚያሳስትና የሚያራርቅ ሊሆን እንደሚቸል መገንዘብ ጠቃሚ ይሆናል ከሁሉ በላይና ከሁሉ በፊት አብያተ ከርስቲያናት ምዕመናኖቻቸውን በአግባቡ በመያዝና በቃሉ እውነት በማሳደግ ከማንኛውም የስሕተት ትምህርት አደጋ እንዲጠበቁ የማድረግ ኀላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት ይጠበቅባቸዋል መንጋውን በመጠበቅና እውነቱን በማስተማር የራሳችንን ድርሻ በአግባቡ ሳንወጣ ሌሎችን ብቻ የምናወግዝ ከሆነ እኛንም ከተጠያቂነት አያድነንም ለችግሮቻችቸንም መልስ አይሆንም የኛ ናቸው የምንላቸው ምፅመናን በተለይም ወጣቶች ከጉያቸን አየወጡ ወደሴሎች አንዲሄዱ የተዳረጉበትን ዋና ምከንያት ምን እንደሆነ ራሳቸንን አስቀድሞ መጠየቅ የሚገባ ይመስለኛል ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት ከስሕተት ትምህርት መስፋፋት አኳያ እራሳችንን ጠይቀን መመለስ የሚገባን በርካታ ጥያቄዎች መኖራቸውንም ማሰብ ጠቃሚ ይሆናል ይህን አሉታዊ ገጽታ መለወጥ የሚቻልበት ዋናው መንገድ ሕዝቡን በቃሱ ማስተማርና ማሳደግ በተለይም የወጣቱን ፍላጎትና ችግር መረዳት መቻል ነው በአሁኑ ጊዜ በበርካታ አብያተ ከርስቲያናት እንደሚታየው ወጣቱን የሚያማከልና የሚያሳትፍ አንዲሁም እቅድ አውጥቶ ትኩረት ሰጥቶ የሚካሄድ አገልግሎት በጣም የተወሰነ መስሎ ይታያል ዛሬ ከሚታየው ሁኔታ ከወጣቱ በወጣቱ ለወጣቱ የሆነ አገልግሎት የግድ አስፈላጊ ነው ይህን ሁኔታ በመረዳትና በትጋት ተነሥተን ልንንቀሳቀስበት ካልቻልን የወጣቱን መፍለስ ላልሆነ የትምህርት አደጋ መዳረግ ስሜቱንና ፍላጎቱን ተከትሎ መሄድን በውጭው አሉታዊ ተጽአኖ ሥር መውደቁና ሲብስም ከእግዚአብሔር መንገድ አየራቀ መምጣትን መግታት አይቻለንም በአሁኑ ጊዜ አንዳንዶቻችን በብዙሃን መገናኛ መጠቀም መቻላችን ለዚህ እጅግ ጠቃሚና ከፍተኛ የአገልግሎት ዕድል ነው ከነዚህ ሚዲያዎች የተነሣ የአግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋትና የእግዚአብሔርንም ከብር ከፍ አድርጎ ለማሳየት የሚያስችል አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮአል ማንኛውም ዕድል ደግሞ ኀላፊነትን አደራን ወይም ተጠያቂነትን አስከትሎ ነው የሚመጣው ሚዲያውን የስሕተት ትምህርት ለመከላከል ብቻ ሳይሆን መንጋውን በቃሉ እውነት ጸንቶ እንዲቆም ለማድረግ መጠቀም ካልቻልን አንድ ከሚያደርገን ይልቅ የሚከፋፍለን እያደገና እየሰፋ ይመጣል ይህን ከእግዚብሔር የተቀበልነውን ሰፊ ፅድል ለአግዚብሔር ከብር ለሰዎች መዳንና የሕይወት አድገት መጠቀም እንጂ ለራስ ከብርና ለገቢ ማስገኛ ታስቦ የሚከናወን መሆን የለበትም ይህንን ዕድል እንደ እግዚአብሔር ቃል መሠረት ከርስቶስንና መስቀሉን በሚያሳይ መንገድ የእረኝነት አገልግሎታችንን በአግባቡ ለማከናወን ካልተጠቀምንበት ይዋል ይደር እንጂ እኛንም አገልግሎታችንንም ለአደጋ ሊዳርገው ይችላል መገናኛ ብዙሃንን እግዚአብሔርን በመፍራት በጥንቃቄና በተጠያቂነት መንፈስ የምንጠቀምባቸው ከሆነ ግን እኛም እንባረካለን የአገለግሎታችንም ፍሬ በምናገለግላቸው ሰዎች ሕይወት ላይ በሚታየው እውነተኛ ለውጥና እድገት ተገልጦ የሚታይ ይሆናል የአገልግሎታችን ፍሬ የሚለካው በምዕመናን ብዛትና በምንሠራቸው ሕንጻዎች ዐይነት ሳይሆን በእግዚብሔር ፊት ይዘናቸው በምንቆመው ሰዎች ዐይነት ነው ዋናው ጉዳይ በከርስቶስ መስቀል የሚታመኑ በእውነት ቃል መሠረት ላይ ጸንተው የሚቆሙ ደቀመዛሙርት መሆናቸው ነው ምድራዊ ኑሮአቸው ተሳካም አልተሳካም ምንጊዜም በየትኛውም ቦታ ኢየሱስ ጌታ ነው ብለው የሚመሰከሩና ጸንተው የሚቆሙ ሆነው ሲገኙ ብቻ ነው ዛሬ ከምንጊዜውም ይልቅ እውነተኛ አስተማሪዎችና ለቃሉ ታማኝ የሆኑ መሪዎች የሚፈለጉበት ወሳኝ ጊዜ ነው አንዳንድ መሪዎች የነገሩን እውነት ብንረዳም ከሰዎች ፍርሃትና ይሉኝታ የተነሣ ሲያልፍም የእንጀራና የቦታ ጉዳይ እየሆነብን በግልጽና በድፍረት ለመናገርና ለማስተማር ባለመቻላችን ዐይናችን እያየ ብዙዎች የአገልግሎት ልብ የነበራቸው ወጣቶች ፈላጊ በማጣት ከአጠገባችን ርቀው ለጥፋት ተዳርገዋል ሌላው ከዚሁ ጋራ አብሮ መነሣት ያለበት ሀገራችን ኢትዮጵያ አሁን ከምትገኝበት ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ወንጌላውያን አብያተ ከርስቲያናት በአጠቃላይ እንዲሁም እያንዳንዱ አማኝ በተናጠል በርካታ አሳሳቢና ውስብስብ በሆኑ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ተከበው ወይም ተጠላልፈው የሚገኙበት ሁኔታ ይታያል የስተት ትምህርቶችና የምግባር ዝንፈቶች ከእምነታችን አኳያ ያጋጠሙ ወቅታዊና መሠረታዊ ተግዳሮቶች ይሁኑ እንጂ በአሁኑ ጊዜ አብያተ ከርስቲያናትንና ሀገሪቱን አየናጡ የሚገኙ ከዚህ የከፉና ሕልውናችንን የሚፈታተኑ የመንፈስ አንድነትን የሚያጠፉ ሌሎች አደገኛ አዝማሚያዎችና ሁኔታዎችም እየተከሠቱ መሆናቸውንም ትኩረት ሰጥቶ ማጤን አስቸኳይ ከሆነበት ደረጃ ላይም መድረሳችንን ማስተዋል የሚገባ ይሆናል ከነዚህም መካከል አንዱ ሀገርን ብቻ ሳይሆን በቤተ ከርስቲያንም ውስጥ አደገኛ ሁኔታ አየፈጠረ የመጣው የዘር ፖለቲካ ነው ዛሬ ጽንፍ የያዘ ብሔርተኝነት ወይም ዘረኝነት በከልሎች ዙሪያ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን አብያተ ከርስቲያናትንም እያወከ በከርስቶስ አለን የምንለውን አንድነት እየናደ ብዙዎች የቀደመውን ዘመን እንዲናፍቁ ግፊት እያደረገ ነው ዛሬ ከከርስቲያንነታቸው በላይ የማንነታቸው ጥያቄ የሚያሳስባቸው አንዳንድ ከርስቲያኖች በተዛባ አመለካከትና ከእምነት ሃዲድ በወጣ ስሜታዊነትና ቅናት የከርስቶስ ቤተ ከርስቲያን ከውጭው ዓለም ተለይታ እንዳትታይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሲያደርጉ ይታያል ይህ ቤተ ከርስቲያን ያጋጠማት ሌላው አሳሳቢና የጊዜው ፈተና ነው ይህ በአንዳንድ ሥፍራ የምዕመኑን ጤናማ ሕይወት ሲበላ የሚታይ የማንነት ጥያቄ ወይም የዘረኝነት ነቀዝ አብያተ ከርስቲያናት በአግባቡ ግንዛቤ በመውሰድ በወቅቱና በቦታው የሚጠበቀውን ያህል ቆመው በድፍረት ሊናገሩበት ባለመቻላቸው ጨለማ ብርሃኑን ሲገፋው ከሚታይበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ይህ ሁኔታ በመካከላችን ከሚታየው የአመራር ብስለት ማጣትና በአንዳንድ ሁኔታዎች ከሜታየው የዘር መሳሳብ አኳያ በውጭው ዐይን አልፎ አልፎ ቤተ ከርስቲያንና ምዕመኑ ተአማኒነት እንዲያጡ አድርጓቸዋል ዛሬ ሀገራችንን ከገጠሟትና ሰላምዋን በማናጋት ላይ ከሚገኙ አጓጉል ሁኔታዎች አኳያ የቤተ ከርስቲያንን አዎንታዊ ጣልቃ ገብነትን የግድ የሚጠይቁ ተግባራት በርካታ እየሆኑ መጥተዋል ዛሬ የስሕተት ትምህርትን የምግባር ዝንፈትን ከመከላከልና አምነትን ከመጠበቅ ጋራ ዘረኝነትን አጥብቆ መዋጋት የወቅቱ ጥያቄና ተግዳሮት ሆኖ ይታያል ይህ ከፊተኛው የበለጠ ቤተ ከርስቲያንን የሚከፍል የሀገርን ሰላምና ደህንነት የሚያናጋ የሰይጣን የዘመኑ ዐይነተኛ መሣሪያ ነው በቤተ ከርስቲያን ውስጥ የአግዚአብሔር ቃል መሠረት ያደረገ እግዚአብሔርን በመፍራት ላይ የተመሠረተ አመራር ሲጠፋ ግልፅነትና መልካም አስተዳደርም ይጠፋል የቤተ ከርስቲያን ተልዕኮም ዐላማውን እየሳተ ይመጣል በታወቀ እውነት ላይ ይሉኝታ ዝምታና እውነትን ከመናገር መቆጠብ የአመራር ዘይቤ እየሆነ ሲመጣ የቤተከርስቲያን እድገት መቀጨጭ ብቻ ሳይሆን የመከፋፈል አደጋ ይመጣል አንድነትና ኅብረትም ይዳከማል በዓለም ያለ የፖለቲካና የፓርቲ መንፈስ በቀላሉ በቤተከርስቲያን ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል በአሁኑ ጊዜ በርካታ ምዕመናን ከሚታይባቸው ዕውቀት ከተለየው ቅናት ተላቀውና ከባዶ ስሜታዊነት ርቀው በቃሉ መሠረትነት በአዕምሮ መታደስ ተለውጠው በመንፈስ ምሪት እንዲመላለሱ አብያተ ከርስቲያናት በአዲስ አሠራርና ስልት መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል እውነተኛ ጨውና ብርሃን መሆን እንዲቻል መሪዎች የሆንን ለቃሉ ታማኝነት ማሳየት ለእውነት መቆም መልካም አስተዳደርንና የአመራር ልቀትን ማሳየት በግልጽነት በትህትናና በእውነት ምዕመናኖቻቸንን መምራት ከጠባብ አመለካከትና ከተሳሳተ ወገንተኝነት መላቀቅ ምንጊዜም ለፍቅርና ለእርቅ ቅድሚያ መስጠት የመንፈስን አንድነት መጠበቅ እድሎችን በመጠቀም ጊዜውን መዋጀትና በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ተጠያቂነት ያለብን መሆኑንም አምነን መቀበል ይጠበቅብናል ከዚህም ጋር ምዕመናንን የሀገራቸው እድገትና ልማት አካልና በረከት እንዲሆኑ ማስተማርና ማደፋፈር አጅግ ጠቃሚ ሆኖ ይታያል ይህ ሲሆን ብርሃናችን በውስጥም በውጭም ደምቆ ሲበራ ይታያል ለመንጋው እውነተኛ ምሳሌ መሆናችንም ይረጋገጣል የኢትዮጵያ መባረከና እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር መዘርጋትም እውን እየሆነ የሚመጣው የዚህ መሠረት ጥብቅና እውነት ሲሆን ብቻ ነው አመሰግናለሁ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርከ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact