Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

ፍኖተ እግዚአብሔር.pdf


  • word cloud

ፍኖተ እግዚአብሔር.pdf
  • Extraction Summary

ረያ ሥጋ ወቃሳ ፖያናሪዎሪሪ ረያ ዝ ሐፉ መሳሪሳፖ ወረርፇ ዝቋማርሮ ሪ ማፅረፖሥፓቱዚህ በኋላ ያለው ሙሉው መጽሐፍ ከግርጌ ማስታዎሻውና ከመፍትሔ ቃሉ በቀር በኣለቃ ኃሩይ የተጣፈ ነው። የመጥሐፉም ሙሱ ዓለማ በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት እግዚአብሔር በባሕርይው አንድ ነው ተረከቦ መገኘት ተወላዲ የወልድ የግብር ስም መንፈስ ቅዱስን የሰረጸ ወይም ያስገኘ አካላት ከሦስቱ አካለት የአንዱ መጠሪያ ስም በዚህ ስም ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ አይጠሩም ዕውቀት ማስተዋል ምስጋና መክፈያ የመጽሐፍ ከፍለ ሐሳብ ተጠናቆ ሌላ ሲጀመር እንደ ንዑስ ምዕራፍ ወይም ከፍል የሚያገለግል።

  • Cosine Similarity

መልስ ምንም ቢሆን ወላዲው ተወላዲ ሠራጺ ተወላዲውም ወላዲ ሠራጺ ሠራጺውም ወላዲ ተወላዲ ሊሆን የማይችል ነው አካላትን ቅሉ ልዩ ልዩ የሚያሰኛቸው ይህ ወላዲ ተወለዲ ሠራጺ የሚለው ንባብ ነው መለኮትን አካላት በሚለያዩበት ስም ጠርቶ ወላዲ መለኮት ተወላዲ መለኮት ሠራጺ መለኮት ማለት መለኮትን እንደ አካላት ሦስት ማለት እንደሆነ አስተዋይ ልቦና ይረዳዋል አንዲህም ከሆነ ሊቃውንት በየአንቀጹ ይሜጫለሱ በአካላት ወይትወሐዱ በመለኮት ያሉት ንባብ ሐሰት ሆነ ማለት ነዋ መለኮት በራሱ ወላዲ ተወላዲ ሠራጺ ከተባለ ሦስት በመሆኑ የመንገዱ ጥርጊያ ወደ ዮሐንስ ተዐቃቢ ቤት የሚያገባ መሆኑ አይጠረጠርም መለኮትን ወላዲ ተወለዲ ሠራጺ ማለትም ሦስቱ አካላት መለኮት መለኮት መለኮት የተባሉበትን ምሥጢር ባለማስተዋል የታሰበ ስሕተት ነው ሊቃውንት ሦስቱን አካላት መለኮት መለኮት መለኮት ብለው ማመናቸው መለኮት በአካል ልዩ ነው ብለው አይደለም አንድ መለኮት በሦስት አካላት ልዩ ነው ብለው አይደለም አንድ መለኮት በሦስት አካላት ህልው ነው ብለው ነው እንጄ ማስረጃ ጂኛ ሊቅ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት ንባብ ወኢይትሀበሉ ሕጉላን ያብኡ ውስተ ቅድስት ሥላሴ ፍልጠተ መለኮት ወኢድማሬ አካላት ወኢንሰግድ ለኮቱ አማልከት አላ ለ አምላክ ወንሰምዮሙ በሾ አስማት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ መለኮት ወ ኃይል እንዘ ሾ አካላት እጉዛን በጽምረተ መለኮት ወህላዌ ትርጓሜ ከዕውቀት የተሳሳቱ ሰዎች ልዩ በሆነች ሦስትነት የመለኮትን ልዩነት የአካላትን አንድነት አግብተው ይናገሩ ዘንድ አይድፈሩ ለአንድ አምላከ እንሰግዳለን እንጂ ለሦስት አማልከት አንሰግድምና አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስብለን በሦስት ስሞች አንጠራቸዋለን እኒህም ሦስቱ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ባንድ መለኮትናሕይወት በአንድ ሕልውና አንድነት የተገናዘቡ ሦስት ሲሆኑ አንድ ባሕርይ አንድ ኃይል ናቸው ብሏልና ድርሳን ሃይማኖተ አበው ባስልዮስ ዘአንጾኪያም ጓኛ ንባብ እንሰ ሶበ አቤ እግዚአብሔር ዕብል በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እስመ አሐዱ ውእቱ መለኮተ ሥላሴ ወሠለስቲሆሙ አሐዱ እሙንቱ በመለኮት ወእሙነ እብል ከመ አሙንቱ መለኮት ወህላዌ ወለለ አሐዱ እምአካላተ ሠላሴ ያበጽሕ ከኃተሙሃይማተ አበው ጎርጎርዮስ ነባቤ ሟነኮት ዎነ ይሟእከቱ ፍጹመ መለኮት ምስለ ዚአሁ አካል ወስም ከፍል ሃይማኖተ አበው ትርጓሜ እኔ እግዚአብሔር ባልሁ ጊዜ እግዚአብሔር ማለትን ስለ አብ ስለ ወልድ ስለ መንፈስ ቅዱስ እናገራለሁ የሦስቱ መለኮት አንድ ነውና ሦስቱም በመለኮት አንድ ናቸው እኒህም መለኮትናሕይወት ሕልውናባሕርይ እንዲባሉ በእውነት እናገራለሁ ልዩ ሦስትነት ካላቸው አካላትም አንዱም አንዱም ከገንዘቡ አካልና ከገንዘቡ ስም ጋራ ፍጹም መለኮትን ገንዘብ ያደርጋሉ ብሏል ኛው ሊቅ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያም ንባብ እሉ ሠለስቱ አካላት ፍጹማን ዲበ መንበረ ስብሐት ወእጎዛን በፅምረተ አሐዱ መለኮት ዘውእቱ አሐዱ ብርሃን ዘይሠርቅ እምኔሁ ሥላሴ ትርጓሜ እኒህ ሦስቱ አካላት በጌትነት ዙፋን ላይ ያሉ ፍጹማን ናቸው በአንዱ መለኮት አንድ አድራጊነትም የተገናዘቡ ናቸው ይህም መለኮትባሕርይ የአካል ሦስትነት ከሱ የሚገኝለት አንድ ብርሃን ነው ብሏል ክፍል ሃይማኖተ አበው አቡሊዲስ ዘሮምምሾ ሊቅ ንባብ ወልድኒ ቃሎሙ ለአብ ወለመንፈስ ቅዱስ ወመንፈስ ቅዱስኒ መንፈሶሙ ለአብ ወወልድ ወበዝንቱ አእምርነ ከመ መለኮተ ሥላሴ ወሉቱ ንሰግድ ወአበዊነሂ እለተጋብኡ በኒቅያ ዝኒ ከማሁ ሃይማተ አበው ነ ሂ መ ከኃቷተሙ ሃይማየተ አበው ምነ ቿ ይሟእከከቱ ይቤሉ እመቦ ዘይፈልጥ መለኮቶ ለእግዚአብሔር አብ እምወልድ ወእም መንፈስ ቅዱስ ውጉዘ ለይኩን ትርጓሜ ወልድ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው መንፈስ ቅዱስ ለአብና ለወልድ እስትንፋሳቸው ነው በዚህም የምንሰግድለት የሦስቱ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ መለኮት አንድ አንደሆነ አወቅን በኒቅያ የተሰበሰቡ አባቶቻችንም የአብን መለኮት ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ የሚለይ ሰው ቢኖር የተለየ ይሁን ብለዋል ብሏል ክፍል ሃይማኖተ አበው ይህን የመሰለ በየአንቀጹ የተነገረ ብዙ ነው ሃታ ሦስቱ መለኮት መለኮት መለኮት መባላቸው አንድ መለኮት በሦስቱ አካላት ሕልው ሆኖ ሦስቱን አካላት ስለአገናዘበ ነው እንጂ መለኮት በአካል የተለየ ሆኖ እንዳይደለ አስተዋይ ልቦና ያለው ሰው መጻሕፍትን በጥንቃቄ ቢመረምር ይረዳዋል መለኮት በአካል የተለየ ቢሆን ሦስቱ ሁሉ ባልተጠሩበትም ነበር አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ መባል ግን በአካል የተለየ ቢሆን በየራሳቸው ተጠሩበት እንጂ ሦስቱ ሁሉ እንዳልተጠሩበት ጆዝኒ ከማ ሃይማተ አበው ዎነ ፀቿ ያምድ ሮ መተዖታፖፖ ፅዕንሦዳ ዩ ስነምፖዕያፖሪታሰ ጳሦኗይር ይናራ ጥያቄ መለኮትን በአካል ሦስት ብሎ መሰኮት የተባለ አካል ነው ማለት ይገባልን። ቅዳሴ ማርያም በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ማለቱ ነው ፀሐይም አንድ ባሕርይ ሲሆን ሦስት ከዊን አለው ይኽውም ከበብ ብርሃን ዋዕይ ነው በከበቡ አብ በብርሃኑ ወልድ በዋዕዩ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ ብርሃነ ፀሐይ ከከበቡና ከዋዕዩ ተፈልጦ ተከፍሎ ሳይኖርበት በራሱ ከዊን ከዓይን ብርሃን ጋራ ይዋሐዳል እንዲሁም ወልድ በቃልነቱ ከዊን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በተለየ አካሉ ሰው ሆነ ብርሃነ ፀሐይ ከዓይን ጋራ በተዋሐደ ጊዜ ክበብና ዋፅዩ እንዳይዋሐዱ ወልድ ሰው በሆነ ጊዜም መለኮት አንድ ስለሆነ አብ መንፈስ ቅዱስ ሰው ሆኑ አያሰኝም ማስረጃ ባለቤቱ ጌታችን ከርስቶስ በቀሌምንጦስ ንባብ አቡየ ፀሐይ ወአነ ብርሃኑ ወመንፈስ ቅዱስ ዋዕየ ትርጉም አባቴ ፀሐይ ነው እኔም ብርሃኑ ነኝ መንፈስ ቅዱስም ዋዕየ ነው እንዳለ ሠለስቱ ምዕትም ንባብ አቡየ ወአነ ወመንፈስ ቅዱስ ፀሐይከበብ ወብርሃን ወዋዕዩሙቀት ብለዋል ቅዳሴ አባ ሕርያቆስም ንባብ አብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ ወመንፈስ ቅዱስ ፀሐይ አሐዱ ውእቱ ፀሐየ ጽድቅ ዘላዕለ ኩሉ ብሏል ቅዳሴ ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ ፀሐየ ጽድቅ ማለት ነውባሕርም አንድ ባሕር ሲሆን ሦስት ከዊን አለው ይኸውም ስፋት ርጥበት ሁከት ነው በስፋቱ አብ በርጥበቱ ወልድ በሁከቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ ሰው ከባሕር ገብቶ ዋኝቶ ሲወጣ በአካሉ ላይ ርጥበት ይገኛል እንጂ ስፋትና ሁከት እንዳይገኙ ወልድም በቃልነቱ ከዊን ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በተለየ አካሉ ሰው በሆነ ጊዜ በመለኮት አንድ ስለሆነ አብና መንፈስ ቅዱስ ሰው ሆኑ አያሰኝም የዚህንም ምሳሌነቱ በአረጋዊ መንፈሳዊ እንደተነገረ በአሥራ አንደኛው አንቀጽ አናመጣዋለን ይህን ሁሉ ተመልከተን መለኮት በአካል ሦስት ከማለት ርቀን በአንድ መለኮት ሦስት አካላትና ሦስት ኩነታት እንዳሉ አምነን ወልድ በተለየ አካሉ ከአንድ መለኮት ተፈልጦ ስሌለበት በቃልነቱ ከዊን ሰው ሆነ ብለን ብናምን ሦስቱ ሰው ሆኑ እንዳያሰኝ የሚያስረዳ ነገር ኛ ሊቅ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አግናጥዮስ እንደሚከተለው ተናግሯዋል ንባብ ኀደረ አሐዱ አካል እም ሠለስቱ አካላት ውስተ ከርሣ ለድንግል ማርያም ወበእንተ ተዋሕዶተ መለኮት ዘንትናገር በዝየ ዘህልው በወልድ ወአኮ በእንተ አብ ወመንፈስ ቅዱስ ወኢንቤ ግሙራ ከመ እሙንቱ ኀደሩ ለተሰብኦ ውስተ ከርሣ ለድንግል ዘእንበለ ዳእሙ ወልድ ባሕቲቱ አሐዱ አካል እም ሠለስቱ አካላት ትርጉም ሦስቱ አካለት አንዱ አካል በማኅጸነ ማርያም አደረ በዚህ አንቀጽ ኅደረ ብለን የምንናገረው የመለኮት ተዋሕዶ በወልድ በቃልነቱ ስላለው ከዊን አይደለም ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ብቻ ሰው ለመሆኑ በማኅጸነ ድንግል አደረ እንላለን እንጂ አብ መንፈስ ቅዱስ ሰው በመሆን አደሩ አንልምና ብሏል አንደኛ መልዕከት ሃይማኖተ አበው መለኮት ዘሕልው በወልድ ያለው የወልድ የቃልነቱ ከዊን እንድሆነ እዝነ ልቦና ያለው ሰው በቅጥነተ ልብ ሆኖ ያስተውል ያፍያ ይመዝሥድያንሦባካዳይጠሳ ይሳተምፖነፖም መሇፅፍሳ ሮጄበቷሪያ ሮሯ የአንጾኪያው ሊቀ ዳዳሳት አትናቴዎስ ጓኛ እንዲህ ሲል ተናገረ ንባብ ወሶበሂ ንቤ አሐዱ አግዚአብሔር ወዱ ሕላዌ ወ ዱ መሰለኮት አኮ ዘያበጥል ላዕሴነ ዝንቱ ተስምዮተ ሾ አካላት እስመ ሃይማት አበው ዎነራፍ ኮ ለለ እም አካላት ሃላውያን በበአካላቲሆሙ ወመለኮትሂ ሕልው በሕላዌሁ ወኢይትፈለጥ ለከዊነ ኮሾ መለኮት አስመ ቅድስት ሥላሴ እሙንቱ በተዋሕዶ እንበለ ፍልጠት ትርጓሜ አንድ እግዚአብሔር አንድ ሕላዌ አንድ መለኮት ብንል አንድ ማለታችን ሾ አካላት ማለትን የሚፈርስብን አይደለም ሦስት አካላት ማለታችንም መለኮትን ከሦስት የሚከፍልብን አይደለም ከሦስቱም አካላት አንዱም አንዱ በየአካላቸው ፀንተው የሚኖሩ ናቸውና መለኮትም በአንድነቱ ፀንቶ የሚኖር ነው እንጂ ሦስት መለኮት ለመሆን የሚከፈል አይደለም ቅድስት ሥላሴ ያለመለያየት በተዋሕዶ አንድ ናቸውና ብሏል ሃይ አበው አመልዕከተ ሲኖዲቆስ ዛኛ ከፍል ። መልስ አይገባም ሥላሴ በመለኮት አንድ መባላቸውስ መለኮት እንደ አካላት ተከፍሎ ሳይኖርበት በአንድነቱ ፀንቶ አካላትን በተከፍሎ ሳሉ በሕልውና እያገናዘበ አንድ ልብ አንድ ቃል አንድ አስትንፋስ ስላደረጋቸው ነው እንጂ በከብር ስላስተካከላቸው አይደለም መለኮት ከአካል ጋር ከሦስት የሚከፈልስ ከሆነ አንድ ልብ አንድ ቃል አንድ እስትንፋስ መሆን የለም ይህም ከሌለ በአብ ለባውያን በወልድ ነባብያን በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን መባል አይገኝም እንዲህም ከሆነ በአንደኛው አንቀጽ የተጠቀሰው አቡሊዴድስ ንባብ ወልድኒ ቃሉሙ ለአብ ወለመንፈስ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስኒ መንፈሶሙ ለአብ ወለወልድ ያለው ሐሰት ሆኖ በየራሳቸው ልብ ቃል እስትንፋስ አላቸው በማለት እንደ ዮሐንስ ተዐቃቢ ዘጠኝ ወልደም ለአብና ለመፈስ ቅዳስ ቃላቸወ መፈስ ቅዳስ ለአብና ለወልድ እስትንፋሳቸው ሕይወታቸወ ነወ ሃ አበው ርር መለኮት ያሰኛል ዮሐንስ ተዐቃቢ ከዚህ ሴላ አልተናገረምና ሕልውናም እንዲያገናዝባቸው ማስረጃ ባለቤቱ ጌታችን ንባብ ለግብርየ እመኑ ከመታእምሩ ወትጠይቁ ከመ አነ በአብ ወአብ ብየ ትርጉም በሥራዬ አመኑ ታውቁ ትረዱም ዘንድ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ ብሏልና ዮሐ ቋቿ ንባብ ዳግመኛ ኢተአምንሁ ከመ አነ በአብ ወአብ ብየ ወዝኒ ቃል ዘአነ ነገርኩከሙ አኮ ዘ እምኀቤየ ዘነበብኩ አላ አብ ዘሀሎ ብየ ውእቱ ይገብሮ ለዝንቱ ግብር ትርጉም አታምንምን እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ ይህ ለእናንተ የምነግራችሁ ነገር ከኔ ከራሴ የተናገርኩት አይደለም በእኔ ያለ እርሱ አብ ይህን ሥራ ይሠራዋል እንጂ ብሎ ለፊልልስ ነግሮታል ዮሐ ጀ ዮሐንስ ዘአንጾኪያም ኛ ንባብ አንኮ ዘንተአመን በ እደው በሾ አማልክት ወኢ በኛ መለኮት አላ ንትአመን በ አካላት ወበሾ ገጻት እንተ ባሕርየ መለኮት ኻ ሃይማተ አበው ዎነ ሾቿ ትርጉም መገናዘብ አንደሌላቸው እንደ ሾ ሰዎች አድርገን በሦስት ሰዎች በሦስት አማልከት በሦስት መለኮት የምናምን አይደለገም ባሕርየ መለኮት አንድ በሚያደርጋቸው በሦስት አካላት በሦስት ገጻት እናምናለን እንጂ ብሏል ያይማኖተ አበው ከፍል የእስከንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ዮሐንስ ንባብ ንሕነ ንትአመን ከመ አብ ሕልው በወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወልድኒ ሕልው በአብ ወመንፈስ ቅዱስ ወመንፈስ ቅዱሰኒ ሕልው በአብ ወወልድ ትርጉም አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ሕልው እንደሆነ ወልድ በአብና በመንፈስ ቅዱስ ሕልው እንደሆነ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ሕልው እንደሆነ እኛ አናምናለን ብሏል ሃይማኖተ አበው ከፍል ኗ ዲዮናስዮስም መለኮትን እንደ አካላት ብንለይ ሰይጣናዊ እምነትን እናምናለን ማለቱ መለኮትን ሦስት ብሎ ሦስትነት ያለው አኃዝ በመለኮት ከተነገረ መንገዱ የዮሐንስ ተዐቃቢ ነውና እምነቱ ሰይጣናዊ መሆኑን ሲያስረዳ ነው መጻሕፍት ሁሉ ይትወሐዱ በመለኮት እያሉ ለአካላት ማስረጃ ያደርጉታል እንጂ መለኮትን ሦስት ብለው የሚከፍሉበት አንቀጽ አይገኝም ስለዚህ በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፉ መጻሕፍት ከተናገሩት ትምህርት ሳይወጡ ማመን ይገባል በእግዚአብሔር መንፈስ የተጸፉ መጻሐፍትን በድፍረትና በትዕቢት ሳይሆን በፈሪሃ እግዚአብሔርና በትሕትና ሆኖ የሚመለከታቸውን በአካል ሦስት በመለኮት አንድ የሚያሰኘውን የሃይማኖት ምስጢር በመግለጽ ይጠቅማሉና መሃይ አበው መሃይ አበውም ሻ ፎ ማስረጃ ቅዱስ ጳውሎስ ንባብ ወኩሉ መጽሐፍ ዘበመንፈሰ እግዚአብሔር ተጽሕፈ ይበቁዕ በኩሱ ትምህርት ወተግሣጽ ወአርትኦ ወአጥብቦ ወጽድቅ ከመ ይትገሠጽ ብእሴ እግዚአብሔር ውስተ ኩሉ ምግባረ ሠናይ ትርጉም በአግዚአብሔር መንፈስ የተጻፈ መጽሐፍ ሁሉ ፍፁም ትምህርትንና ምክርን በመሆን ልቦናን በማቅናትና በማራቀቅ ጽድቅንም በማሠራት ይረባል ይጠቅማል የእግዚአብሔር ሰው በጎ ሥራን ሁሉ ይማር ዘንድ እንዳለ ኛ ጢሞ ያምድ ሥዛፊያርይና ዕዳዳሰሳ ያዋሪርረም ቦሟጠሩያዕምፈፀፇ ይላበሰሳ ከብዙ ስሕተት የሚያደርስ የሥላሴ የስማቸውን ምሥጢር ለይቶ አለማወቅ ነው በባሕርይ የሚጠሩበት ስም አለ በአካል የሚጠሩበት ስም አለ በግብር የሚጠሩበት ስም አለ በባሕርይ የሚጠሩበትን ስም ለአካልና ለግብር በአካል የሚጠሩበትን ስም ለባሕርይና ለግብር በግብር የሚጠሩበትን ስም ለባሕርይና ለአካል ሰጥተው ሲናገሩ የአንድነታቸው የሦስትነታቸው ምሥጢር ፈራሽ ሆኖ ይገኛል ስለዚህ ጠንቅቆ አስተውሎ መመልከት ይገባል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ መባል የአካል ስም ነው አብ ማለት ጥንት መሠረት መገኛ ማለት ነው ጥንት መሠረት መገኛ በመሆንም ወላዲ አሥራጺ ይባላል ጥንት መሠረት አስገኝ በመሆን ወላዲ አሥራጺ ተባለ እንጅ ወላዲ አሥራጺ በመሆኑ አብ የተባለ አይደለም ይህንም ለመረዳት ጎርጎርዮስ ቿኛ የተናገረውን መመልከት ነው ንባብ አእምር ኩሎ ግብረ እምሾ ግብራት ዘውእቶሙ አስማት ወውእቱ ፍጥረት ወስም ወዘመድ ዘይተበሀል ሰብእ ወገብር ወመጋቢ ሰብእሰ በእንተ ፍጥረተ ጠባይዒሁ ወገብርኒ በእንተ ግብርናቲሁ ወመጋቢኒ በእንተ ስም ዘተሠይመ ወናሁ ንቤ ካዕበ በአንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወአኮ እሉ አስማት ዘቦኡ ላዕሌሆሙ ድኀረ አላ እሙንቱ አካላት ወብሂለ ሰብእሂ አኮ ውእቱ ስም ዳዕሙ ውእቱ ፍጥረቱ አስመ ለኩሎሙ ሰብእ ቦሙ ስም በበይናቲሆሙ ለለ እምኔሆሙ እሉ እሙንቱ አዳም አብርሃም ይስሐቅ ወያዕቆብ ወአቃኒመ እግዚአብሔርሰ እሙንቱ አስማት ወአስማትኒ እሙንቱ አቃኒም እስመ ትርጓሜሁ ለአቃኒም አካላት ጽኑዓን ወቀዋምያን ፍጹማነ ገጽ ወመልክከዕ ብሂል ወሥሉስ ቅዱስ ይሰመዩ አስማተ ጽኑዐነ ትርጉም በሾ አካላት ያለውን ግብር ሁሉ በሦስት ግብራት አወቅ እኒህም ፍጥረት ስም ዘመድ የሚባሉ ስሞች ናቸው ፍጥረት የተባለው ሰብእ ሰው መባል ነው ስም የተባለው ገብር አገልጋይ መባል ነው ዘመድ የተባለውም መጋቢ መባል ነው ሰብእ መባሉ ስለ ባሕርዩ መገኘት ነው ገብር መባሉም ተገዥ ስለሆነ ነው መጋቢ መባሱ ስለተሾመ ነው ሰው ስለ አካሉ መገኘት ሰብእ እንደተባለ ስለ አካላቸው ሕላዊ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ ስለ ተገዛ ገብር ስለ ተሾመም መጋቢ አንዲባል ስለ ወለደ ወላዲ ስለ ተወለደ ተወላዲ ስለ ሠረጸ ሠራጺ እንላለን አኒህም ስሞች አካላት ሲኖሩ የኖሩ ናቸው እንጂ ኑረው ኑረው ኋላ የተጠሩባቸው አይደለም ሰብእ መባልም በተፈጥሮው የወጣ ስም ነው እንጂ ኋላ የወጣ ስም አይደለም ለሰዎች ሁሉ እያንዳንዳቸው የሚጠሩበት ኋላ የወጣላቸው ስም አለና ይኸውም አዳም አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ እንዳለው ነው የእግዚአብሔር ዓቃኒም ግን አስማት ናቸው አስማትም ዓቃኒም ናቸው የዓቃኒም ትርጓሜ በመልክከ በገጽ ፍጹማን ሆነው ፀንተው የሚኖሩ አካላት ማለት ነውና ልዩ ሦስት የሚሆኑ አካላትም ፀንተው በሚኖሩ በነዚህ ስሞች ይጠራሉ ብሏል ሃይማኖተ አበው ድርሳን ኛ መቃርዮስ ዘእስከንድርያም ጻዮ ንባብ ወአስማቲሆሙ ሰአካላት አኮ ግብር ከንቱ ሶበ ንሰምዮ ለአብ አበ በአንተ ዘኮነ ወላዲ ወለ ወልድኒ ወልደ በእንተ ዘተወልደ አእምአብ ወለመንፈስ ቅድስኒ መንፈስ ቅድስ በእንተ ዘውጽአ እምአብ ትርጉም አብ ስለ ወለደ አብ ብንለው ወልድንም ከአብ ስለተወለደ ወልድ ብንለው መንፈስ ቅዱስንም ከአብ ስለሠረፀ መንፈስ ቅዱስ ብንለውም አካላት ስማቸው ግብር የሌለው ከንቱ አይደለም ብሏል ሃይማኖተ አበው ከፍል ነገር ግን አንባቢ ሆይ አብን በእንተ ዘኮነ ወላዲ ወልድንም በእንተ ዘተወልደ መንፈስ ቅዱስም በእንተ ዘሠረጸ ስላለ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የግብር ስም መስሎህ እንዳትሳሳት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት የአካል ስም መሆኑን አስተውል አካል ግብርን ያስገኛል አንጂ ግብር አካልን የሚያስገኝ አይደለምና መጻሕፍትም የፊቱን ወደ ኋላ የኋላውን ወደ ፊት ማድረግ ልማድ ነው ጎርጎርዮስ ገባሬ ተአያራት ሃአበው መጩ ሃይማተ አበው ም ዛቿ ከፍል ቁ ማስረጃ ጌታችን ንባብ አልቦ ዘዐርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ አጓለ እመሕያው ትርጉም ማንም ወደ ሰማይ የወጣ የለም ከሰማይ የወረደው ነው እንጂ አርሱም የሰው ልጅ በሰማይ የሚኖር እንዳለ ዮሐ ሾ ንባብጳውሎስም ክርስቶስ ውእቱ ዘወረደ እም ሰማይ ትርጉም ከሰማይ የወረደ ከርስቶስ ነው እንዳለ ሮሜ ጂ ዳግመኛም ንባብ ወዳግም ብአሲ አምሰማይ ሰማያዊ ትርጉም ከሰማይ የመጣው ሁለተኛው ሰው ሰማያዊ ነው እንዳለ ኛ ቆሮ ጣ ይህን የመሰለ በየአንቀጹ ብዙ አለና ያስተውሏል አካል በመለኮት ከዊን ይገናዘባልና መለኮት ተብሎ ይጠራል የአካል ግብር አይገናዘብምና ወላዲ መለኮት ተወላዲ መለኮት ሠራጺ መለኮት ሊባል አይገባም የሚለያዩበትም የግብር ስም በመሆኑ ሦስት መለኮት ከማለት የሚያደርስ ይመስላልናያደርሳልና አብ መለኮት ወልድ መለኮት መንፈስ ቅዱስ መለኮት ቢል ግን አካል በመለኮት ከዊን የሚገናዘብ ስለሆነ አያስነቅፍም አንባቢ ሆይ ሥላሴ በባሕርይና በባሕርይ ግብር በአካልና በአካል ግብር የሚጠሩበት ስም አለና በባሕርይ የሚጠሩበትን በአካል ከሚጠሩበት በአካል የሚጠሩበትን በባሕርይ ከሚጠሩበት በባሕርይ ግብር የሚጠሩበትን በአካል ግብር ከሚጠሩበት በአካል ግብር የሚጠሩበትን በባሕርይ ግብር ከሚጠሩበት ስም አያቀላቀልህ እንዳትቸዝር በቅጥነተ ሕሊና ሁነህ አስተውል የመጻሕፍትን ከላይ መነሻቸውን ከታች መድረሻቸውን ጠንቅቀህ ተመልከት አንዳንድ ጊዜ ስለ አንዳንድ ነገር በንባብ የሚገናኙበት ምክንያት አይታጣምና እንዳትሳሳት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት የአካል ስም እንደሆነ ወላዲ ተወላዲ ሠራጺ ማለት ግን የግብር ስም እንደሆነ በዚህም ልዩነት እንዳለበት በላይኛው አርእስት የተናገረውን በትሕትና በፈሪሃ እግዚአብሔር ሆነህ ተመልከት ሃሃሃህሀሮዐ ራምድ ቃሳያለዳሰፖፉዕ ማተ ሦሰፍቱ ዕሔሐና ዕዳሦ ባሕርይ ይ ስነሯ። ዕሰምው ልብ ቃል እስትንፋስ ማለት ተከፍሎ በሌለባት በአንዲት ባሕርይ ያለ የከዊን ስም ነው ይኸውም ልዩነት ሳለበት አንድነት አንድነትም ሳለበት ልዩነት አለበት ልዩነቱ በከዊን ነው አንድነቱ ግን በሕልውና መገናዘብ ነው ወልድ ሰው ሆነ በተባለ ጊዜ አካል ተዋሐደ እንጂ ባሕርይ አልተዋሐደም እንዳይባል ወንጌላዊ ቃል ሥጋ ኮነ አለ እንጂ ወልድ ሥጋ ኮነ አላለም ባሕርይም ከተዋሐደ የሥላሴ ባሕርይ አንድ ነውና ሾቱ ሰው ሆኑ አንዳያሰኝ ከልብና ከእስትንፋስ ለይቶ ቃል ሥጋ ኮነ አለ ቃልም ማለት በአካለ አብና በአካለ መንፈስ ቅዱስ በኮዊን የምትለይ በሕልውና የምትገናዘብ እንደሆነች ነገር በምሳሌ መዝሙር በሃሌ እንደተባለው አስቀድመን ምሳሌውን መርምረን ዖየከዊን ስም ልብ አብ ለራሱ ለባዊ አዋቂው አዋቂ ሆኖ ለወልደና ለመፈስ ቅዳስ ልበና ዕወቀት ማኑን የማጭሟጫከት ስም ነው ቃልም የወልድ የከዊን ስም ነወ ለሪሱ ነባቢ ተናጋሪ ሆኖ ለአብና ለመፈስ ቅዳስ ንባብ ሟኑ የማለጽበት የከዊን ቃል የወያን ስሙነወ እስትንፋስ የመፈስ ቅዳስ የከዊን ስሙነወ ወንፈስ ቅዳስ ለራሱ ሕያው ሆኖ ለአብና ለወልድ ሕይወት እንደሆነ የምናወቅበት የከዊን ሕይወተ አብ ወወልደ የወሠሆን ስሙነዉው በሁለተኛው አንቀጽ በነፋስና በፀሐይ በእሳትና በቀላይ መስለን ተናግረናልና በማስተዋል ይመለከቷል መለኮት እንደ አካላት ከሾ ይከፈላል የሚል ሰው ይህን ነገር ከራሱ አንቅቶ በልብወለድ ቃል ተናግሮታል እንጂ መጻሕፍት ከተናገሩት ኃይለ ቃልና ከመሰሉት ምሳሌ ምስከር አምጥቶ ለማስረዳት አይቸልም የሥላሴን ባሕርይና አካል እንደ ሰው ባሕርይና አካል አድረጎ አካል የሌለው ባሕርይ ባሕርይም የሌለው አካል የለምና ባሕርይ አካልን ተከትሎ ከሦስት ይከፈላል ይላል መልስ ባያስተውለው ነው እንጂ ይህ ነገር ከሰማይና ከምድር ይልቅ የተራራቀ ነው የሰው ባሕርይ በአካል ቢከፈል በየራሱ ልብ በየራሱ ቃል በየራሱ አስትንፋስ ያለው ሆኖ በየራሱ ልዩ ልዩ ሥራውን ይሠራል አንዳንድ ቅዱሳንም በፀጋ ቢተዋወቁና አንዳንድ ሥራ ቢሠሩ ያደረባቸው መንፈስ ቅዱስ በሀብት አገናኝቷቸው ነው እንጂ የባሕርይና የሕልውና አንድነት ኖሯቸው አይደለምሥላሴ ግን አካላቸው የተለየ ሲሆን ባሕርያቸው ተከፍሎ የሌለበት አንድ ለመሆኑ ማስረጃው የሦስቱ ልብ አንድ አብ ሆኖ አንድ ፅውቀትን ያውቃሉ የሦስቱ ቃል አንድ ወልድ ሆኖ አንድ ነገርን ይናገራሱ የሦስቱ እስትንፋስ አንድ መንፈስ ቅዱስ ሆኖ አንድ የሕይወትን ሥራ ይሠራሉ እንዲህም ከሆነ ሊቃውንት ይለሱ በአካላት ወይትወሐዱ በመለኮት ያሉትን ተመልክቶ ይልቁንም አጤን ይበልጡ ቃለ አጤ እንዲሉ እርሱ ባለቤቱ አነ ወአብ ንሕነ ዮሐ ል አነ በአብ ወአብ ብየ ዮሐ ያለውን ተረድቶ ባሕርየ መለኮት በአካል ከሦስት የማይከፈል መሆኑን ማመን ይገባል ከዚህ ግን ወጥቶ መለኮት እንደ አካላት ከሦስት ይከፈላል ማለት ግን አብን ልብ ወልድን ቃል መንፈስ ቅዱስን እስትንፋስ ማለትን ትቶ እኔና አብ አንድ ነን እኔ በአብ ሕልው ነኝ አብም በእኔ ሕልው ነወ ለሦስቱ በየራሳቸው ልብ ቃል እስትንፋስ አላቸው ብሎ ሦስት አማልከት በማለት የዮሐንስ ተዐቃቢን ሃይማኖት መመስከር ነው ይወልደዋል አይቀድመውም ማለት ቅሉ አካል በተከፍሎ ሲለይ አንድ ባሕርየ መለኮት ተከፍሎ ሳይኖርበት ሦስቱን አካላት በማገናዘብ ማዋሐድ በቅድምና የነበረ ስለሆነ ነው ይህንም ለመረዳት ባስልዮስ ዘቂሣርያ የተናገረውን ይመልከቱ ኛ ንባብ ይደልወነ ናእምር ኀበ ኅብረተ ተዋሕዶተ መለኮት ዘ ሾ አካላት ወናስተዋሕድ በአኀብሮ ዘዚአሆሙ ማለኮት ንእመን በሃይማኖት ከመ ይትወሐድ መለኮት በአብ አስመ እምኅበ አብ ተወልደ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስሂ ወፅአ እምኔሁ እንዘ ኢይቀድም እምካልኡ ወካልኡ እምሣልሱ ወበልደተ ወልድ ወበጸአተ መንፈስ ቅዱስ እምአብ ይትወሐድ መለኮተ ሥላሴሁ ለአምላከነ ትርጉም በአንድ መለኮት ተዋሕዶ የሦስቱን አካላት መገናዘብ ልናውቅ ይገባል በአንድ መለኮት በማገናዘብም ልዩ ልዩ የሆነ አካላትን እናዋሕድ መለኮት አንድ እንደሆነ በማመን በአብ ያለ መለኮት ወልድን መንፈስ ቅዱስን እንዲዋሐድ እንመን አብ ከወልድ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ሳይቀድም ወልድ ከአብ ተወልድዋልና መንፈስ ቅዱስም ከርሱ ሠርዖአል ከአብ ወልድ በመወለዱ መንፈስ ቅዱስም በመሥረፁ የአምላካችን የሦስትነቱን አካል መለኮት ይዋሐዳል ብሏልና ክፍል ሃይማተ አበው ቻነ ከፍል ቁ አሁን በዚህ መስመር ያነበብውን የባስልስዮስን ቃል አስተውሎ የሚመለከት ሰው መለኮትን በአካል ሦስት ማለት ከሚያመጣው ሾልብ ኮቃል እስትንፋስ ከማለት ተጠብቆ በአብ ልብነት ለባውያን በወልድ ቃልነት ነባብያን በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት ሕያዋን ብሎ በአካል ዞ በመለኮት አንድ በምታሰኝ ሃይማኖት ይፀናል መለኮት አንደ አካላት ከሦስት ይከፈላል የሚል ሰው ግን ወልድ ከአብ የሚወለደው ልደት ሰው ሁሉ ከአባቱ እንደሚወለደው ልደት ነው ማለቱ እንደሆነ ጠንቅቆ ማስተዋል ያሸዋል ማናቸውም ልጅ ከአባቱ ሲወለድ ባሕርዩ በአካል የሚከፈልና የሚለይ ስለሆነ አባት ከልጁ ይቀድማል ይበልጣልም ማስረጃ ቴዎዶጦስ ዘአንቆራ ኛ ንባብ ወእመሰ ኮነ ብእሲ አበ ከሥት ነገሩ ከመ የዐቢ አብ አምወልድ ወስሞሂ ያጤይቅ ከመ ውእቱ እምቅድመ ወልቶ ትርጉም ሰው አባት ሲባል ከልጁ እንዲበልጥ ነገሩ የታወቀ ነው አባት መባሉም ከልጁ አስቀድሞ እንደነበረ ያስረዳል እንዳለ ወልድ ግን ከአብ ሲወለድ አካሉ በተከፍሎ ቢለይም ሕላዌ መለኮት በተከፍሎ መለየት የለበትም አወላለዱም ብርሃነ ፀሐይ ተከፍሎ መለየት ሳይኖርበት ከክበብ እንዲገኝ በሕላዌ መለኮት ከአብ ተከፍሎ መለየት ሳይኖርበት ነውና መቅደም መቀዳደም መብለጥ መበላለጥ የለበትም አሁን ማስረጃ አድርገን የጠራነው ቴዎዶጦስ ንባብ ወለነሰሂ ይደልወነ ነሐሊ ዘንተ በሕላዌ መለኮት አላ ነአምን በወልድ ዋሕድ ከመ ውእቱ ቀዳማዊ ምስለ አብ በኩሉ ዘመን ሃይማየተ አበው ምነ ዛሾ ከፍል ቁ ቿ ወወልደ አብ ዋሕድ ይሰመይ ብርሃነ እስመ ብርሃን ዘተወልደ እም ብርሃን ኢይትበሀል ተወልደ እምድኀረ ብርሃን አላ በጊዜ ዘኮነ ቦቱ ውእቱ ብርሃን ይትረከብ ብርሃን ዘተወልደ እምኔሁ ወወትረ ሕልው ምስሴሁ ብርሃንኒ ያጤይቀከ አምሳሊሁ ለወልድ ዘውእቱ ሕልው ምስለ አብ በኩሉ ጊዜ እምቅድመ ኩሉ ዓለም ትርጉም በመለኮት ባሕርይ ይህን ማሰብ ለእኛ አይገባንም ወልድ ዋሕድ በዘመን ሁሱ ከአብ ጋር የነበረ ቀዳማዊ እንደሆነ እናምናለን እንጂ ከአብ የተወለደ ዋሕድ ቃልም ብርሃን ይባላል ከከበብ የተገኘ ብርሃን ከከበብ በኋላ ተገኘ አይባልምና ብርሃን ከበብ በተገኘበት ጊዜ ተገኝቶ ከከበብ ሳይለይ አብሮ ይኖራል አንጂ ብርሃንም የወልድ ምሳሴነቱን ያስረዳሃል ይኸውም ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ ከአብ ጋራ ሁልጊዜ የነበረ ነው አንዳለ ሃይማኖተ አበው ከፍል ይህን ምሳሌ ጠንቅቀን ብንመለከት አማናዊውን አጉልቶ ያሳየናል የሰውም ቃል በተወለደ ጊዜ አወላለዱ አሁን በተናገርነው በብርሃንና በከበብ አምሳል ነው ቃል ከልብ በተከፍሎ መለየት ሳይኖርበት በአካል ከዊን ይወለዳል በአካል ከዊን ተለይቶ መወለዱንም የሚያስረዳ ነገር ከብራና ላይ በቀለም በተጻፈ ጊዜ አካል ገዝቶ ይታያል ይነበባልም ባሕርዩ ግን በተከፍሎ መለየት የለበትምና በልብ ውስጥ ሕልው ሆኖ ሲታሰብ ይኖራል ማስረጃ ቴዎዶጦስ ዘእንቆራ ኛ ንባብ ወለከሂ ቃልከ ዘይትወለድ እምልብከ ይሄሱ ውስቴትከ ተወሊዶ እምልብከ ሃይማጣተ አበው ምነ ዛ ከፍል ቁ ትርጉም ያንተስ ስንኳ ከልብህ የሚገኝ ቃልህ ከልብህ ተገኝቶ በልብህ ውስጥ ሕልው ሆኖ ይኖራል እንዳሰለ ሃይማኖተ አበው ከፍል ንባብ ዳግመኛም ወህየንተ ልብ ዘዝየ ነአምሮ ሰአብ ህየ ወህየንተ ቃል ዘዝየ ነአምሮ ለቃል ዘእግዚአብሔር ከመ ቦቱ ሕላዌ ወቦቱ አካል በፍጹም ገጽ ወመልከዕ ዘከመ ገጸ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ እስመ ውእቱ ወልዱ ለአብ ትርጉም በኛ ባለ በልብ አምሳል አብን እናውቀዋለን አንደ አብና እንደ መንፈስ ቅዱስ ባለ በፍጹም ገጽ በፍጹም መልከዕ አካልና ባሕርይ እንዳለው በእኛ ባለ በቃል አምሳል ቃለ እግዚአብሔር ወልድን አናውቃኃለን አብን አህሎ መስሎ የተወለደ የአብ ልጅ ነውና ብሎ የአብ ልብነት በልብ የወልድ ቃልነት በቃል የመንፈስ ቅዱስ አስትንፋስ በአስትንፋስ መመሰላቸውን ያስረዳል ሃይማኖተ አበው ከፍል ልጅ ከአባቱ ባሕርይ በአካል ተለይቶ የሚከፈል ስለሆነ አባትና ልጅ አንድ ልብ አንድ ቃል አንድ እስትንፋስ በመሆን አይገኙም ወልድ ግን ከአብ ሲወለድ ባሕርይ እንደ አካሉ የማይከፈል አንድ ስለሆነ ሦስት አካላት በአንድ ልብ በአንድ ቃል በአንድ አስትንፋስ ተገናዝበው ይኖራሉ ይህንም ለመረዳት በየአንቀጹ የተነገረውን መመልከት ነው ሃሃሃህሀሮዐ ሃይማተ አበው ቕ ዛሾ ከፍል ቁ » ዝኒ ከማ ቁ ያምድ ወሴፈድ ማዘፉ ዖረአስዐ ዕሙጳሮታእ ይናገራ ወልድ ማለት አካሉ በቃልነቱ ከዊን ተድኅሮ ሳይኖርበት አብን አህሎ መስሎ ከአብ አካል በመገኘቱ የሚጠራበት የተረከቦ ስሙ ነው ተረከቦውም ተፈልጦ ሳይኖርበት በሕልውና እያለ ነው የነፍስ ቃሏ ከልብነቷ ተገኝቶ ሳይለይ በአካሏ ሕልው ሆኖ እንደሚኖር ማነጻጸር ነው ማስረጃ ቄርሎስ በእስተጉቡእ ንባብ ወልድ ዋሕድ በሕላዌሁ ዘእምኀበ እግዚአብሔር አብ ይሰመይ ቃለ እስመ ውእቱ ተወለደ እም አብ ትርጉም ወልድ ዋሕድ ከእግዚአብሔር አብ ተወልዶ በአብ ሕልው ሆኖ በሚኖርበት ባሕርዩ ቃል ይባላል አንዱ እርሱ ከአንድ አብ ተወልዷልና ብሏል ተወላዲ ማለት ግን በተከፍሎ የሚጠራበት የግብር ስሙ ነው ወልድ ማለትና ተወላዲ ማለት በግሥ አንቀጽ መልከ ፊደሉ አንድ ሲመስል የምሥጢር ልዩነት እንዳለው አሁን የተናገርነውን የተረከቦንና የተከፍሎን ምሥጢር ጠንቅቆ ማስተዋል ነው ተረከቦ ያልነውም ተረከቦ ጫት መኘት ሜት ነው ወደ ኋላ ሳይቀር የአካሉ ሕላዌ ከአብ አካል የተለየ ሆኖ በፍጹም ገጽና በፍጹም መልከ መታወቁ ነው እንጂ እግዚአበሔር የተገኘበት ጊዜ አይደለም ማስረጃ ሱኑትዩስ ንባብ ወኢይትረከብ ሀልዎቱ እምኃበ ወኢምንትኒ ትርጉም አኗኗሩ ከምንም ከምን አይገኝም እንዳለ ከምንምተገኘ አይባልም ሠለስቱ ምዕትም በቅዳሴ ንባብ ኢይከል መኑሂ ይባዕ ማዕከለ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከመ ያዕምር ዘከመ እፎ ህላዌሁ ወለዶ አብ ለወልዱ ኢይትበሀል ዘጊዜ ወበዘከመዝ መዋዕል ወለዶ ኢይትአመር ልደቱ እም አብ እስመ ዕፁብ ውእቱ ወኢይትአወቅ ህላዌሁ እስመ ስውር ውእቱ ትርጉም ማንም ማን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ መካከል ሊገባ አይቸልም አኗኗሩ እንደምንም አንደሆነ ያውቅ ዘንድ አብ ልጁን ወልዶታል ነገር ግን አብ ልጁን በዚህ ጊዜ እንዲህም ባለ ዘመን ወለደው አይባልም ከአብ መወለዱ አይመረመርም የሚያስጨንቅ ነውና አኗኗሩ አይታወቀም የተሰወረ ነውና እንዲሱ ተከፍሎም በመለየት እንደሆነ የሚያስረዳ ሊቃውንት በብዙ አንቀጽ ገልጸዋል ንባብ ተጋብኦ በተከፍሎ ወተከፍሎ በተጋብኦ ሃይጭተ አበው መጭ ከፍል ቁ ትርጉም አንድነት በመለየት መለየትም በአንድነት አለ ጓኛ አትናቴዎስ ዘአንጾኪያ ኛ ሱኑትዩስ ዘእስክንድርያ ኛ ከርስቶዶሉ ዘእስክንድርያ እመልዕከተ ሲኖዲቆን አንቀጽ ሁለተኛ እይ ንባብ ኀቡራን አንበለ ተሌልዮ ወሊሉያን አንበለ ትድምርት ትርጉም ባለመለያየት አንድ ናቸውና አንድ ባለመሆንም ልዩ ናቸው እያሉ ይናገራሱና ቆዝሞስ ዘእስከንድርያ ከፍል ኛ ሃይ አበው ጓኛ ወልድ ማለትና ተወላዲ ማለት በምሥጢር ልዩነት እንዳለበት በዚህ ማስተዋል ነው ምፇድ ። እንኪያስ ሦስቱ ገጻት በአንድ መንበር ተቀምጠው ከታዩ ነቢዩም መገበር ያለውን ዮሐንስ አፈወርቅና ሳዊሮስ መንግሥት ብለው ከተረጎሙት መንግሥት በአካል የማይከፈል አንድ እንደሆነ ታወቀ ተረዳም ኢሳይያስም ንባብ ርኢከዎ ለእግዚአብሔር እነዘ ይነብር ዲበ መንበሩ ልዑል ወነዋኅ ትርጉም እግዚአብሔርን ከፍ ባለ በረጅም ዙፋን ተቀምጦ አየሁት ብሎ አንድ መንበርን አንድ እግዚእን ከተናገረ በኋላ ንባብ ወሱራፌል ይቀውሙ አውዶ ይጸርሁ ወይብሱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ጸባዖት መልዐ ኩሎ ምድረ ስብሐቲከ ትርጉም ሱራፌል በዙሪያው ቁመው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር የሠራዊት ጌታ ምሥጋናህ በምድር መላ እያሉ ይጮሁ ነበር ብሏል ኢሳ ሾ ሦስት ጊዜ መላልሶ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ማለት አካላት ሦስት መሆናቸውን ምስጋናው አንድ ቅዱስ መሆኑንና መንበሩም አንድ መሆኑን ሦስቱ በአንድ መንግሥት አንድ እግዚእ ጌታ መሆናቸውን ያስረዳል እንዲህም መንግሥት በአካል የሚከፈል ሦስት ነው ማለት ስህተት እንደሆነ አስተውል አስተዋይ ልቦና ያለው ሰውም እንዲረዳው የታመነ ነው ያምፇድ ማታኖወቶኗ ማተወሲሮ ማዘፇኖሦጋወደዴ ማገፖ መጋፈሰ ዎፍዕ ማተፖኖሪዲ ማዘፇ ሰደ ሰደ ሮይናረራ ወላዲ መለኮት ተወላዲ መለኮት ሰራጺ መለኮት ማለትን ነቅፈን አብ መለኮት ወልድ መለኮት መንፈስ ቅዱስ መለኮት ማለት አያስነቀፍም ስላልነ አብ ማለትና ወላዲ ማለት ወልድ ማለትና ተወላዲ ማለት መንፈስ ቅዱስ ማለትና ሰራጺ ማለት አንድ አይደለምን። ምን ይለየዋል የሚል ሰው ቢኖር መልሱ ይህን ለይተን በተናገርንበት በአራተኛው አንቀጽ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት የአካል ስም ወላዲ ተወላዲ ሰራጺ ማለት ግን የግብር ስም እንደሆነ በዚህም ልዩነት እንዳለበት ያሳየነውን ምሥጢር ቢመረምር ልዩነቱን ይረዳዋል አሁንም እየደጋገመነ በሚከተለው መስመር እናስጠነቅቀዋለን ወላዲ ተወላዲ ሰራጺ ማለት በአካል ቅሉ የማይገናዘብ ልዩ ነው አብ ወልድ መንፈሰ ቅዱስ ማለት ግን በሕላዌ መለኮት ባለች በባሕርይ ከዊንና በሕልውና የሚገናዘብና የሚዋሐድ ነው መገናዘቡንም የሚያስረዳ ባስልዮስ ዘቄሳርያ ንባብ ለወልድሰ ቦቱ ኩሉ ዘተናዝርነ በእንተ ሕላዌ አብ ዘበድልዎት ዝንቱ ውእቱ ዘተወልደ እም አብ እስመ ወልድ ዋሕድ ውእቱ ወቦቱ ኩሉ ኮነ ወአልቦ ዘይትከፈል ምንትኒ ማዕከሌሁ ወማእከለ አቡሁ ወዝንቱ ስም ዘውእቱ ወልድ ያጤይቅ ሕብረተ ሕላዌሆሙ አስመ ወልዱ ውእቱ ዘተወልደ እምኔሁ ትርጉም ስለ አብ ባሕርይ ጌትነት በሚገባ የተናገርው ሁሉ በወልድ ያለ ነው ይኸውም ከአብ የተወለደው ነው በመለኮት አንድ ባሕርይ የሚሆን አንድ ልጅ ነውና በመለኮት አንድ ሕልውና የሚሆን በአባቱ ያለ ሁሉ በእርሱ አለና ሁሉ የተፈጠረበት አንድ ልጅ ስለሆነ በአርሱና በአባቱ መካከል ምንም ምን መለየት የለም ይኸም ስም ይኸውም ወልድ መባል የባሕርያቸውን አንድነት ያስረዳል ከእርሱ የተወለደ የባሕርይ ልጅ ስለሆነ ብሏል ሃ አበው ከፍል አንባቢ ሆይ በአካል ስም ወልድ ብሎ በመለኮት አንድ ባሕርይ ያለውንና ይህን ስም ይኸውም ወልድ መባል ነው ብሎ የባሕርያቸውን አንድነት ያስረዳል ያለውን ጠንቅቀህ አስተውል በእርሱና በአባቱ መካከል ምን ምን መለየት የለም በማለቱ በሁለቱ አካላት ያለ መለኮት ተከፍሎ የሌለበት አንድ መሆኑን ያስረዳልና ማስረጃ ቴዎዶጦስ ዘእንቆራ ንባብ ንነግረከ ወናሌብወከ ዘንተ ስመ ዘውእቱ ወልድ ከመ ውእቱ ሕላዌ ምስለ አብ ትርጉም ይህንን ስም ይኸውም ወልድ ማለት ነው ከአብ ጋር አንድ ባሕርይ መሆኑን እንዲያስረዳ እንናገራለን ብሏል ሃ አበው ክፍል ይኸውም የባስልዮስን ቃል የመሰለ ነው እንዲህ ባለ ምሥጢር የአካል ስም ከግብር ስም የግብር ስም ከአካል ስም ልዩ ነውና በስህተት ባሕር እንዳትጠልቅ በከህደት ገደል እንዳትወድቅ ተጠንቀቅ ሃይ አበው ከፍል ሸ ምኔ ሾቋፀ ሃይ አበው ዛሾ ያምድ ቋሥዛፊ ዩራጎፖው ሰቃ ሐሰሪፉዕ ጳ ርቴተምውይናገራሰ ጥያቄ ለሥላሴ በየራሳቸው ልብ ቃል እስትንፋስ አለው ካልተባለ አካለ ጎደሎ ያሰኛል እንጂ በአካል ፍጹማን ያሰኛልን። በሦስትነቱ ነው እንጂ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸውና ሦስት ሲሆኑም አንድ ይባላሉና ሦስት ኩነታት እንዳለ ቢታይ ቢታሰብም ስፍሐት ኃይሉን የሚገልጥባቸው እርጥበትና ሁከትም ከስፍሐት አይለዩም ስፍሐትም ከርጥበቱና ከሁከቱ ስለተመሰገኑ ጠባያትም እንዲሁ እናገራለሁ ብሏል ድርሳን ቋጂኛ በዚህ ጊዜ ጠባይዓት የተባሉት ኩነታት እንደሆኑ አንዲት ጠባይም ሦስትነት ባለው ከዊን በሦስት አካላት እንዳለች ያስተውሏል እንዲህም ሲሆን ተወላዲ ቃለ እግዚአብሔር በተወላዲነት ፀንቶ ቢኖር አካሉ ባለች የጠባይ ከዊን ሰው ሆነ አንላለን ጠባይ የሌለው አካል የለምና ይህንም የሚያስረዳ ኪራኮስ ሊቀ ጳጳሳት ዘአንጾኪያ ንባብ ኢይደሉ ይኩን ሕላዌ ዘእንበለ አካል ወኢይደሉ ይትረከብ አካል ዘእንበለ አምሳሉ ዘውእቱ አርአያሁ ትርጉም ባሕርይ ያለ አካል ሊኖር አይችልም አካልም አካልን ከሚመስለው ከጠባይ ጋር ነው እንጂ ብቻውን ሊገኝ አይችልም ይኸውም መታወቂያው ነው ብሏል ክፍል ሃ አበው እንዲህም ባልን ጊዜ ጠባይ ተከፍሎ ባይኖርባት በከዊን በሦስቱ አካላት ትገኛለች ብሏልና ሦስቱ አካላት ሰው ሆኑ እንዳያሰኝ ማስተዋል ነው መለኮት አምላክ ማለት የጠባይ ስማቸው አይደለም በአንድነት ፈጥረው ስለገዙ መለኮት ስለተመለኩም አምላክ የሚያሰኛቸው በአንድነት የሚጠሩበት የባሕርይ ግብር ስማቸው ነው እንጅ እንዲህም ከሆነ ዘንድ ዮሐንስ አፈውርቅ የእግዚአብሔር የባሕርይ ስሙ አይገኝም ብሎ ነግሮናልና ልዩነት አንዳለበት በሰባተኛው አንቀጽ ለይተን ካሳየነው ምከንያት በቀር እግዚአብሔር ማለትና መለኮት ማለት ምስጢሩ አንድ ነው ይህንም የሚያስረዳ ዮሐንስ ዘእስከንድርያ ንባብ እጉዛን አሙንቱ በጽምረተ መለኮት ወበዝንቱ መለኮት ይሰመዩ እግዚአብሔር ትርጉም በአንድ መለኮት አንድ አድራጊነት የተገናዘቡ ናቸው በዚህ በአንድ መለኮት አግዚአብሔር ይባላሉ ብሏል ሃይ አበው ከፍል ጳ ኛ ማስረጃ ከባስልዮስ ዘአንጾኪያ ንባብ አንሰ ሶበ እቤ እግዚአብሔር እብል በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አስመ ውእቱ መለኮተ ሥላሴ ወሠለስቲሆሙ እሙንቱ በመለኮት ኞ ሃይጭተ አበው ዚከራኮስ ዎነ ዛቿ ክፍል ሃይ አበው ው ትርጉም እኔ እግዚአብሔር ባልሁ ጊዜ እግዚአብሔር ማለትን ስለ አብ ስለ ወልድ ስለ መንፈስ ቅዱስ እናገራለሁ የሦስቱ መለኮት አንድ ነውና ሦስቱም በመለኮት አንድ ናቸውና ብሏል አንቀጽ እ ይ እግዚአብሔር ማለትና መለኮት ማለት አንድ ከሆነ አፈወርቅም እግዚአብሔር ማለት የባሕርይ ስሙን አያስረዳም ካለ መለኮት ማለት ስሙ ለማይታወቅ ባሕርይ መጠሪያ ሊሆን የሚነገር ስሙ እንጂ የጠባይ ስሙ እንዳይደለ በዚህ እንረዳለን መጻሕፍትም መለኮት አምላከ ሰው ሆነ ማለታቸው የጠባይ ስሙን ባያገኙት በግብር ስሙ ጠርተውት ነው ዳግመኛም ወልድ ቃል ሰው ሆነ ብለው አምላከ መለኮት ባይሉት ፍጡር የሚሉ እነ አርዮስ ከመ እም ነቢያት የሚሉ እነ ንስጥሮስ ዝርው የሚሉ እነ መርቅያን ባልተረቱም ነበርና ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ አንድ በሚያደርገው ሦስቱን በሚያገናዝባቸው ስም ጠርተውታል እንጂ መለኮት በሦስት ይከፈላል ማለታቸው እንዳይደለ ጠንቅቆ ማስተዋል ነው ሃሃሃህሀሮዐ ሃአበው ዘባስልዮስ መኔ ሻጓ ምጋሃድ ይመ ዮድ ፇርጋጓሜሟው ሦዳንን ይናገ መገቻ ታሮልፈያም ሃረጋሜው ኀ ዕው ኛ ብርሃን ይሆናል ማስረጃ አግናጥዮስ ንባብ አጉዛን እሙእንቱ በፅምረተ መለኮት ዘውእቱ ብረሃን ዘይሰርቅ እምኔሁ ሥላሴ እንዳለ ጥያቄ በዚህ አንቀጽ ብርሃን የተባለ መለኮት ከሦስት የሚከፈል ከሆነ አንዱን ልብስ ሦስት ሰዎች ከሦስት እንዲለብሱ ሦስቱ አካላት አንዱን ብርሃን ከሦስት ተካፈሉት ሊባል ይገባልን። በሕይወት ከሚመሳሰሉ ብዙ ሰዎች አንዱ ቢሞት ሁሉም ሞቱ ያሰኛልን ኮሾኛ አገዛዝ ይሆናል ማስረጃ ነቢዩ ዳዊት ንባብ ውስተ ኩሉ በሐውርት መለኮቱ ትርጉም አገዛዙ በሀገሮች ሁሉ ነው እንዳለ መዝሙር ኛ ጌትነት ይሆናል ማስረጃ ጳውሎስ ንባብ ወከመዝ ይትአመር ኃይሉ ወመለኮቱ ዘለዓለም ትርጉም የዘለዓለም የሚሆን ኃይሉ ጌትነቱም እንዲህ ይታወቃል አንዳለ ሮሜ ጳ ቅዱስ ጴጥርስም ንባብ ዘበኃይለ መለኮቱ ወኀበ ለነ ኩሎ ምግባረ ዘይወስድ ኅበ ሕይወት ወጽድቅ ትርጉም በጌትነቱ ኃይል ወደ ሕይወትና ወደ ጽድቅ የሚወስድ ምግባርን የሰጠን ብሏል ኛ ጴጥ ጳ« ቴሬኔዎስምኮኛ ንባብ ቅዱስ ጳውሎስ እስመ ዘሐመ ተሰቅለ በድካም ሕያው ውእቱ በኃለ እግዚአብሔር ትርጉም ደከሞ የተሰቀለውና የሞተው በእግዚአብሔር ኃይል ሕያው ነው ያለውን ኛ ቆሮ ሲተረጉም ንባብ ወሐይወ በኃይለ እግዚአብሔር ዘውእቱ መለኮት ትርጉም በእግዚአብሔር ኃይል ተነሣ ይኸውም መለኮቱ ነው ብሏል ይ አበው ከፍል በዚህ መለኮት የተባለ ጌትነት ወይም ሥልጣን እንደሆነ ማስተዋል ነው ኛ ከብር ይሆናል ማስረጃ ሐዋርያው ጴጥሮስ ንባብ ከመ በአንተ ዝንቱ ትኩኑ ሱቱፋነ ለመለኮተ ዚአሁ ትርጉም ስለዚህ ነገር የከብሩ ተካፋዮች ትሆኑ ዘንድ ለምግባር ለትሩፋት ሁሉ ኛ ጴጥሮስ ባለው መረዳት ነው ኛ ባሕርይ ይሆናል ማስረጃዛኛ ዲዮናስዮስ ሊቀ ዳዳሳት ዘአንጾኪያ ንባብ ይሴለሱ በአካላት ወይትወሐዱ በመለኮት እንዳለ አንቀጽ እይ ሃሃሃህሀሮዐ ጂኛ አምላከነት ይሆናል ማስረጃ ኛዮሐንስ ዘአንጾኪያ ንባብ ይገብር መንከራተ በመለኮቱ ወይትዌከፍ ሕማማተ በትስብእቱ ትርጉም በአምላከነቱ ተአምራትን ያደርጋል በሰውነቱ መቀበል አንዳለ ክፍል አንድ አመልከተ ሲኖ በኛው አንቀጽ ነገሩን ኋላ በኛ አንቀጽም እናመጣዋለን ያልነው ይህ ነው ሲኖዲቆን ይህ ሁሉ አንድ የሚሆኑበትና የሚገናዘበበብት ነው እንጄ የሚለያዩበት አይደለም ይህን ያህል ስህተት የሚያመጣ የመለኮትን የሚስጢሩን ስልት አስተውሎ አለመመልከት ነው መለኮት በአካላት የሚለይ ቢሆንስ ሦስቱ ባልተጠሩበትም ነበረ ወላዲ ተወላዲ ሰራጺ ማለት በግብር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት በአካል ልብ ቃል አስትንፋስ ማለት በከዊን የሚለያዩባቸው ስሞች ስለሆኑ እየራሳቸው ተጠሩባቸው እንጂ ሦስቱ ሁሉ አልተጠሩባቸውም አምላክ መለኮት ከዊን ማለት ነው እግዚአብሔር ማለት ግን በባሕርይ አንድ የሚሆንበት በሕልውና የሚገናዘበብት በመሆኑ ሦስቱ ተጠሩበት ሐተታሦስቱ መለኮት ለማለት ሳዊሮስ ዘገብሎን በተረፈ ቄርሎስ እስመ ሾቱ ጉልቄ መለኮቱ ያለውን የሚጠቅስ ቢኖር መልሱ ምሥጢሩን ባይመለከት ነው እንጂ ቢመረምረውስ ይህን ምስከር አድርጐ ባልተነሣም ነበር አሁን በአርእስቱ እንደተናገርነውሦስቱ ስለተጠሩበት ሾ ጐልቀ መለኮቱ አለ የሚዋሕዱበት አንድ እንደሆነ ሲያስረዳ መለኮቱ ብሎ በአንድ አንቀጽ ተናገረው እንደ እነሱ አነጋገር ቢሆን ኖሮ ግን መለኮታቲሆሙ ባለ ነበረ እንጂ መለኮቱ ባላለም ነበር ምሥጢሩም አትናቴዎስ ዘእስከንድር ንባብ አምላከ ውእቱ አብ አምላከ ውእቱ ወልድ አምላከ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ወኢይትበሀሉ ሠለስተ አማልከተ አላ አምላከ ትርጉም አብ አምላክ ነው ወልድ አምላክ ነው መንፈስ ቅዱስ አምላክከ ነው ነገር ግን አንድ አምላከ ይባላሉ እንጂ ሦስት አምላከ አይባሉም ሃይ አበው ከፍል ብሏል ልብ ቃል እስትንፋስ ማለት በከዊን የሚለያዩበት በህልውና የሚገናዘበብት እንደሆነ ከዚህ አስቀድመን በኛው አንቀጽ ተናግረናል ይህውም ሕያዋን የሚያሰኛቸው ሕይወት ነው ሕይወትም እንደሆነ ንግበር ሰብአ በአርአያነ ባለው በሰው ይታወቃል ሰው አእምሮው ንባቡ እስትንፋሱ የተለየው እንደሆነ ሞተይባላል ካልተለየው ግን ሕያው ነው ይባላል አንጂ ሞተ አይባልም የእግዚአብሔር የባሕርዩን ከዊን ከሚመሰከሩ መጻሕፍት አንድ ደገኛ መጽሐፍ ሰው ነውና ማስረጃ ቅዱስ ቁርሎስ ዘአስትጉቡዕ ንባብ ወኮንኩ መጽሐፎ ሰከርስቶስ ትርጉም የክርስቶስ መጽሐፍን ሆንኮኩ ንባብ ወየአምር መጽሐፈ እግዚአብሔር ሞመሃይማየተ አበው ዘአትናቴዎስ ምነ ትርጉም የእግዚአብሔር መጽሐፍ ሰው ያውቃል አንዳለ በኛው አንቀጽ ነገሩን ኋላ በኛ አንቀጽም አናመጣዋለን ያልነው ይህ ነው ኮኛ አንቀጽ ሥዛፊ ዓም ዕዳሦቃሳ ዳርረጠሩ ለሥላሴ በየራሳቸው ልብ ቃል እስትንፋስ አላቸው ካልተባለ ሥላሴ በአካል ፍጹማን ናቸው አያሰኝም ለተባለው ጥያቄ መልሱን ከነምስከሩ በኛው አንቀጽ አስረድተናል ከዚያ የቀረውንም በዚህ አንቀጽ እንናገራለን ለሦስቱ አካላት በየራሳቸው ቃል አላቸው ማለት እንዳይገባ ቃላቸውም አንድ ወልድ ብቻ እንደሆነ የሚያስረዳ ነገር በሥነፍጥረት እናሳያለን እግዚአብሔር በዕለተ እሑድ ለይኩን ብርሃን ካለ ጀምሮ በዕለተ ዓርብ ንግበር ሰብአ በአርአያነ አስኪል ድረስ በነቢብ የፈጠረው ፍጥረት ብዙ ነው በማንኛቸው ቃል ተፈጠረ ይባላል በአብ በተለየ ቃሉ እንዳይባል ፍጥረት የተፈጠረ በወልድ ቃልነት እንደሆነ መጻሕፍት በብዙ አንቀጽ ይመሰከራሱ ከብዙም በትቂቱ የሚያስረዳ ዮሐንስ ወንጌላዊ ንባብ ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ትርጉም አስቀድሞ ቃል ነበረ ብሎ ተነሥቶ ንባብ ወቦቱ ኩሉ ኮነ ወዘእንበሌሁሰ አልቦ ዘኮነ ወኢምንትኒ አምዘኮነ ትርጉም ሁሉም በእርሱ ሆነ ያለ አርሱ ግን የሆነ የለም ምንም ከሆነው ሁሉ ብሏል ዮሐ ቅዱስ ጳውሎስም ንባብ ወአሐዱ እግዚእነ ኢየሱስ ከርስቶስ ዘኩሉ በእንቲአሁ ወንሕነኒ ቦቱ ትርጉም አንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሱ በእርሱ የሆነ እኛም በእርሱ ብሏል ቆሮ ቿ ዳግመኛም ንባብ ወበድኀሪሰ መዋዕል በወልዱ ዘረሰዮ ወራሴ ለኩሉ ወቦቱ ፈጠሮ ለኩሉ ትርጉም እርሱ በኋለኛው ዘመን በልጁ ነገረን ሁሉን ወራሽ ባደረገው ዓለሙንም ሁሉ በፈጠረበት ብሏል ዕብ ከአረጋዊ መንፈሳዊ ማስረጃ ንባብ ወዓዲ ይሰመይ ወልድ በእንተ ዘተፈጥረ ቦቱ ኩሉ ወካዕበ ወልድ ይሰመይ ቃለ እስመ አእምሮቱ ለእግዚአብሔር ውእቱ ትርጉም ዳግመኛ ሁሉ በእርሱ ስለተፈጠረ ወልድ ይባላል ወልድም ቃል ይባላል የአግዚአብሔር መታወቂያው ነውና ብሏል ድርሳን አትናቴዎስም ዘእስከንድሪያ ኛ ወደ አከኒጦስ በጻፈው መጽሐፍዎ መአከኒጦስ የቆጵሮስ ኤጳስ ቆፅስ ነበር። ብሎታልና ዘዳ በዚህ አንቀጽ ንግበር ሰብአ በአርአያነ ወበአምሳሊነ ያለው የአብ ቃል እንደሆነ ያስረዳል ነቢይም ንባብ ወበቃለ እግዚአብሔር ፀንዓ ሰማያት ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኩሉ ኃይሎሙ ትርጉም በአግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ተሠሩ ሃሃ አበውምነ ጓ ሠራዊቶቻቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ ብሏል መዝ ቋ ዮሐንስ ወንጌላዊ በቅዳሴው ንባብ ወኩሎ ተግባረከ ፈጠርከ በቃልከ ትርጉም ፍጥረትህን ሁሉ በቃልህ ፈጠርህ ብሏል አትናቴዎስም ዘእስከንድርያ ንባብ ፈጠረ አብ ኩሎ ፍጥረተ በቃሉ ዘውእቱ እምነ መለኮቱ ወበመንፈሱ ቅዱስ ትርጉም አብ ፍጥረቱን ሁሉ ከባሕርይው በተገኘ በቃሉና በቅዱስ መንፈሱ ፈጠረ ብሏል ሃይ አበው ከፍል ሠለስቱ ምዕትም ኮኛ በፀሎተ ሃይማኖት ንባብ አብን ገባሬ ሰማያት ወምድር ዘያሰተርኢ ወዘኢያስተርኢ ትርጉም ሰማያትና ምድርን የሚታየውንም የማይታየውንም የፈጠረ ወልድንም ንባብ ዘቦቱ ኩሉ ኮነ ወዘእንበሌሁሰ አልቦ ዘኮነ ወኢምንትኒ ዘበሰማይኒ ወዘበምድርኒ ትርጉም ሁሉ በእርሱ የተፈጠረ በሰማይም በምድርም ያለ እርሱ የተፈጠረ ምንም የለም ብለዋል ሃ አበውቄሟቼ» ጓጸ ይህን የመሰለ በየአንቀጹ የተነገረው ብዙ ነው ነገር ግን መጻሕፍት ፍጥረት ሁሱ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ገንዘብ በሚሆን በአንድ ቃል ተፈጠረ ሲሉሦስቱን አካላት በአንድ መለኮት የማያገናዝቡ ሰዎች በየራሳቸው ሦስት ቃሎች አሉ ባሉ ጊዜ በማናቸውም ቃል ተፈጠረ ይሉት ይሆን ወይስ በሠርግ በዱለት በገበያ የተሰበሰበ ሰው ሁሉም በየቃሉ እየተናገረ በአንድነት ሲጮህ እንዲሰማ ሦስቱ አካላት በየቃላቸው አንድ ጊዜ ሲናገሩ ተሰሙ ይሉ ይሆን መጻሕፍት በመሰከሩ ነው እንጂ በጉሥዓተ ልብ አይደለምና ይህ ከብዙ ስህተት የሚያደርስ ስለሆነ ይህን ነገር ጠንቅቀን እናስተውል ከፍል ሦስቱን በአንድ ልብ እንዲያውቁ በአንድ ቃል እንዲናገሩ በአንድ እስትንፋሰ የሕይወት ሥራ እንዲሠሩ የሚያደርጋቸው ሦስቱን የሚያገናዝብ መሰኮት አንድ ቢሆን ነበረ መለኮት በአካል የሚለይ ሦስት ከሆነ ግን ለሦስቱ በየራሳቸው ልብ ቃል እስትንፋስ አላቸው ማለት ግድ ነው እንዲህም ከሆነ መጻሕፍት የተናገሩት ቃል ሁሉ ሐሰት ሆነ ማለት ነው እኛስ በአካል ሦስት በመለኮት አንድ ብለው አብን ልብ ወልድን ቃል መንፈስ ቅዱስን አስትንፋስ በማለት መጻሕፍት የመሰከሩት እውነት እንደሆነ አውቀን ተረድተን እናምናለን ይህንም የሚያስረዳ አቡሊድስ ወልድሂ ቃሎሙ ለአብ ወመንፈስ ቅዱስ ወመንፈስ ቅዱስሂ መንፈሶሙ ውእቱ ለአብ ወወልድ ወበዝንቱ አአመርነ ከመ ዱ ውእቱ መለኮተ ስላሴ ወሎቱ ንሰግድ ወአበዊነሂ እለ ተጋብኡ በኒቅያ ይቤሉ እመቦ ዘይፈልጥ መለኮቶ ለአግዚአብሔር አብ እም ወልድ ወእም መንፈስ ቅዱስ ውጉዘ ለይኩን ብለዋል ብሏል አንቀጽ ቋኛ አይ ዮሐንስ ዘእስከንድርያም ንባብ አአምን በዱ አምላክከ ወአአምር ተዋሕዶተ ሥላሴ ወሥላሴ በተዋሕዶ ወተዋሕዶትኒ በእንተ መሰኮት ዘሾ አካት በአሐቲ ከብር ወሥላሴኒ ዓዲ በእንተ ተዋሕዶተ አምላክኒ ዘኮ አካላት ዘውእቶሙ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እስመ ምሥጢረ ሥላሴ ይትሌለይ በአካላት ወኢይትሌለይ በመለኮት ወለአመኒ ንስምዮሙ ለኮ አካላት በሾ አስማት ኢንሬስዮሙ ሠለስተ አማልከተ ወኢይከውን ዝንቱ አላ አምላከ ዘውእቱ አብ ምስለ ወልዱ ወመንፈስ ቅዱስ እምቀዲሙ እንበለ ፍልጠት ትርጉም በአንድ አምላከ አምናለሁ አንድነት በሦስትነት ሦስትነትም በአንድነት እንዳለም አውቃለሁ አንድነትም በአንዲት ከብር ያሱ የሾቱ አካላት መለኮት አንድ ስለሆነ ነው ዳግመኛም በአምላካችን ተዋሕዶ ላይ የሚነገር ሦስትነትም አካላት ሦስት ስለሆኑ ነው እኒሁም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው የሥላሴ ምሥጢር በአካል ይለያያል በመለኮት ግን አይለይምና ሦስቱን አካላትም በሦስት ስሞች ብንጠራቸው ሦስት አማልክት አናደርጋቸውም ሦስት አማልከት ማለት አይገባምና አንድ አምላክ ናቸው እንጅ ይኸውም ከጥንት ጀምሮ ያለመለየት ከልጁና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ የነበረ አብ ነው ብሏል ሃይ አበው ድርሳን ወልደም ለአብ ለመፈስ ቅዳስ ቃላቸው ነወ መነፈስ ቅዳስም ለአብ ለወልድ እስትንፋሳቸው ነወ የሦስቱ አካላት ጫኮት አንድ አንደሆነ በዚህ አመን ለርሱ እንሰግዳለን። መሃ አበውገጽ ምነ ሽሃ አበውነ ጻ ፀ ዳግመኛም ንባብ አንዘ ሊሉያን አሙንቱ ይከውኑ እስመ መለኮተ ሥላሴ ወበሰለስቲሆሙ ሀሎ መለኮት ትረጉም ልዩ ሲሆኑ በአንድነት ይኖራሱ የሦስቱ መለኮት አንድ ነውና በሦስቱም አካላት አንድ መለኮት አለና ብሏል ሃይአበው ድርሳን ቋኛ ዮሐንስ ዘእስከንድርያም ንባብ ንሕነሰ ነአምን ከመ ወልድ ይትዋሐድ በመለኮት ምስለ አብ ወመንፈስ ቅዱስ ወእመቦ ዘኢየአምን ከመ መለኮት ንሕነ ናውግዞ ትርጉም እኛስ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በመለኮት እንዲዋሐድ እናምናለን መለኮት አንድ እንደሆነ የማያምን ቢኖር ግን እኛ እናወግዘዋለን ብሏል ኪራኮስም ኛ ንባብ ወእሙንቱ ይነብቡ በዘያብህም ልሳናቲሆሙ እንተ ኢኮነት ግሥጽተ አኮ ከመዝ ሃይማኖትነ ለነሰ ለርቱዓን አላ አምላከ ንሰብከ ወ ሕላዌ ወ መለኮተ ወ ኃይለ ወኢንብል ከመ በዝየ ሱታፌ ለ አካላት በከመ ይቤ ዮሐንስ ዘይሰመይ ተዐቃቢ ዘይትሜካህ በእበዱ ምስለ አለ ይብሉ ሠለስቱ አማልእክት ወሠለስቱ ሕላዌ ዘሠለስቱ አካላት አኮ ዝንቱ ንባበ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትርጉም ያልተሠራች ያልተቀጣች አንደበታቸውን ምላሽ የሚያሳጣ ነገርን ይናገራሉ የቀና እምነትን የምናምን የእኛ ግን እምነታችን አንድ አምላከ ብለን ነው እንጅ ሦስት አማልከት ብለን አይደለም በአንድ ኃይል ያለ አንድ ባሕርይ አንድ መለኮት እንደሆነ እናስተምራለን በዚህ አንቀጽ መለኮትን አንድ ነው እንዳልነ ልዩ ልዩ የሚሆኑ አካላትን አንድ የምንል አይደለንም በስንፍናው የሚመካ ተዐቃቢ የሚባል ዮሐንስ ሦስት አማልከት ከሚሱ ሰዎች ጋራ የሦስቱን አካለት በባሕርይ ሦስት እንዳለ መለኮትን አንድ በማለታችን አካላትን አንድ አንልም ይህ የቅድስት ቤተከርሰቲያን አነጋገር አይደለምና ብሏል ይ አበው መልዕከት ዳግመኛም ንባብ ንትዐቀብ ከመ ኢንምሀር በልሳናቲነ በዝንቱ መካን ከመ ንብል ሠለስቱ አማልክት ወሾ ሕላውያት እስመ ዘይብል ዘንተ ናሁ ተሀበለ ያስተጋብዕ ሎቱ ብዙኃነ አማልከተ ትርጉም ሦስት አካላት በማለታችን ሦስት አማልክት ሦስት ሕላውያት የማለትን ትምህርት ለአንደበታችን ልማድ ከማድረግ እንጠበቅ ይህን የሚል ሰው እነሆ ብዙ አማልከትን ይሰበስብ ዘንድ ይደፍራልና ብሏል መልእ ና አበ ዮሐንስ ዘአንጾኪያ ጓኛ ንባብ ንህነሰ ናሰትት ቃሎሙ ለአላውያን እለ ይትአመኑ ብዙኃነ አማልከተ ወሕላውያተ ፍሉጣነ ለጳ እግዚአብሔር ዘኢይትከፈል በሕላዌ መለኮት ወናወግዝ ዓዲ አለ ይብሉ ሠለስቱ መለኮት አንተ ዘአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ትርጉም እኛስ በመለኮት ባሕርይ ለማይለይ ለአንድ እግዚአብሔር ልዩ ልዩ ሕላውያትን የሚሰጡ ብዙ አማልከትን የሚያመልኩ የአላውያንን ትምህርታቸውን እንነቅፋለን ዳግመኛም የአብ የወልድ ሃአበው ገጽ ። የታተሙ ናዓትት ይላል ጻ የመንፈስ ቅዱስ የሚሆን መለኮትን ሾ የሚሉትን እናወግዛለን ብሏል ሃይ አበው ከፍል ዳግመኛም ንባብ ወሶበሂ ንቤ ሠለስቱ አካላት በበአካላቲሆሙ ንቤ ባሕርየ ፍጹመ ወጳ ሕላዌ ወ መንግሥት ወ እበይ ወጳ ከብር ይትበሀሉ በእንተ አሉ ሠለስቱ አካላት አብ ብርሃን ወልድ ብርሃን መንፈስ ቅዱስ ብርሃን እንዘ ብርሃን ዘኢይትከፈል ወዘኢይትዌለጥ በሕላዌ መለኮት ወዓዲ ንብል አብ ሕይወት ወልድ ሕይወት መንፈስ ቅዱስ ሕይወት እንዘ ሕይወት ወካእበ ይተበሀል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ወለለ አምአካላት ሕላዌ ወ አምላክከ እሙንቱ ወኢይትበሀሱ አማልክተ አኮ ዘንተአመን በሾ እደው ወጀ አማልከት ወኢበ መለኮት አላ ንትአመን በ አካላት ወ ገጻት አንተ ባሕርየ መለኮት ትርጉም ሾ አካላት በየአካለቸው አሉ ብንል ፍጹም ባሕርይን ሕልውናንም አንድ ብለን መንግሥት አንድ እበይ ጌትነት አንድ ከብር ነው እንላለን አካላት ስለሆኑ በመለኮት ሕላዌ አኗኗር የማይከፈልና የማይለይ አንድ ብርሃን ሲሆን አብ ብርሃን ወልድ ብርሃን መንፈስ ቅዱስ ብርሃን ይባላሉ ዳግመኛም በመለኮት አኗኗር አንድ ሕይወት ሲሆኑ አብ ሕይወት ወልድ ሕይወት መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ነው እንላለን ዳግመኛም አብ አንድ ይባላል ወልድ አንድ ይባላል መንፈስ ቅዱስ አንድ ይባላል ከአካላትም እያንዳንዱ አንድ ሕላዌ አንድ አምላክ ናቸው ሦስት አማልክት ግን አይባልም መገናዘብ እንደሌላቸው ሰዎች አድርገን በሦስት ሰዎች በሦስት አማልከት በሦስት መለኮት የምናምን አይደለንም ባሕርየ መለኮት ሃይማተ አበው መቕ ዛኮ አንድ በሚያድርጋቸው በሦስት አካለት በሦስት ገጻት እናምናለን እንጂ ብሏል ዳግመኛም ዛሾኛ ዲዮናስዮስ ዘአንጾኪያ ንባብ ወንትአምን በዝንቱ ሕላዌ ወንሰግድ አሐተ ስግደተ ብሎ ተነሥቶ አንቀጽ አይ ንህነሰ ንሰብከ ከመዝ ወንሰግድ ለ አምላከ ባሕቲቱ ወንትአመን ከመ መለኮት ዘሠለስቱ አካላት ወኢንበውአ ውስተ ከፊለ መለኮት ወመንግሥት አላ ንብል ሕላዌ ወ መንግሥት ወአሐቲ ሥምረት ወ አካላት ወ ገጻት እንበለ ተዘርዎ ትርጉም እኛስ እንዲህ እናስተምራለን ለአንድ አምላከ ብቻም አንሰግዳለን የ አካላት መለኮትም አንድ እንደሆነ አናምናሰለን መለኮትንም መንግሥትንም ወደ መከፈል አንገባም አንድ ሕልውና አንድ መለኮት አንድ መንግሥት አንድ ፈቃድ ያለመለያየትም ሦስት አካላት ሦስት ገጻት እንላለን እንጂ ብሏል አመልዕከተ ሲኖዲቆን ዳግመኛም ንባብ ውእቱሰ አምላከ ወአኮ ሾ አግዚእ ወአኮ ብዙኃን ወከብረ ምልከናሂ ልዑል ለመለኮት ወበመለኮት ምልክና ወቅድስት ሥላሴ ይእቲ ትትመለከ ወትትአመር በሾ አካላት ወተዋሕዶተ መለኮቶሙ ርሑቅ እምኩሉ ክፍለት ወእመኩሉ ፍልጠት ሞሃ አበው ዘዮሐንስ ዎነ ትርጉም እርሱስ አንድ አምላከ ነው እንጂ አማልከት አይደለም አንድ ጌታ ነው እንጅ ሦስት ጌቶች አይደለም ከፍ ያለ የአምላከነት ከብርም ለመለኮት ነው መግዛትም በመለኮት ነው ልዩ ሦስትነትም በሦስት አካላት አንዳለች ታውቋል በአንድነትም ትመሰካለች የመለኮታቸውም አንድነት ከመከፈል ከመለየትም የራቀ ነው ብሏል ኛ እመልዕከተ ሲኖዲቆን ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙም ወኢይትሀበሉ ኅጉላን ያብኡ ውስተ ቅድስት ሥላሴ ፍልጠተ መለኮት ብሏል አንቀጽ ጳ አይ ሃይ አበው ሱኑትዮስ ዘእስከንድርያ ንባብ ዘኢየአምን ወዘኢይትአመን ከመ መለኮቶሙ ወ ህላዌሆሙ እንተ ሠለስቲሆሙ ወ ቃሎሙ ወጳ ምግባሮሙ ውጉዘ ለይኩን ትርጉም ሦስት ሲሆኑ መለኮታቸው አንድ ሕልውናቸውም አንድ ቃላቸውም አንድ ምግባራቸው አንድ እንደሆነ የማያምንና የማያሳምን የተለየ ይሁን ብሏል ሃይ አበው ከፍል ጓኛ አትናቴዎስ ዘአንጾኪያም ወሶበሂ ንቤ እግዚእ ወ ህላዌ ወ መለኮት ብሏል አንቀጽ እይ ። በወልድ አካል ብቻ ባለ ኃይልና ክሂል ሥልጣን ተነሣ አንዳይባል እግዚአብሔር ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው በእግዚአብሔር ኃይልና መንፈስ እንደተነሣ መጻሕፍት ይመሰከራሱ ማስረጃ ብፁዕ ጳውሎስ ንባብ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ ወበመንፈሱ ቅዱስ ከመ ተንሥአ እሙታን ኢየሱስ ከርስቶስ ትርጉምበኃይሉ የአግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አሳየ በቅዱስ መንፈሱም ከሙታን ተለይቶ እንደተነሣ ኢየሱስ ክርስቶስ ብሏል ሮሜ ቨ ዳግመኛም ንባብ በከመ ውእቱ ከርስቶስ ተንሥአ እሙታን በስብሐተ አቡሁ ከማሁ ንሕነኒ ናንሶሱ ውስተ ሐዳስ ሕይወት ትርጉም ክርስቶስ በአባቱ ጌትነት ከሙታን ተለይቶ እንደተነሣ እኛም እንደሱ ተነሥተን በአዲስ ሕይወት እንኖራለን ብሏል ሮሜ ዳግመኛም ንባብ እመሰ መንፈሱ ለዘአንስኦ ለኢየሱስ እሙታን ዘኅዱር ላዕሌክሙ ውእቱ ዘአንስኦ እሙታን ለኢየሱስ ያሐይዋ ለነፍስትከሙኒ በውእቱ መንፈሱ ዘየኀድር ላዕሌከሙ ትርጉም ኢየሱስን ከሙታን ለይቶ ያስነሣው የአግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ካደረባቸሁ ኢየሱስን ከሞታን ለይቶ ያስነሣው አሱ መንፈስ ቅዱስ አድሮባቸሁ ባለ በሕይወትነቱ ሥጋችሁን ሕያው ያደርጋታል ብሏል ሮሜ ቿ ንባብ እመ ከመ ተአምን በአፉከ ከመ ክርስቶስ ውእቱ እግዚእ ወተአምን በልብከ ከመ አንሥኦ አግዚአብሔር እሙታን ተሐዩ ትርጉም በአፍህ ብትናገር ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በልብህም ብታምን አግዚአብሔር ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ትድናለህ ብሏሷል ሮሜ ሀ ይህን የመሰለ በየአንቀጹ የተነገረው ብዙ ነውና ከዚህ ቀጥሎ በተመለከተው ምዕራፍና ቁጥር እየገቡ መመልከት ነው ኛ ቆሮ የአስክንድርያ ሊቀ ዳዳሳት ቄርሎስም ንባብ ተብህለ በእንቲአሁ ከመ አንሥኦ አብ እሙታን ትርጉም አብ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ስለ እርሱ ተነገረ ብሏል ዮሐንስ አፈወርቅም ንባብ ዘከመ ገብረ እዘዘ ኃይሉ ዘገብሮ በከርስቶስ ዘአንሥኦ አሙታን ትርጉም ከሙታን ለይቶ ባስነሣው በከርስቶስ እንዳደረገው ተአምራቱ ብዛት ያለውን ኤፌ ሲተረጉም ንባብ ትርጓሜሁ ለዝ እስመ በኃይል ዘቦቱ አንሥኦ ለከርስቶስ ይስሕበነ ኀቤሁ ትርጉም የዚህ ትርጓሜው ክርስቶስን በአስኮነኮሣበት ኃይል አስነሥቶ ወደ እርሱ አቅረቦናል ማለት ነው ብሏል ድርሳን ሾ ዳግመኛ ንባብ ዘንተ ንብል በእንተ ዘውእቱ እምኔነ ዝንቱ ዘአንሥአ እግዚአብሔር እምነ ሙታን ትርጉም ከእኛ ባሕርይ ስለተገኘ ሥጋ ይህን እንናገራለን ይኸውም እግዚአብሔር ከሙታን ለይቶ ያስነሣው ነው ብሏል ድርሳን ዳግመኛም ንባብ ወሶበ ትሰምዑ ቃለ ዘይብል ከመ እግዚአብሔር አንሥኦ ለከርስቶስ ኢተሐልዩ ከመ ውእቱ ይብል ዘንተ በእንተ ቃል አላ ይቤ በአንተ ሥጋ እግዚእነ ትርጉም እግዚአብሔር ከርስቶስን እንዳስነሣው የሚናገር ቃል ብትሰሙ እርሱ ይህንን ስለ ቃል እንደተናገረ አታስቡ የተናገረ አይምሰላችሁ ከእኛ ባሕርይ ስለነሳው ሥጋ ተናገረ አንጅ ብሏል ድርሳን ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን ሁሉ ተመልከተው በአብ አካል ብቻ ወይም በመንፈስ ቅዱስ አካል ብቻ ባለ ኃይል ከሂል ሥልጣን ተነሣ አንዳይሉ ጌታችን ኢየሱስ ከርስቶስ በገዛ ሥልጣኑ እንደ ተነሣ ሲመሰከር ቤተ አይሁድን ንባብ ንሥትዎ ለዝንቱ ቤተ መቅደስ ወበሥሉስ ዕለት አነሥኦ ትርጉም ይህን መቅደስ አፍርሱት እኔ በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ ብሏል ዮሐ ይህንም ወንጌላዊ ንባብ ውእቱሰ በእንተ ቤተ ሥጋሁ ይቤሎሙ ትርጉም እርሱ ግን መቅደስ ስለሚባል ሥጋው ነገራቸው ብሎ ተርጉሞታል ዮሐ ጳ ዳግመኛም ንባብ ወበእንተ ዝንቱ ያፈቅረኒ አብ እስመ አነ እሜጡ ነፍሰየ ከመ ካዕበ አነሥአ ወአልቦ ዘየሀይደንያ ለልየ እሜጥዋ በፈቃድየ እስመ ብውህ ሊተ አንብራሂ ወብውህ ሊተ ካዕበ አንሥአ ትርጉም ስለዚህ አብ ይወደኛል እኔ ነፍሴን እሰጣለሁና ደግሞ አስነሳት ዘንድ ማንም ከኔ የሚወስዳትም የለም እኔ በፈቃዴ እሰጣታለሁ እንጅ ለእኔ ችሎት አለኝ እሰጣት ዘንድ ዳግመኛም ችሎት አለኝ አሥነሣት ዘንድ ብሏል ዮሐ ቿ ዳግመኛ ንባብ አነ ውእቱ ትንሣኤ ወሕይወት ትርጉም እኔ ነኝ ትንሣኤ ሕይወትም ብሏል ዮሐ ጸ በመጻሐፈ ኪዳንም ንባብ ወተንሣእኩ በሥልጣነ ባሕቲትየ ትርጉም በኔ ብቻ ሥልጣን ተነሣሁ ብሏል እኛም ይህን ሁሉ ተመልክተን ወልድ በአካሉ ባለች በገንዘቡ ኃይል ከሂል ሥልጣን ተነሣ ብለን አምነን በወልድ አካል ያለች ኃይል ከሂልሥልጣን በአብና በመንፈስ ቅዱስ አካል ያለች አንዲት ናትና መጻሕፍት አንድነታቸውንና ሕልውናቸውን ለመንገር አብ አንሥኦ መንፈስ ቅዱስ አንሥአ እያሱ ስለመሰከሩ ወተንሣእኩ በሥልጣነ ባሕቲትየ አለ ብለው ስለአስረዱ ኃይል ከሂል ሥልጣን ከሦስት የማይከፈል አንድ እንደሆነ እምነታችንን እንገልጻለን በዚያውም ላይ የአብ ኃይሉ ጥበቡ የሚባል እርሱ ከርስቶስ እንደሆነ የሚያስረዳ ቅዱስ ዳውሉስ ንባብ ከርስቶስ ኃይለ እግዚአብሔር ውእቱ ወጥበበ እግዚአብሔር ውእቱ ትርጉምክርስቶስ የእግዚአብሔር ኃይል ነው የእግዚአብሔር ጥበብም ነው ብሎ ነግሮናል ኛ ቆሮ ያፍያ በኃይል በከሂል በሥልጣንም በሚሠራ በባሕርይ ሥራ በሦስቱ አካላት መለያየት እንደሌለ የሚያስረዳ ነገር ከሙታን ተለይቶ መነሣት የከርቶስ አካል ብቻ ግብር ሲሆን ማስነሣት የሦስቱ አካላት የባሕርይ ግብር ነው ስለዚህ ከሦስቱ አካላት ለሰው ሁሉ የሚሰጥ ሕይወት በአንድነት በሚሠራ በባሕርይ ግብር እንደሆነ መጻሕፍት ያስረዳሉና ቄርሎስ ንባብ ሕላዌ ዘሥሉስ ቅዱስ ኩሉ ዕበይ ወኩሉ ከብር ይደሉ ለባሕቲቶሙ ወኩሱ ዘኮነ በአምላክነ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወለእመኒ ተብህለ በእንተ አብ ከመ ውእቱ ማሕየዊ ዘእንበለ ኑፋቄ አስመ ለዝንቱ ግብር ወልድኒ ይገብር ወዓዲ ይገብሮ መንፈስ ቅዱስ ወለእመኒ ወልድ ሕይወት በእለ ይፈቅድዎ ለሕይወት እስመ ኢይገብር ዘንተ ዘእንበለ ፈቃደ አቡሁ ዘይትዔረዮ እስመ ቦቱ ለርእሱ ዘአብ ወላዲሁ ወለሊሁኒ ይቤ ከሠተ ኢይገብር ግብረ ምንተኒ ዘእምኀበቤየ አላ እገብር ግብሮ ለአቡየ ዘሀሎ ብዬ ወለእመ ተብህለ በእንተ መንፈስ ቅዱስ ከመ ውእቱ ማሕየዊ ዘአንበለ ኑፋቄ ይገብር ዘንተ እስመ መንፈሰ ሕይወት ውእቱ ንሕነሰ ንብል እስመ ሕይወት ውእቱ በህላዌሁ እግዚአብሔር አብ ወወልድ ዋሕድ ዘተወልደ እምኔሁ በዝንቱ አምሳል ሶበ ይትበሀል ከመ አብ አንሥኦ ለከርስቶስ ንሕነሰ ንረክብ ከመ ለሊሁ አንሥአ ርእሶ ወይቤሎሙ ለአይሁድ ንሥትዎ ለዝንቱ ቤተ መቅደስ ወአነ አነሥኦ በሠሉስ መዋዕል ትርጉም በአካል ልዩ የሚሆን የሥላሴ ባሕርይ አንድ ነው ፍጹም ጌትነት ፍጹም ክብርም ለሦስቱ ብቻ ይገባል ፍጥረት ሁሉ በአምላካችን በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስም ተፈጠረ አብ ያለ ጥርጥር ያለ መለየት ማሕየዊ እንደሆነ ምንም ቢነገር ይህን ሥራ ማዳኑን ያለመለየት ወልድ ይሠራዋልና ወልድም ሕይወትን በሚሹ ሰዎች የሕይወትን ሥራ ቢሠራ በማስነሣት ሕይወት በሚተካከለው መተካከል በአካል ነው በአባቱ ፈቃድ ነው እንጅ ያለ አባቱ ፈቃድ ይህን አይሠራምና የወለደው የአብ ገንዘብ የእርሱ ገንዘብ ስለሆነ አርሱም እራሱ በሕልውናየ ያለ አባቴ የሚሠራውን እሠራለሁ እንጅ እኔ ከራሴ ብቻ አንቅቼ ምንም አልሠራም ብሎ ገልጾ ተናግሯልና መንፈስ ቅዱስም ማሕየዊ እንደሆነ ቢነገር ያለ መለየት ይህን ይሠራል የሕይወት መንፈስ ነውና እኛ ግን እግዚአብሕር አብ በባሕርዩ ሕይወት እንደሆነ እንናገራለን ከእርሱ የተወለደ አንድ ልጁም በዚህ አምሳልማሕየዊ በመባሉ አብ ከርስቶስን አስነሣው ቢባል አኛ እርሱ ራሱ ራሱን እንዳስነሣ ከመጻሕፍት እናገኛለን አይሁድን ይህን መቅደስ አፍርሱት እኔ በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ ብሏቸዋልና እንዳለ ከፍል ለኀበ ነገሥት ሄራን ሃሃሃህሀሮዐ ዳግመኛ ንባብ እግዚእነ ከርስቶስ ያነሥአነ ለኩልነ አስመ ሕያው ውእቱ በእንተ አቡሁ እስመ ዘተወልደ እምአብ ሕያው ዘለዓለም ወበእንተዝ ደለዎ ሎቱኒ ዓዲ ይኩን ሕይወተ አስመ ዘተወልደ እምሕይወት ማሕየዊ ትርጉም ጌታችን ክርስቶስ ሁላችንን ያስነሣናል አባቱ ሕያው ስለሆነ እርሱም ሕያው ነው ለዘለዓለም ሕያው ከሚሆን ከአብ ስለተወለደ ስለዚህም ሕይወት ይሆን ዘንድ ዳግመኛም ለእርሱ ተገባው ሕይወት ማሕየዊ ከሚሆን ከአብ ተወልዷልና ብሏል ከፍል ዛ ኪራኮስም ቋልፄኛ ንባብ ንሕነሰ ፅኑዐን በጽድቅ ወንሰብከ እንዘ ንትአመን በሥሉስ ቅዱስ እለ ሕልዋን ቅድመ ወይሄልው ለዓለም ንጹሐን ሾ አካላት ፍፁማን ዘውእቶሙ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሕላዌሆሙ ወ መለኮቶሙ ወ ግብሮሙ ወአሐቲ ሥምረቶሙ ወአሕቲ ከሂሎቶሙ ሕልዋን በዘዚአሆሙ ወአኮ አብ በርእሱ ባሕቲቱ ዘይገብር ዓዲ አኮ ወልድ ዘይገብር በርእሱ ባሕቲቱ ወአኮ መንፈስ ቅዱስኒ በርአሱ ባሕቲቱ ዘይገብር አላ ዳዕሙ ለዘፈቀደ አብ ይፈጽምዎ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወምግባሮሙኒ እስመ ውእቱ መለኮቶሙኒ አካላት ዕሩያን በአርአያ ወአምሳል ወመልክከዕ ትርጉም በአውነት የፀናን እኛ ቅድመ ዓለም በነበሩ ለዘለዓለም በሚኖሩ በልዩ ሦስት አካላት አምነን ፍጹማን የሆኑ ሦስቱ አካላት ከመለየት ከመለወጥ ንጹሐን እንደሆኑ አናስተምራለን እኒሁም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው በሕልውና አንድ በባሕርይም አንድ በግብርም አንድ በፈቃድም አንድ ሁሉን ማድረግ በመቻልም አንድ እንደሆኑ እናስተምራለን በዘዚአሆሙ በሚገናዘቡበት በልብነት በቃልነት በእስትንፋስነት በየራሳቸው በወላዲነት በተወላዲነት በሠራጺነት የሚኖሩ ናቸው አብ በተለየ አካሉ ብቻውን ሥራ የሚሠራ አይደለም ወልድም በተለየ አካሉ ብቻውን ሥራ የሚሠራ አይደለም አብ ያሰበውን ወልድና መንፈስ ቅዱስ ይሠሩታል እንጅ ግብራቸውም አንድ ነውና ሦስቱ አካላት በግብርና በመመሳሰል በቅርጽም የተካከሉ ናቸው ብሏል ከፍል ጳ ከዚህ በላይ እንደተነገረ ከሦስቱ አካላት ለዓለሙ ሁሉ የሚሰጥ የዘለዓለም ሕይወት በአንድነት በሚሠራ ግብር ከሆነ ይህን የሚያደርጉበት ኃይል ክሂል ሥልጣን ከሦስት የተከፈለ ነው ማለት አይገባምና ይህን በአስተዋይ ልቡና መመልከት ያሻል አንዳንድ ሰዎች በሚናገሩት በሦስቱ አካላት ላይ የሚገኝ ዕሪና ብቻ ነው እንጅ ሕልውናም ዋሕድናመገናዘብም አንድነትም አይገኝበትም ይላሉ እንዲህም ማለታቸው መጻሕፍት ስለ ዕሪና እና ስለ ሕልውና ስለ ዋሕድናም የተናገሩትን ምሥጢር አስተውሎ ባለመመልከት ነው ፅሪና የሚነገር በአካል ላይ በሚወድቅ ምሥጢር ነው ሕልውናም የሚነገር በከዊን ላይ በሚነገር ምሥጢር ነው ዋሕድናም የሚነገር ስለ ባሕርይ ነው ወይም ስለ ጠባይዕ በሚነገር ምሥጢር ነው ስለዚህ ከዚህ በላይ ዘርዝረን ያሳየናቸውን ነገሮች ማሳሳትን የሚያመጣ ስልት ስልታቸውን ለይቶ ሳያውቁ የሃይማኖትን ነገር ማስተማር መጻሕፍትንም መጻፍ ምሥጢረ ሥላሴን ያፋልሳል መጻሕፍትንም ያጣላል ሰሚንና ተመልካቹንም ገደል ይሰዳል ማቴ ስለዚህ ጠንቅቆ ማስተዋል ይገባል የዚህን ነገር በሰፊው ልናስረዳ በቻልን ነበር ነገር ግን በብዙ ዘመን አንፈጽመውም ባስልዮስ ዘቂሣርያ ንባብ ወይእዜኒ ናሕፅር ነገረ ወንፈጽም ዘንተ ከፍለ ወንኅድግ ኩሎ አእምሮ ለእግዚአብሔር ዘይመውዕ ኩሎ ግብራተ ትርጉም ነገርን በማሳጠር ይህን ምሥጢር ፍጹም ዕውቀትንም ሥራን ሁሉ ድል መንሣት ለሚቻለው ለእግዚአብሔር እንተው ብሎ እንደተነገረን አ ከፍል ነገራችንን በማሳጠር አንወሰን ኛ አንቀጽ ፖሪዩፀ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact